ዲያቆን ዳንኤል ክብረት መምህር ግርማን ያተኮረ እና የሚያመሰጥር እይታው የተፃፈ መልስ

ክፍል አንድ

እርግጠኛ ነኝ ይህ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የፃፈው በይበልጥ ለመምህር ግርማ መፃፉን እገነዘባለሁ። ይህ የመልስ ጽሁፍ ብዙ ሐሳዊያን ስላሉ ፣ባህታዊያን ነን ብለው ብዙ ችግር የሚፈጥሩትን የሚያታልሉትን በድጋፍ መልክ አይወክልም ። ወንድማችን በሐሳብህ እነሱን ብለህ ከሆነ በጣም ጥሩ ነው ጥሩ ብለሐል በርታ … ነገር ግን እንደምረዳውም እሳቸውን መምህር ግርማ የሚያጠቁም መሆኑን ስለተረዳሁ ይህን ጽፌልሀለሁ :: ይህ ጽሁፍ ስለ መምህር ግርማ እና በንጹ መንፈስ ለሚያገለግሉ ሁሉ ነው
ለእይታዎችህ በየተራ ቁጥሩ መልስ ለመስጠት ያህል :-

ቁ1/ A/ መምህርን እንድታውቃቸው ያህልትንሽ ልንገርህ ብዙዎቻችን አንተም ሳትወለድ በፊት
A.1/ መምህር ግርማ ዲያቆን ሆነው ለረጅም አመታት በባሌ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በምግባር በታዛዝነት በጽናት እግዚአብሔርንና ቤተክርስቲያንን ምእመንን አገልግለዋል
A.2/ እንደማንኛውም ሰባኪ ለዘመናት ከዲቁና ጀምሮ እግዚአብሔር እንደገለጠላቸው ህዝበ ክርስቲያናችንን በመንፈሳዊ ስብከት በዚያን ግዜ ጅምሮ አገልግለው ። ፍሬው ያማረ ከብዙሺህ የሚቆጠር ምእመንን ለንስሐና ለቅዱስ ቁርባን አብቅተዋል፣ ክርስቶስን እንዲያውቁ አርገዋል ፣ሕዝቡ የቤተክርስቲያን ሀብት እንዲሆን አርገዋል።
A.3/ ሌላው ልነግርህ የምፈልገው ነገር አንተ አቡነ ጎርጎሪዩስን ሳታውቃቸው በፊት ከብዙ አመታት በፊት መምህር ግርማ የአቡነ ጎርጎሪዩስ በፍቅር ተወዳጅ ተማሪ እንደነበሩ እወቅ። በጣም የሚዋደዱ አባትና ልጅ እንደነበሩ ለእውቀት ያህል እንድትረዳ እፈልጋለሁ። ማለት ምኑንም ሳትጀምሩት መምህር ግርማ የመንፈሳዊ ትምህርትና የጸሎት ብርታ እንደነበራቸው ከአቡነ ጎርጎሪዩስ ጋር የጠነከረ የጠራ የአባትና ልጅ የፍቅር እንደነበራቸው ተረዳ።

ተቺና፣ነቃፊ ስላልሆኑ፣ተንኮል ስለሌላቸው፣በድብቅ ሌላውን ለመጉዳት የማይጠነስሱ ስለሆነ እሳቸው ፍቅር ስላላቸው በጎነታቸውን ስላየ መንፈሳዊ ጉዛቸውን ክርስቶስ ስለወደደው እሱ አብዝቶ ሰጣቸው
እርግጠኛ ነኝ ይህ ሁሉ አልታየህም ያየህው በምን አይን እንደሆነ አልገባኝም

