የለሊት ወፍን ማን ገደላት? – (ከደራሲና ገጣሚ መኳንንት ታዬ)

ሚኒሶታ

በአንድ ወቅት  የምድር አራዊትና የሰማይ አእዋፋት  ወገን ለወገንህ ተባባሉና  ሁሉም ከእያሉበት  ተጠራርተው  ሲያበቁ  በአንድ ችግር ላይ መወያት  ጀመሩ። ይኸውም በአራዊቱ  እና በአኢዋፍቱ ዘንድ ችግር እንዳለና  እራሳቸውንም  ማስከበር እንዳለባቸው ይመክሩ ጀመር ። በአእዋፋቱ ዘንድም አራዊቱ ዘንድ ችግር እንዳለ እና ደኑን ተማምነው  ያልተገባ ነገር እያደረጉ እንደሆነ እንደሚጠራጠሩ ለዚህ ደሞ መፍትሄው  ጦርነት ብቻ እንደሆነ  እየተነጋገሩ እያሉ የለሊት ወፍ መጣች። ሁሉም በድንጋጤ  ቢያያትም ቅሉ የማን ወገን ናት  በሚል መልኩ እርስ በእርሳቸው ቢተያዩም  ደፍሮ ግን  ሊጠይቃት የወደደ ግን ስላልነበር  እርሷም የማንነቷን  ገልፃ አልተናገረችም። ብቻ ግን አንድ ነገር አስባለች፤ ጦርነቱ ሲጀመር  ብዙም  ወደሰማይ ከፍ ሳትል  ብዙም  ወደ መሬት  ሳትቀርብ  በረራዋን ለማድረግ።

ይሁን እና  በዚህ መሃል ጉባዬው ጋር ለመገኘት የረፈደባቸው ይቅርታ እየጠየቁና ያጋጣማቸውን እየነገሩ ተቀላቀሉ። የእለቱ ፀሃይ በጣም የሚያቃጥል  ቢሆንም  ከህልውና የሚበልጥ የለም በሚል ይመስላል  በሁለቱም ወገን  ምክከሩ  የአሰላለፍ አካሄዱ የ እለቱን  ውሎ በሚመለከት ተነጋገሩ። ከአእዋፍ ወገን ፤ እነ- እርግብ ፤ እነ-ንስር  ፤እነ -ጥንብ አንሳ  እነ- አሞራ ብቻ  ሁሉም ከያሉበት ተጠራርተው የመገናኘታቸውን ያህልም ፤ ጦሩን ማን ይምራ የሚለውም ነገር  ብዙ ካነታረካቸው በሓላ፤ በስተመጨረሻ ንስር የጦሩ መሪ ሊሆን ተማምለው ባሉበት  ሠኦት ፤ የለሊት ወፍ  ፈንጠር ብላ ተቀምጣ ነበርና ፤”አንቺ የማን ወገን ነሽ?ሲል ንስር በቁጣ ቃል ጥያቄ አቀረበላት። እርሷም ፈጠን ብላ “ምን ጥያቄ አለው  ክንፌን ስታይ የማን እመስልሃለው ብላ ጥያቄውን በጥያቄ መለሰችለት። በዚህ ሁኔታ እያሉ የአራዊቱን አሰላለፍ ማን ይሰልል እያሉ አእዋፋቱ ሲነጋገሩ ይህቺው የለሊት ወፍ “እኔ ብሄድስ? ምክንያቱም  ጡት ስላለኝ  አጥቢ ናት  እና ከእኛ ወገን  ነች ብለው  ስለሚያስቡ ያለውን ነገር ሁሉ በሚገባ አጤነዋለው” ብላ እንደጨረሰች  የሁሉም  ሃሳብ አንድ ሆነና  የለሊት ወፍ ተላከች።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አሸባሪዉ ኢህአዴግና የፀረሽብር ህጉ መወገድ አለባቸዉ

