በይዘቱ ወቅታዊ የቴሌ-ኮንፍረንስ ስብሰባ ግብዣ

ጋባዥ፥ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት የሰሜን አሜሪካ ግብረ ኃይል
ተጋባዥ፥ ኢትዮጵያውያን ሚዲያዎች በሙሉ

 

በስብሰባው ላይ የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች፥

 

1) የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ – የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀመንበር እና የፓርላም አባል.
2) ስቶ በላይ በፍቀዱ – የአንድነት ፓርቲ ላዕላይ ምክር ቤት አባል , የፍኖተ ነፃነት ኢዲቶሪያል ቦርድ ሰብሳቢ እና  የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ግብረ ኃይል ዋና አስተባባሪ

 

በኢትዮጵያችን በአገር አቀፍ ደረጃ በመካሄድ ላይ በሚገኘው የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ እእንዲሁም በቀጣዩ የነፃነት እና የዴሞክራሲ ትግላችን ላይ እነዚኽ የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ባልደረቦች በቴሌ-ኮንፍረንስ ከኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት ስለሚያደርጉ የውይይቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ የሰሜን አሜሪካ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ ግብረ ኃይል በአክብሮት ጋብዞዎታል። የአንድነት ፓርቲ መሪዎችን ጥያቄዎች መጠየቅ ይችላሉ።

 

በዚኽ ቴሌ-ኮንፍረንስ ከተጋበዙት ሚዲያዎች ውስጥ ጥቂቶቹ፥

 

1) ፓልቶክ ሚዲያዎች፥ ቃሌ፣ ሲቪሊቲ እና ከረንት አፌር
2) ሪዲዮ እና ቴሌቪዥን ስርጭቶች፥ የአሜሪካ ድምጽ (አማርኛ፣ ትግሪኛ እና ኦሮምኛ ፕሮግራሞች)፣ ኢሳት ቴሌቪዥን እና ሬዲዮ፣ የጀርመን ሬዲዮ ጣቢያ፣ የዲሲ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ሬዲዮኖች በሰሜን አሜሪካ በሙሉ
3) ድረገጾች፥ ዘሐበሻ፣ ኢትዮሚዲያ፣ ኢትዮሚዲያ ፎረም፣ አቦጊዳ፣ ኢትዮሪቪው፣ አውራምባ ታይምስ፣ ኢካድ ፎረም እና ሌሎች

 

ቴሌ-ኮንፍረንሱ የሚደረገበት ቀን እና ሰዓት፥

  • ቀን፥ ቅዳሜ ነሐሴ 25 ቀን 2005 ዓ.ም. (Saturday, August 31, 2013) – ከሁለት ቀኖች በኋል!

  •  ሰዓት፥ ከቀኑ 1፡00 ሰዓት (1:00 PM Estern Time)

  • በቴሌ-ኮንፍረንሱ ለመሳተፍ፥ (267) 507-0240 ይደውሉ እና 20-18-20 ኮድ ይጠቀሙ

 

ውድ የድረገጾች አስተናጋጆች፥

የጊዜ እጥረት እየተፈታተነን ነው። ስለዚኽ ይኽን ጥሪ በድረገጾቻችሁ ላይ በማውጣት የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ወገናችን ሁሉ ስለቴሌ-ኮንፍረንሱ እንዲያውቅ እንድታደርጉልን በአክብሮት ትብብራችሁን እንጠይቃለን። ለቴሌ-ኮንፍረንሱ ሁለት ቀኖች ብቻ ስለቀሩን ጥሪው እንደደረሳችሁ በድረገጾቻችሁ እንደምታሰፍሩልን ተስፋ እናደርጋለን።

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  ቴድሮስ አድኃኖም ለቀጣይ ዙር ብቸኛ ተወዳዳሪ ብቸኛ እጩ የዓለም ጤና ድርጅት በመግለጫው ዐስታውቋል

እስከዚያ በአክብሮት መልካሙን እንመኛለን!

Share