B/ የጸሎት ሕይወት ላልከው መንፈስህ ከፈቀደልህ ጠጋ ብለህ ጠይቃቸው እያቸው ። እግዚአብሔር እረድቶአቸው ምን ያህል በጸሎቱ ህይወት እንደረዳቸው ግንዛቤ ታገኝ ይሆናል
C/ ሌላው ነገር ወገንህ ምን ያህል በእርኩስ መንፈስ እንደተወጠረ የገባህ አይመስለኝም። መሰበኩን ብዙ ትናገራለህ እንጂ የልቡን ጭንቀት ለማየት የተጠጋህ እንካን አልመሰለኝም። አንተ እንዳልከው ማጥመቅ ስራው የሆነ የለም ብለሃል ይህ ያንተ አባባል ነው ። እግዚአብሔር ከተያዘውና ካለቀው ትውልድ አንፃር እንዲያገለግሉ ከወደደላቸው አንተ ምን አስቀናህ አገባህ ።
ክርስቶስ ልጆቹ ይድኑ ዘንድ ፍላጎቱ ነው ። እውነት እልሃለሁ በኔ እይታ ደግሞ አንተ ያልከው የመዳንን በር የሚዘጋ አባባል ነው ፣ ትውልድ በሰይጣን ተጨንቆ ይኑር ብዙ ግልፅ የሆነ ጥምቀትና መናፍስትን ማስወጣት ጥሩ አይደለም ይበቃል የሚል አባባል ያዘለ ይመስላል::

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሄኖክ የሺጥላ - (አምቦ ተነሽ አትነሺ)

D/ የመንፈስ ቅዱስን አሰራር ከመረጃ ፍለጋ ልታገኘው አትችልም በፍጹም ልትደርስበት አትችልም ካልተፈቀደልህ
E/ ላንተ ጥያቄ … ክርስቶስ ሲመርጣቸውና ሲያድርባቸው ላንተና አልገባ ላላቸው መንገር ነበረበት እንዴ??
አንተን መጠየቅ ነበረበት ወይ?? ይህን በእውነት ከመለስከው ግራ ሊያጋባ ለፃፍከው ነግር ብዙው መልስ ይሆንሃል

ቁ2/ A/ ሌላው ነገር ለምሳሌ አንተ ….. ከመምጣትህ በፊት ዳንኤል ክብረት ሊመጣ ነው ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ተብሎ ከወር በላይ አይደል እንዴ ጥሪውና ዝግጅቱ … ምን አለበት ታዲያ መምህርም በተሰጣቸው ጸጋ የወንጌልና የፈውስ ግልጋሎት ማዘጋጀቱ ምኑጋር ነው ችግሩ? ባይሆን ጥላቻ ካልሆነ
B/አንድ ነገር ልንገርህ ክብሬ ይገለጣል ብለህ ከምትሸሽ ። ተገልጠህ ነፍሳትን ማዳን ወደ ክርስቶስ ማምጣት እንደሚበልጥ እርግጠኛ ሆኜ እነግርሃለሁ።
C/ ሌላው ስለሌሎች ክብር መገለጥ መጨነቅህና ስብከትህ በዚያ ዙሪያ ማጥፋትህ ጥሩ አይደለም ። ያአንድ ግለሰብ መምህር ራሳቸውን ጠንቅቀው ከክርስቶስ ጋር ስለሚያውቁ ብዙ አትድከም። በቅድስና ላይ ብታተኩር ይሻላል
D/ ስለመሸጥ ተናግረሃል .. ልጠይቅህ ጥንት አባቶቻችን መጸሐፍ መሸጥ የሚባል ነገር አልነበረም ። አንተ ወይም ሌሎች ለምን መጸሃፍ ትሸጣላቹሁ? ይህን ከመለስክ መምህር ለምን እንደሚሸጡ መለስክልን ማለት ነው።
E/ብዙ ነገሮችህ ቅዱሳኖችን እየጠራህ እነሱ እንዲ አያረጉም ነበር እነዚህ ግን እንዲህ ነው ትላለህ ። አሁንም ልጠይቅህ … የድሮዎቹ ሰባኪ ለአገልግሎታቸው ብር አይቀበሉም ነበር ። ልምንድነው አንተም ሌሎችም ግን የግልጋሎት ዋጋ በብር ይሰጣቹሃል ለምን ይመስልሃል? … ይህን ከመለስክ መምህር ለምን እንደሚሸጡ መለስክልን ማለት ነው። በተጨማሪ ላሳውቅህ የምፈልገው መምህር ሁሉ ጋር በነፃ በፍቅር ነው የሚያገለግሉት ሰዎች አስገድደው ዋጋ ካልተቀበሉ ብለው ያስገድዳሉ እንጂ