እዛም እንደደረሠች  አራዊቱ በመልክ በመልክ ተሰብስበው ይወያያሉ። ሁሉም አሉ፤ አንበሳ ፤ ነብር አያጅቦ፤ ተኩላ  እነ ዝሆን  ብቻ አራዊቱ ወገን የቀረም የለ። ይሁንና በውይይታቸው መሃል እንዳሉ የለሊት ወፍ  ደረሰች ። ሁሉም አፈጠጡ፤ አንበሳ ነበርና  የጦሩ አበጋዝ “ምን ፈለግሽ?’’ ሲል አፈጠጠባት። የለሊት ወፍም  ምንም እንዳልተፈጠረ በመቁጠር ለማርፈዷ ይቅርታ ጠይቃ  ለመቀላቀል ስትሞክር አንበሳ ጠንከር ባለ ንግግር “የማን ወገን ነሽ?” ሲል አፈጠጠባት። የለሊት ወፍም ፈጠን ብላ ምን ጥያቄ አለው !

ከአራዊቱ ወገን ለመሆኔ ጡቴን ማየት ብቻ አየበቃም? ስትል በማፍጠጥ በመመለሷ ሁሉም በይሁንታ ተቀብሉዋት።  ስለሚያደርጉት ጦርነት እና  የቦታ አያያዝ ብሎም ማን ፊት አውራሪ  እንደሚሆን እና  ማን ጦር መሳሪያ  አቀባይ  እንደሚሆን  ፕላኑን  አውጥተው ከጨረሱ በሓላ ፤ አንበሳ ወደ ለሊት ወፍ ዞር ብሎ ፡አጅሪት እስቲ ሂጅና ያለውን ነገር ሰልለሽ ያላቸውን ሃይልና እና  የታጠቁትን የጦር መሳሪያ አይነቱን ንገሪን አላት። መላኩ  ያስደሰታት የለሊት ወፍ  ስትበር ሄዳ ‘የአራዊቱን አቅም ምን ያህል ደካማና በአሰላለፍም ከኣኢዋፍቱ  እንደማይበልጡ አፏን እያጣፈጠች  ነገረቻቸው። በሁኔታው የተደሰቱት አእዋፍቱም  በፍጥነት ጦርነቱን ቢጀምሩ አራዊቱ ካለቸው ብቃት ማነስ ጋር ተጨምሮ በድንጋጤ ሊረበደበዱ እንደሚችሉ ነግራ ፤ ለመጀመር እየተዘጋጁ ባሉበት ሰዐት ለፊት አውራሪው ንስር ጠጋ ብላ “ምንም እንኳን ሁኔታው ባይመችም ቅሉ ጦርነቱ ባሸናፊነት እንዲወጡ እርሷ  ለአስር ደቂቃ  ፀሎት አድርጋ መምጣት እንደምትፈልግ አሳምናው በራ  ወደ አራዊቱ ዘንድ በመሄድ ለእነኛ የነገረቻቸውን  ሁሉ ለእነዚህም  ነግራ ጦርነቱን አስጀመረች። በሁለቱም ወገን ከባድ ውጊያ ሆነ። የለሊት ወፍም ከፍ ብላ በበረረች ግዜ ኣኢዋፍቱን በርቱ እንጂ መጠቃታችን ነው ስትል ዝቅ ብላ አራዊቱን በርቱ እንጂ መጠቃታችን ነው፤ እያለች ቀኑን ስታዋጋ ዋለች። ከሁለቱም በኩል በጣም ብዙ ሰራዊት ወደቀ። ሬሳ በሬሳ ላይ ተደራረበ። የሚገርመው በእለቱ ከሁለቱም ወገን የጦርነቱ ሚስጠር ያልገባቸው እንዲሁ በየወገንህ ሲባል ብቻ ሰምተው የተሰለፉም ነበሩበት። ባላወቁትም  የሞት ሰለባ ሆኑ። ግና በዚህ ሁሉ ምሀል ስትሽሎኮለክ  የነበረችው የለሊት ወፍ  የምታደርገውን ንስር ከሩቅ ሆኖ ይመለከት ነበርና ሳታስበው አደጋ ጥሎ ከሙታን ጋር ቀላለቀላት።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደርግ አልነበረችም፤ የወያኔም አይደለችም፤ የቅንጅትም አትሆንም

