በኢትዮጵያ አየር መንገድ ትሰራ የነበረች አንዲት ቻይናዊት ሆስተስ በፖሊስ ከአገር ተባረረች

ዋንግ ዤንግዢያን የምትባለው የ28 አመት ሆስተሷ ባለፈው እሁድ ከስልጠና መባረሯን የሚገልፅ ደብዳቤ ከአየር መንገዱ የደረሳት ሲሆን ይህን ተከትሎ በንዴት ከፍተኛ ጉዳት ማድረሷን ለማወቅ ችለናል፡፡ ደብዳቤው እንደደረሳት በአጠገቧ የነበረውን አውሮፕላን መስታወት ከመሰባበሯም በላይ ወደ እንግዳ መቀበያ ዴስክ በመሄድ ጠረንጴዛውን ገልብጣ ሌሎች ሰልጣኞች ላይ ጉዳት ልታደርስ ስትል በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደዋለች ምንጮች አስረድተውናል፡፡ አየር መንገዱ ለፖሊስ እንዳስታወቀው በወቅቱ በዚህች ቻይናዊት ድርጊት የተነሳ ከ580 ሺህ ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት ተጎድቷል፡፡ ካለፈው ሁድ ጀምሮ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የነበረችው ቻይናዊቷ ራሴን አጠፋለሁ ብላ ስለዛተች 24 ሰአት ሙሉ ፖሊስ ጥብቅ ቁጥጥር ሲያደርግባት መቆየቱን ከምንጮቹ ለመረዳት ችለናል፡፡ ቻይናዊቷ ድርጊቱን የፈፀመችው በመተጥ ሀይል ተገፋፍታ እንደሆነ የተናገረች ሲሆን ትላንት አርብ ከእስር ተለቃ ወደቻይና መባረሯን ለማወቅ ችለናል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  በአዲስ አበባ፣ በወልቂጤ፣ በአፋር፣ በደሴና በአዳማ ሙስሊሞች ላይ መንግስት እርምጃ ወሰደ

1 Comment

  1. who is going to pay for the damaged materials. and why the EAL gave a chance for foreigners to work in EAL as Hostess? there are many job less (unemployed) well educated Ethiopian girls.

Comments are closed.

Share