ቁ3/ በኢየሱስ አልወጣም በማሪያም ነው ብለሃልይህ? እዚህ ጋር እንደመናፍቅነት እይታህ የጎላ ነው ። ይህ በስህተት እይታ ያየ ፣ የሰይጣንን ቃል ሰምተህ እንጂ መምህር ጋር እንዲህ አይደለም ። እይታህ ለመንቀፍ ችኩል እንደሆነ እረዳለሁ።
አጋንንት በሚካኤል ስም ቢወጣ ። የክርስቶስን ክብር ዝቅ ማረግ አይደለም ።በሚካኤል ስም ቢወጣ የጌታ ፈቃዱ ሆኖ መሆኑን ዘንግተሃል። በየትኛው አይን እና ህሊና እንዳየህው እራስህን ጠይቅ?
ቁ4/አንተ በመቁጠሪያ ይወጣል ይላሉ ብለሃል:: እይታህ በጣም መሳሳቱን እይ ። እሳቸው እንዲህ አላሉም ከሄዱበት መንፈሳዊ መንገድና ጉዞ አንፃር የተደበቀ መናፍስትን በክርስቶስ ስም ማድከሚያ የእኛ ጦር መሳሪያ ነው። አሁንም ላይገባህ ይችላል ግን ምን ማረግ ይቻላል ለብዙዎች ግን ጦር መሳሪያችን ነው እወቀው።
ቁ5/ያ ግዜና ይህ አንድ አይደለም ለምሳሌ በዚያ ግዜ ከ200 ሰው 1 ስው በመናፍስት የተጎዳ ነበር አሁን ግን ከ200 ሰው በትንሹ 190 ሰው የተጠቃ ነው።
ሌላው ደግሞ መተተኞቹና አስማተኞቹ በጣም በዝተው ። ትውልዱን ከዲያብሎስ ጋር አንድ ሆነው በስውር የጨረሱበት ዘመን ነው ።ሰይጣንን ለአላማቸው ጠርተው ሂድ ይህን አድርግልኝ የሚሉ ብዙ እንዳሉ እኔ ላንተ አልነግርህም ። አይ አላውቅም ውሸት ነው ካልክ የቆሎ ተማሪ የሆነን ሰው በተወለድክበት ቦታ ጠይቃቸው በጣም ብዙ ይነግሩሃል።
አንተ እንዳልከው ይህ የሰይጣንን ኃይል የሚያሳይ ነው ብለሃል ። እየውልህ እይታህ በተሳሳተ መንገድ መቆሙን አየን ።የእኛ እይታ ደግሞ ደግሞ የሰይጣን ደካማና አልቃሻ ነቱን በክርስቶስ እንዴት እንደሚባረር ተረዳን መምህር ግርማ አስተማሩን ።
ይህ ሁሉ ሰው በሰይጣን ሲያዝ ክርስቶስ የለምን ጥምቀቱና ቁርባኑ አይሰራምን ብለህ ጠይቀሃል
ጥያቄ ላንተና የተመሳሰለ ሃሳብ ላላቸው
በመፃህፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙዎች ተይዘው የተጎዱ አሉ ። ለምን ይመስልሃል ሲያዙ ዝም የተባለው? ይህን ከመለስክ አሁንም መልሱን አግኝተሃል።
ክርስቶስ ነፃነት ሰጥቶናል ግን በራሱ እጅ ሰው ይያዛል። ጥምቀቱና ቅዱስ ቁርባል ታላቅ የክርስቶስ ልጅነትና ኃይልን አሲዞን ነበር ነገር ግን በራስ እጅ የዲያብሎስ እጅ ውስጥ እየገባን እንጂ
ቁ6/ክፉ የሚሰሩ ሰዎች ይጋለጡ ዘንድ ለነሱና ለዲያብሎስ አጋዝ የሆነ አስተያየት መሆኑን እገነዘባለሁ። ሰይጣን ውሸታም ነው ። የክፉዎች መረብ የመታቾች ተንኮል የነቃና ይፈርስ ዘንድ የማይፈቅድ ጥንቃቄ ያለበት አባባል ይመስላል
ቁ7/መምህር ግርማ ይህ ቅድስና ነው አላሉም ። ለክርስቶስ መንጋ እንዲያገለግሉ ክርስቶስ ሾማቸው እንጂ። በክርስቶስ ሹመት አንተ ምንም አያገባህም ። ብትችል ከበረከታቸው ተካፈል እንጂ እንዲህ ነው እንዲህ ነው ልትል አቅሙም ስልጣኑም የለህም ። ገዳምም ይሁን ከተማ በክርስቶስ ምርጫና አሰራር የሚያገባህ አይመስለኝም።
