በደቡብ አፍሪካ በአቡነ ያዕቆብ ላይ ተቃውሞ ለማሰማት መዘጋጀታቸውን ምዕመናኑ ገለጹ

(ዘ-ሐበሻ) በደቡብ አፍሪካ የሃገር ቤቱ ሲኖዶስ ሊቀጳጳስ አቡነ ያዕቆብ ላይ ተቃውሞ ለማሰማት ም ዕመናኑ ከፍተኛ ዝግጅት በማድረግ ላይ እንደሚገኙ በስፍራው ለሚገኘው የዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ ዘጋቢ ገለጹ። አዲስ አበባ ስድስተኛውን ፓትርያርክ ለመምረጥ የሄዱት አቡነ ያዕቆብ ወደ ጽረ አርያም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ሲመለሱ ተቃውሞውን ለማድረግ እንደተዘጋጁ የገለጹት ምእመናኑ ሊቀጳጳሱ የቤተክርስቲያን አንድነትን ካሰናከሉት የወያኔ ጳጳሳት ጎን በመቆማቸው እንደሚያወግዟቸው ነው የገለጹት።
በ1997 ዓ.ም የቅድሥት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪ በነበሩበት ወቅት ተማሪዎቹ የአድማ በመቱበት ወቅት ለመንግስት በመሰለል የተማሪዎቹ ተቃውሞ እንዲረግብ ከፍተኛውን አስተዋጽኦ እንዳደረጉ የሚገነገርላቸው አቡነ ያዕቆብ በደርግ ስርዓት የባሀር ሃይል መቶ አለቃ እንደበሩ የሚያውቋቸው ወገኖች ይናገራሉ። አንዳንዶች ደግሞ አይ መቶ አለቃ ሳይሆኑ በደርግ የወጣቶች ብሔራዊ ውትድርና ጢዮ የሚባል ቦታ በውትድርና አገልግለው አሰብ ድረስ ሄደዋል ይላሉ። እነዚሁ የሚያውቋቸው ሰዎችም የምንኩስና ስማቸው አባ ገብርኤል ወልደሚካኤል እንደሚባልና በደርግ ወታደርነት ጊዜ ውስጥ እንደመነኮሱ ይናገራሉ። በሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የተነሳውን ተቃውሞ በማርገብ ለመንግስት ያላቸውን ታማኝነት በማሳየታቸው በ1998 ዓ.ም ሃምሌ ስምንት በደቡብ አፍሪካ ሊቀጳጳስ ሆነው የተሾሙት አቡነ ያዕቆብ በተለይ አቡነ ጳውሎስ በሕይወት በነበሩበት ወቅት ወደ ደቡብ አፍሪካ ተመላልሰው ሲታከሙ ለዋሉት ውለታ ሕይወታቸው ከማለፉ በፊት የአፍሪካ አህጉር ሊቀጳጳስ ተብለው በሱዳን፣ በጅቡቲ እና በኬንያ ያሉ አብያተ ክርስቲያናትን እንዲቆጣጠሩና እንዲሾሙ ተደርጓል ያሉት የዘ-ሐበሻ ውስጥ አዋቂዎች የአቡነ ያዕቆብ ዓለማዊ ሥምም መቶ አለቃ አስማማው እንደሚባል ነግረውናል።
የደቡብ አፍሪካው የዘ-ሐበሻ ዘጋቢ እንዳለው የወያኔን ሥርዓት ጥለው በተሰደዱ የደቡብ አፍሪካ ምእመናን ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ በመሄድ የቤተከርስቲያን አንድነት እንዳይሳካ ካደረጉት የሃገር ቤቱ የወያኔ ደጋፊዎች ጋር አብረው መወገናቸው በተለይ በደቡብ አፍሪካ በሚገኘው የጽረ አረአያም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ምእመናን ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን በማስከተሉ ሕዝቡ በአንድ ላይ ተቃውሞውን ለማሰማት ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቋል።
በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ አማኞች በሁለቱ ሲኖዶሶች መካከል ሊደረግ የነበረው እርቀ ሰላም የሃገር ቤቱ ሲኖዶስ ተልከው አሜሪካ የሄዱት ተደራዳሪ አባቶች ሳይመለሱና የ እርቁን ውጤት ሳይሰሙ የመንግስትን ፍላጎት ለማሟላት 6ኛ ፓትርያርክ መምረጣቸው እንዳስቆጣቸው በተለያዩ መንገዶች በመግለጽ ላይ ናቸው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከቤሩት የተሰማ አሰቃቂ መረጃ (ይህን ቪድዮ ከ18 ዓመት በታች የሆኑ እንዲያዩት አይመከርም)

ይህን ጉዳይ ተከታትለን እንደምናቀርብ ከወዲሁ እንገልጻለን።

8 Comments

  1. የመቶ አለቃ ”አስማማው” በማለት ፋንታ የመቶ አለቃ አጣላው ወይም ለያየው ቢባሉ ስማቸው ከግብራቸው ጋር የበለጠ አይስማማም ?