በዚህ ሁሉ መሃል አንበሳ በድንገት  ዞር ብሎ ቢያይ   የለሊት ወፍ  የለችም። ከሓላው ይከተለው ለነበረው ወታደር በቁጣ “የለሊት ወፍ የታለች ?” ብሎ ጠየቀው። ወታደሩም ፈጠን ብሎ ከንስር በተጣለ ቦንብ ስትጋይ አይቻታለሁ አለ።” ለነገሩ እኔም ላጋያት ነበር የፈለኳት ብሎ ጦርነቱ እየመራ ቀጠለ። በዚህ ሁኔታ ሆዱን መሸከም ያቃተው አያ ጅቦ ከሞቱት ወገኖች መሃል የሞተውን  (እርሙን) ሊበላ ወደሓላ ቀረ። ከአእዋፍቱም ወገን እንዲሁ እነ ጥንብ አንሳ ሆን ብሎ እጁን በመስጠት ከተማረከ በሓላ የሞተውን መብላት ጀመረ። በስተመጨረሻ ጦርነቱን የሰሙት  የቤት  እንሰሳት  በገላጋይነት በመግባት “ለሊቱን  ለአራዊት  ቀኑን  ለአእዋፋት” ብሎ አምላካችሁ ከፍሎ ሰጥቶአችሁ እያለ ውጊያው ምንን በተመለከተ ነው? ሲሉ በዝርዘር የውጊያው አላስፈላጊነት አስረዱአቸው። በሆነውም ከልብ እንዳዙኑ ገልፀው ሁሉን አሳምነው ሲያበቁ በጦርነቱ ወቅት ችግር ፈጣሪ እና ታማኝታቸውን በአቅም ማጣት ምክንያት  እና በመምሰል ለመሆን  የሞከሩትን ጦር ወንወጀለኞች፤ እንደ ለሊት ወፍ ያለው  ከሁለቱም ወገን እንዳትገባ፤ ጥንብ አንሳና ጅብ ዜግነታቸው ተነጥቆ በቁም አስር እንዲቆዩ ተወስኖ፤ ከእንግዲህ የሰላም አገር መስርተው ሊኖሩና የጋራ ጠላታቸውን በጋራ  እንደሚከላከሉ ተስማምተው ሊስታርቋቸው የመጡትንም አመስገኑ::

በስተመጨረሻም ለአስታሪቀነት ከመጡት አንዷ እመት በግ ተነስታ “እስቲ የጦርነቱን መንስሄ ከሁለቱም ወገን ብታስረ ዱን“ ስትል ሁሉንም አይን አይናቸውን እያየች ጠየቀች። በሁለቱም ወገን ይሄ ነው ብሎ ምክንያት የሚሰጣት በመጥፋቱ አፍረው አንገታቸውን በደፉበት ግዜ አሞራ ከሩቅ ሆኖ”መሳሪያ ሻጮች ናቸው የሚያጣሉን” ሲል ሁሉም በምክንያቱ ተገርመው ሳቁ። በግም በነገሩ ተገርማ  ስታበቃ ”ይገርማል የሚያፈስ ጣራ ያላት ሃገር ይዘን ብዙ ግዜ የምንጣላው ለአጥር በሚሆን እንጨት በሚደረገው  ፍለጋ ስለሆነ ነው። ነገር ግን መጀመሪያ መቅደም የነበረበት ጣራን መሸፈን ነው ወይስ አጥር? ብላ ሁሉንም አፍጣ ጠየቀች። ሁሉም በአንድነት አሱማ ጣራ ይቀድማል አሉ። አዎ አንዲህ ስላችሁ አጥር አትጠሩ ማለቴ ሳይሆን ከጦርነት በፊት ለምን የሚል ቃልና ትርፉስ የሚለውን አስተሳሰብ አትርሱ። በማለት የእለቱን የማስታረቂያ ንግግር ስታደርግ ሁሉም ተመስጠው በመስማት አድንቀው ሲያበቁ ከዚህ በሓላ ስለሁሉም በማሰብ ስልጣኔን አየር እየዛቁ ለሃገር ለወገን በሚሆን ነገር ላይ በማተኮር ዘመናቸውን እንደሚኖሩ ተነጋግረው  ተሳስመው ተለያዩ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አፍንጫህን ላስ - አቶ ሂደት።