ቁ8/አንተ የወደፊቱን አሳች እያሰብክ እየፈራህ ዛሬ ክርስቶስ የመረጣቸው የጠራቸውን መምህር ግርማን ወቃሽና አዋራጅ ለመሆን ምክንያት ትደረድራለህ ። ከሩቅ ሆነህ መረጃ ሰብስበህ ያወሩልህን እውነት ብለህ ከምትነዛ ቀረብ ብለህ ትምህርታቸውን ተማር በጣም ብዙ ትምህርት ታገኝበትና እይታህ ይቃናል የክርስቶስ ሐዋሪያ መሆናቸውን ትረዳለህ። ለዚህ እድል ክርስቶስ ይርዳህ።
ቁ10/ ከክርስቶስ ይልቅ መምህር ግርማ አልጎሉል አልከበሩም ይህ እይታህ እዚህ ጋር እንደመናፍቅነት እይታህ የጎላ ነው ። በመምህር ግርማ ስብከትና ፈውስ ክርስቶስ ከበረ ክርስቶስ ሰራ እንጂ እኔ ያሉበት ቦታ አላየሁም ።ሌሎች ሌላ ነገር ብለውክ ይሆናል በራስህ ቀርበህ ከማየት ይልቅ።
በአጠቃላይ በመምህር ግርማ ዙሪያ ላወጣህው ድብቅ ገላጭ ጽሁፍ ወንድማችን እይታህ እንደተሳሳተ እነግርሃለሁ ሕዝቡም አይቶት ይመሰክራል
ሁሉ ሰው እንደ እምነቱና እንደገባው መጠን መርከስም መቀደስም ተፈቅዳል ስለዚህ መቀበልም አለመቀበልም እንደዚሁ ። እኔ ለምን መምህር ግርማን አልተቀበላቹሁም አይደለም ነገር ግን
ልክ ለሌላው ሊድን ሲል ከሰይጣን ሰንሰለት ሊላቀቅ ሲል ግን ብዙዎች አወቅንልህ ብለው የሚከለክል የዲያብሎስን ያህል ምክር ይመክራሉ … ሰውየው ግን ተይዞ ለዘመናት ሲያነደው ማንም ትንፍሽ ያላለ …. የመዳኛው ሰአት ሲደርስ ግን … ሁሉ የሞት ሽረት ላንተ ጠበቃ ሆኖ ሲከለክልህ ግራ ሲያጋባህ ይታያል ። ይህም ያስጠይቅሀል….
“ሉቃ 11፥52
እናንተ ሕግ አዋቂዎች፥ የእውቀትን መክፈቻ ስለ ወሰዳችሁ፥ ወዮላችሁ ራሳችሁ አልገባችሁም የሚገቡትንም ከለከላችሁ”
የሌላውን ሰይጣን ያሰረበትን ሰንሰለት እንዳይበጠስ ወደ መዳን የሚገቡትን ከልካይ ሆነህ መቀመጥህን አስተውል
አስተውል ልኡል እግዚአብሔርን ዝም ብለህ ተቃዋሚ ሆነህ መቆምህን እንድትረዳ ልብህን መርምረው። አንተ ክፍ ትውልድ ልኡል እግዚአብሔር ያነሳውን ባለሞል ልታሰናክል እንደማትችል እነግርሀለሁ ።ባይሆን በምኞትህ እንደምትወድቅ የጌታ መለኮታዊ ቃሉ ይነግረናል:: ከመደፋፈርህ በፊት አስተውል ከቻልክ ቅዱስ መንፈስ ካለብህ በፀሎት ጌታን ለምን!!
እግዚአብሔር መምህር ግርማን ሀይሉን ፍቅሩን ለመንጋው የገለጠባቸው የሚገልጥባቸው ታማኝ ባለሟል ከሆኑት ውስጥ ስለሆኑ ።(ይህንንም ስል በሌሎች በጣም ብዙ አባቶቻችን ገልፃል ይገልፃልም ማለቴም ነው)እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በሳቸው በኩል ስለሚገስፀን የጌታን ቃል እንማራለን እናድጋለን ። ግን ሌሎች በቅናት ልቦና ቆመው ሆይ ሆይ እንደሚሉት “አድናቂና ዝምብሎ ተከታይ ቲፎዞ ግን አይደለንም”