  2. betekirstianin mechawecha kaderegut andu ye derg wetaderoch nachew. enezihin sewoch woyane kemareke behuwala beteleyaye zede papas dires endidersu adrigowal. sewochu minim emnet yelachewum. belebesut kemis wust tesheshigew yemiserut sira lela new. woyanen tekmew rasachew metekem new sirachew. abune yacobim andu new. le wetaderinetu tekawami balihonim gin lehaymanotu minim yemaysera ena emnet yelesh sew bemehonu awegzewalew. le debub africa kerto leand betekirstian enqwa aymetinim.

  3. እውን እንደዚህ የምታደርጉት እና የምታስቡት ወገኖች ክርስትያኖች ናችሁ? ቤተክርስትያናችንን ለፖለቲካ ጥቅማቹ ብላችሁ የምታረክሱዋትን እና አባቶችዋን የምታንጉዋጥጡ ሁሉ መቼም ሁሉን የሚያይ አምላክ የስራቹን እንደሚሰጣችሁ አልጠራጠርም። እባካችሁ ልለምናቹ ቅድስት ቤተክርስትያናችንን ከዚህ ቆሻሻ ፖለቲካችሁ ጋር አትቀላቅሉዋት። ቤተክርስትያን የወንጌል እንጂ የጥላቻ መስበኪያ አትሆንም።
    “ቤቴ ለአሕዛብ ሁሉ የጸሎት ቤት ትባላለች ተብሎ የተጻፈ አይደለምን? እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት አላቸው።” የማርቆስ ወንጌል 11:15

  4. L-Zhabesh-azegage: pls teru zegaby benorh teru newe! Wesht yehone zena atawtu! Gezaw seders abunum semelesu ewnetun teredutalachu! Beterfe pls y-ortodox amagnoch kehonachu L-betekerstyan andenet yemetekem neger betawetu teru newe! Lela sew ketetera zemawem yeun chefary! Kumnegeru lela newe! NESEHA!!!

  5. በመጀመሪያ በ ሳውዝ አፍሪካ የሚገኘው ሰው ምን አይነት ነው ኢስኪ ትን ራሳችን እንመርምር
    1. ሊባ አዘላይ የሰው ገንዘብ የሚዘርፍ ነው 99.9 ሁሉም ስራው መስረቅ ነው
    2. ዘ ሃበሰ የሚለው ደገሞ የ ሊባ ተባባሪ ነው
    3. ጳጳሶቻችን ኣባቶቻችን ለቀቅ አድርጋቹ ራሳቹ እንደ ለመዳቸሁ ተባሉ
    4. በ/ክርስትያናችን ከ ፖለቲካ አትቀላቁላት
    5. አሉ ባልታቹሁን አቁሙ

  6. ere ebakachehue kemenete abatochachene gare atatalune. Meneme yeseru yeserachewene yemikefelewe Amelake becha newe. Legna tekebetewe esketesetune derese abatenetachewene meqebele becha newe. Kezeaya weche ayagebaneme .ebakachehue erefulene.

  7. Hi Ze-Habesha; better to be called (Ze-Banda). Do you think that even Weyane itself is as evil as you? First of all; please try to use appropriate wording and letters before you post as a News. The next step could be to know and ask yourself, “Is the information that I am broadcasting polluting or helping?”. Everybody knows that having blog or website is as simple as anything. However, Religion, specially and most specially OrthodoxTewahedo is really sacred that people with dirty mouths like yours, the editor of this blog, and the government authorities could not be entitled to talk about or even comment. To do so please stand first for the benefit of the religion and the religious affiliates of the church; not for your politics (which means LIE, trust me).

    Please refrain to talk about our church and the fathers and even its members. Your political dirty game could be played in the available dirty fields.

    HULUN BINAGERUT HOD BADDO YIKERAL.

Comments are closed.

Share