ቸር እንሰብትS

 

2 Comments

  1. ደራሲና ገጠሚ መኳንንት ታዬ, ዛዲያስ የለሊት ወፉ ማነው ትላላህ, አፃፃፍህ ስለ ደብረ ሰላም ቤተ ክርስቲያን ስለመሰለኝ ነው, አንተስ ጎራህን በግልጽ ያለየህ የለሊት ወፏን አይደለህምን????? ካልሆንክ አሰየው ነው

  2. መልካም ልጅ መኳንንት። አዎን የሚያጨቃጭቀን የአንድነት ጠር የሆነው የቤተክርስቲያንና የኢትዮጵያ ጠላት ወያኔ ነው። ነገሩ ባልገባቸው ወንድሞችና የዋሐን እህቶች በኩል እርሱ የፈጠረውን ችግር እኛ ያመጣነው ይመስል ለምን ገለልተኛ ሆናችሁ ለምን እኔ የሾምኩትን አትቀበሉም እያለ ቢዘገይ የተረሳ መስሎት አንድነትን ለመከፋፈል ያመጣብን ደባ ነው-ጦርነቱ። መጀመሪያ ጣሪያ/አንድነታችን /ይቀድማል። ከላይ ለተፈጠረው መከፋፈልና መወጋገዝ ሳንወግን ታረቁ ማለታችን ፍጹም ክርስትና ነው። እንዳይታረቁም የሰላምንና የእርቅን ሂደት ያጨናገፈው ራሱ ወያኔና አገልጋዩ የሆኑ አንዳንድ’ጳጳሳት’ተብዬዎች ናቸው። ለማንኛውም የኛዋ ደብረሰላም በአምላክ ፈቃድ አትናወጥም። እኛ የማትያስም አይደለን የመርቆርዮስም አይደለን የከርስቶስ ነን። በቤተክርስቲያናችን ሥርዓት ደግሞ በአንድ ጊዜ ሁለት ፓትርያርክ ሊኖር ስለማይችል ወይ ታርቀው አለበለዚያም በሆነው መንገድ አንድ ሆነው ስናገኝ የአንዱን ስም እንጠራለን። ከዚያ በፊት ግን ከወንጌል አላማ ወይ ፍንክች! በማያውቁት መፍረድ፣መወገን፣መደለል፣ሌላው ቀርቶ የዋህ ብቻም መሆን ከፍርድ አያድንም። የዋሃንም እንደ እባብም ልባም መሆን ይገባቸዋል አልያ የዋህነት ብቻውን ቂልነት ወይንም አለማወቅ ብቻ ከሆነ አያድንምና። ለነገሩ የዚህ የመለያየት አላማ ዋነኞቹ አቀንቃኞች የግል ግትርነት ጠባይና ውዳሴ ከንቱ -እነገሌ ታግለው ይህንና ያን አደረጉ ለመባል ካልሆነ በስተቀር መጀመሪያ ችግሩ ሲፈጠር የነበረው ሁኔታ ምንም እንዳልተለወጠ ያውቁታል። እናም በኃይማኖት አንዴ እዚህ አንዴ እዚያ የለም! ጸንቶ መቆም ብቻ ነው። ያን ጊዜ ኃያሉ ጌታ መልስ ይሰጣል። ልክ ለዋልድባ መነኮሳት ፈጣን መልስ እንደሰጠ። ሁለቱንም በአንድ ሳምንት። አሁን ለፈጣሪ የቸገረው በጽሑፉ ውስጥ እደተጠቀሰው የሌሊት ወፍ መብዛቱ ነው። ስለዚህም ምህረቱን አዘገየ። ሲዘገይ ደግሞ ወደ እውነት ከመመለስ ይልቅ እከመቼ የሚል ፈሊጥ ይዞ ባንዳ እንሁን ተባለ። ይህ ደግሞ ለሰውም ህሊና ለፈጣሪም አይመችም። ስለዚህ አንቀበለውም። አንተስ ከየት ወገን ነህ ወዳጄ???

Comments are closed.

Share