ተጨማሪ ያንብቡ:  ፈንድ ፈንዳጅ ዲያስጶራ እባክህ ስማ! ለዘራፊዎች የማይነጥፍ ጥገት መሆንህ ይብቃ!

መንፈሳዊ ወገኖቼ አምላካችን ክርስቶስ በባለሞሉ በመምህር ግርማ በኩል ሊያሳስበን የፈለገውን መንፈሳዊ ንቃት ያስተዋላቹሁ ። አይዛቹሁ በርቱ አብዝቶ ይግለፅልን በሀይማኖት ምግባር ፍቅር እምነት በርቱ ”ፊሊጽሲዮስ 1፥ 28-29 በአንድም ነገር እንኳ በተቃዋሚዎች አትደንግጡ” ሳያውቁ ግራ ለተጋቡብን ወገኖቻችንም በፀሎታቹሁ አሳስቡላቸው ወደማስተዋል ህሊና እንዲኖሩ

በወደደን በክርስቶስ እንሻገራለን!!

በክፍል ሁለት እንገናኝ!

ከኢያሱ ሚካኤል

25 Comments

  1. አባ ግርማ አላችሁ!!!!ኦርቶዶስ ከውስጥም ከውጪም ዘመቻ እየተደረገበት ነው::ዘማቻው ለበጎ አይደለም::ከመሠረቱ እንዲናድ ጥረት ነው::ምዕመናኑ የእምነቱ አስተምሮት የላላ ነው::ይህ ከጨቅላ እድሚው የጀመረ ነው::የመድሐኒ ዓለም እምነቱ በትምህርት ላይ ታንጾ የጠነከረ ቢሆን ለተራ የዘመኑ ጋኒን ጎታች ቀርቶ ከምዕራባዊያን ተፈብርኮ ለሚደሰኮረው ባልተበረከኩ::አባ ግርማ በሉት መጽሐፍ ገላጭ:ጠጠር ወርዋሪ በሉት መቁጠራ ቸርቻሪ: አንድም የሠራው የፈውስ ሥራ የለም::ለሰዓታት በካናዳው ካሊገሪ ከተማ ከኦገስት 5-7 ባደረገው የውሃ መርጨት ሥራ የብዙ ሰው ልብስ ከማበስበሱ ባሻግር አንድም ተአምር አልታየም:: ፈውስ ነበር የሚሉን ካዳሚዎቹ ብቻ ናቸው::ልብ በሉ ይህ በኦርቶዶስ ላይ የሚደረግ ዘመቻ ነው::ማንም እየተነሳ ክርስቶስ ነኝ ሲል ከልካይ ከሌለው ውሎ አድሮ ቤተክርስቲያኑ የቀጣፊዎች ቤት ትሆናለች::

    • ወይ የእርግማን ልጆች ምነው ምነው በእርግማን ባህር ትዋኛላችሁ ለነገሩ የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም ይባል የለ።እረባካችሁ በካልገሪው የፈውስ አገልግሎት ወቅት እጅግ ብዙ ሺህ ህዝብ እንደነበረ ብታውቁ ኖሮ ከላይ ላላችሁት ድፍረታችሁ እንዴት ባፈራችሁ። ለነገሩ ምን እፍረት አላችሁ አገልጋይነታችሁ ወደ ድቅድቁ ከተጣለው ስለሆነ።ስለዚህ በካልጋሪ የታየው የልዑል አምላክ ድንቅ ምህረት የተደረገበት ብዙ ወገኖቻችን የተፈወሱበት ነው።ዳሩ የክፋት ልጆች እንዴት ብሎ ይገባችኋል?

  2. በል ወዳጄ በነካ እጅህ በየትኛው መፅሐፍ ላይ በመላእክት ሥም አጋንንት እንደወጣ ፃፍልን።

  3. It is heart breaking to see that in our time when Satan controlled our church through a false priest like Girma. Please, followers of Girma read a bible.

  4. እባክዎ ክቡር ፀሐፊ የዲያቆን ዳንኤልን ጽሁፍ እንደገና በቅንነትና በትዕግሥት ያንብቡት፡፡

  5. Wedime egziabiher amilak kale hiwote yasemalin..
    !!!chirstose fikire yegebewu sile egziabiher hawariat yayewun …yesemawun endih yaworal….!!!Dakon Daniel bememihir wengel ersihin bitayewu betam yaligebah yayihud kahin mehonihin tagegnewaleh…
    Daniel…ewunet chirstosin atawukewum…bitawukewu nuro yalayehewun ataweram neber…..for me you are by the book person like menafik….!!!!Just pray…siged …seliyi…then yigeletilihal eshi….!!!egna gin me memihir girma edime yistilin….wengel betam gebitonal…..sile memihir wengel endet biye lingerih….endewu edil agigneteh sibiketachewun bisema…weyi …min tile yihon..!!yete endaleh yigebah neber…gin you are not positive…..!!!
    egziabiher amilak yiridah…..Anyways yayenewun binawora melikam neber…Ato Daniel betam newu yazenikubih….zim bileh yemitawora neger ayimesilegnim neber.!!!!!!
    Ato

  6. Be sm ab weweld wemenfes kdus amen
    Betam tru mels setehw . diakon kbret mm girma yawarede medelev. Ke and tawaki mmhr negn yemil sew endezih mesafu badonetun yasayal. Mm girma yemisetut agelglot yegl betachew bihon mknyat bagegne neber. Gn esachew yemiyageleglut yetekedese tabot balebet Kdus kurban Be misetbet Kdus Kdus Kdus egziabher eyetebale Ye egziabher Sm yemi kedesbet betekrstyan New. Esu Be artodoks tewahdo yemiyamn ke hone tabot Mn yahl hayl endalew baweke neber. Ahun gn bemawekm weym bale mawek Ye egziabhern sm yetesafebet tabotn mnm hayl endelelew New yaderegew. Slezih ke shufu bestejerba and neger ale. Mnalbat le shufu ke menafkan yetekefelew neger ale.
    Egziabher lbonaw ykfetlet.
    Kbr le egziabher weweladitu dngl welemeskelu Be kdsna lemiyagelegult yhun
    Amen

  7. ኢያሱ ባነሳኧው ነጥብ አንድም አመክንዮ የለህም። ስሜትህን ነው የነገርከን

  8. እራሱም ግርማም እንድህ አይልም ግን የዳንክ ሳትሆን የገቢው ተጠቃሚ ነው የምመስለው

  9. Dear
    Did you hear about what Daniel write or hear from someone else? It appears that you read it or hear it by setting Ato Girma in your mind and then you start to write what you understand from your point of view not from writers point of view.

    First, Understand what has been written there from the writers point of view then if you are a critical thinker, try to write on it that will help you for all your future writing concept.

    Daniel wrote about the growing bad trend in the church by supporting his writing from the church teaching philosophy and bible point of view. If you do not agree with him in all context then you are not the follower the church b/c it is all the teaching of the church and the bible.

    For Ato Girma, first of all, he was practicing it 7 years ago near bole (Micheal) and behind ERO (GOD ABE Church), lately, he was denied any further services in those church. Then ASK why?
    was that b/c he was spiritually enough to make that? No there are so many issues to be seen in this case……

  10. Lets use this opportunity wisely to reveal the truth. I would like to appreciate Daniel Kibret’s initiative to break dead lock. This is a very big and challenging problem that faces our church. I don’t have any belief that what this guy is doing is with the spirit of God. However, if there are some people who can defend Daniel’s reflection and view, please come with evidences and lets gently discuss , if possible lets meet in person and reveal the truth for the sake of our brothers and sisters who are confused and follows him without knowledge. I hope Daniel Kibret will take the lead as you have more access. Or Eyasu micheal can organize a meeting as the all we are benefited from the outcome. Thanks Yonata

  11. Dn. Daniel let me ask these questions for you to contemplate. We adherents of the EOTC follow the Alexandian way of interpreting the word of GOD that we take one or two Biblical word and explain it the way we can understand in our real world. In contrary the Antiochian way is taking the biblical words as they are and live straight accordingly. I have listened to many of your sermons in youtube the Alexandian way and you preach it very well that I personally admire which is the way I like. At this time our church is lucky to have many teachers officially graduated from Theological Colleges who speak the true word that way. We thank GOD for that matter. We have learned a lot this kind of sermons from our teachers, you and your likes, but still our people is still drowning.

    Why do you think our church’s servants specially our Mezemiran and Preachers do not live the word they preach? Why is our people not improving in spiritual life though we have a lot of Christian resources (including servants and even churches next to our doors)? Why do you think a lot of our Protestant brothers left us, is that merely because we didn’t tell them the right Tewahedo word? Why is there very mixed and unbelievably complex thoughts/doings around our church intellectuals? How many percent of our Mergetoch and Kahinat are pure from the works of ‘Asmat’s. Specially Mergetoch (debteroch) which are relatively the highest intellectuals of the church, honestly, how many of them are Kahinat (kihnetachewn yetebeku mekedes yemichilut sintochu nachew). Why do you think Mergetoch usually do the ‘Mezemer’ only which does not need any purity check-up like Diakons & Kahinat for Kidase? I believe, from what I see from my personal background – and I am sure you know pretty well about this, most of them are contaminated with the works of ‘Asmat’ which is circulated unanimously around them perceived as hidden power of GOD, which then the devils in the names of the Asmat will make them loose their ground in their christian life in a very smartest way unknowingly. You have your own books and you have read enough books, have you looked in to the Church’s book stores where many non-orthodox books are officially sold, printed out by those who are sole publishers and distributors of many of our prayer books, ‘gedlat’ and related books. I have seen some like Girma Moges, Merbibe Selomon, mestime aganint, Fitha negest and many more who when prayed according to their guidance sewun keAganint gar yemiyakoragnu – this is what is happening to our debteroch and kahinat. Any way why is not told or preached about this serious thing which is killing our spirituality in our church. Why you your self never say any thing about this sickness in our church, is that because you don’t know about it?

    You are historian I hope you investigate about why this kind of malicious satanic works penetrated in our church? Memehir Girma has a lot to say about this in historical perspective (which he directly links to the types of Israeli kahinat who came with Tabote tsion) and it seems right for me. Yeras bet sayatsedu dejaf endet yitsedal?

    May GOD help us all open our insight to know the sneers of the all time Evil work of Satan, the fallen angel

    • በውኑ ሂደታችን ወዴት እንደሆነ እያወቅን ያለን አይመስለኝም በተለይ አወቁ እና ተማሩ የምንላቸው ሰወች ላይ እንዲህ አይነቱ የሂደት መዛባት ጎልቶ ይታያን

  12. እናንተ የዲያብሎስ አሽከሮች ጌታችሁ እንደላካችሁ ከሰይጣኑ ይበልጥ እየሰራችሁ ነው ወዮላችሁ እናንተ የገሀነም ልጆች ለአንደ በታችሁ እንኳ የማታፍሩ ዳሩ ከዲያብሎስ የሚጠበቀው ይሄው ነው።አዎ ሰይጣን የሰውልጅን ፈውስ አይቀበልም አይመቸውም።እናንተም በመምህር ግርማ ላይ የምትሰነዝሩት ነቀፌታ የህዝበ እግዚአብሄርን ልጆች መዳንየማይቀበለው ዲያብሎስ አገልጋዮች ስለሆናችሁ ክርስቶስ ቅጣቱን ይሰጣችኋል።ሳትቀደሙ ንሰሀ ግቡ።።

  13. በውኑ ሂደታችን ወዴት እንደሆነ እያወቅን ያለን አይመስለኝም በተለይ አወቁ እና ተማሩ የምንላቸው ሰወች ላይ እንዲህ አይነቱ የሂደት መዛባት ጎልቶ ይታያን

  14. to tell the truth Dn.Daniel kibret is logical and acceptable spiritual scientist in the world. Like Girma and some “spiritual administrators” are gamblers. so we know what structures.GOD please help our church such obstacles of us

  15. መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ፡- እስመ በቅንአትሰ ኢይትረከብ ፀጋ እግዚአብሔር
    በቅንአት የአግዚአብሔር ፀጋ አይገኝም

    ቅንአት ማለት ለሌላ ሰው የተደረገውን መልካም ስጦታ እና ፀጋ በመፈለግ መመቅኘትና ስም ማጥፋት የማይገባ ነገር መናገር ቅንአት ይባላል፡፡ የእግዚአብሔር ፀጋ በሰዎች ምርጫ የሚሰጥ ሳይሆን እግዚአብሔር በአወቀና በተረዳ ለቤተክርስቲያን ለምዕመናን ይጠቅማል ብሎ ለመረጠው የሚሰጠው ስጦታ ነው፡፡ በዚህ በአለንበት ዘመን በፍፁም ፀጋ እግዚአብሔር ተቋርጧል፡፡ ወይም የፀጋ ስጦታ ያለው ሰው የለም አይባልም ምክንያቱም እግዚአብሔር አምላካችን ሁሌም ህያው ስለሆነ ነው፡፡ አንዳንድ እንደእነ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የመሳሰሉ ከየት ጎራ እንደሆኑ የማይታወቁ አስማሳይ በቤተክርስቲያኒቱ ስም የሚነግዱ በሚዲያ መቅረብን መንግስተ ሰማያት መግባት አድርገው የሚገምቱ ከእኛ በቀር ለምን ሌላ ሰው አንቱ ይባላል ብለው የትውልድን ተስፋ የሚያጨልሙ አንዳንድ አስማሳይ የወንጌል አገልጋይና ተራ ሁለገብ መልስ ሰጪ የሆኑ የእግዚአብሔርን ሥራ ቀርበው ሳያዩ የእግዚአብሔር ሰዎችን ሥራ ቀርበው ሳይረዱ በቅናት መንፈስ በየፌስቡኩ የለቀቁትን የቅናት ውጤታቸውን ተመልክተን አላውቂ በመሆናቸው አምላክ ሆይ ይቅር በላቸው ብለናል፡፡
    ለመሆኑ ለዘመናት በቤተክርስቲያኑቱ ላይ አንዳንድ ከአምልኮተ አግዚአብሔር ወጥተው ለአንጀራ ብቻ ተጠግተው ሕዝቡን በደብተራዊ መተት ግራ ሲያጋቡትና ሲመትቱበት የኖሩትን ለምን ተው አላላቸውም፡፡ ሰይጣንን በሰው ልጅ ላይ መልክዓ ሳጥናኤል እየደገሙ ሲያሳብዱ ለምን ከክርስቲያናዊ ህይወት ውጭ ነው ብሎ አልፃፈም? ለነገሩ አንተም የእነርሱ ተባባሪ ስለሆንክ ዝም አልክ፡፡ አሁን ግን በአደባባይ ለምን አጋንት ወጣ ትውልዱ ለምን ቆረበ ሰገደ፣ ፀለየ፣ መቆጠሪያ ለፀሎት ተጠቀመ፣ ብሎ ለሰይጣን ዋስ ሆኖ መቆም በጣም ይገርማል፡፡ ይህ አባባልህ ምንም ዲያቆን አያሰኝህም፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ መልክቱ በምዕራፍ 13 ቁጥር 13 ላይ ‹‹በክርክርና በቅናት አይሁን›› ይላል ይህ ዳንኤል ክብረት እውነት ለትውልዱ ያሰበ ቢሆን ነገሩን ጉባዔው የሚካሄድበት ቦታ ድረስ መጥቶ ለግለሰቡ ቃለ መጠይቅ በማድረግ ትምህርታቸውንም በማድመጥ አና የጉባዔውን ምዕመናን በመጠየቅ መሆን ነበረበት ግን ለምን በፀጋቸው እግዚአብሔርን አገለገሉ ፣ ለምን የእግዚአብሔር አምልኮ የገባው ሕዝብ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ወደዳቸው፣ ትምህርታቸውንስ ለምን ሰማ በማለት በቅናት የተፃፈ ጽሁፍ ስለሆነ መላከ መንክራት ግርማ ወንድሙን አይመለከትም፡፡
    ለመሆኑ መላከ መንክራት ግርማ ወንድሙ ማናቸው? እስኪ በጥቂቱ እንመልከት መላከ መንክራት ግርማ ወንድሙ ከካህን አባታቸው ከመምሬ ወንድሙ መንግስቱ ተወልደው በባሌ ጎባ ባለወልድ እና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በብፁዕ አቡነ መቃሪዎስ ዲቁና ተቀብለው ከዚያም በኋላ ብዙ መንፈሳዊ ትምህርት እና የእርኩስ መንፈስ ውጊያን ከግብጽ አባቶች በህይወት አይተውና ተምረው ዛሬ በሥልጣነ ክህነት ሕዝቡን አጋንንት በማውጣትና ድውይ በመፈወስ ፀጋቸው እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡ አገልግሎታቸው ብዙ ፈተና እና ትችት ያለበት ቢሆንም ፕሮግራሙ የሚካሄድ በእግዚአብሔር ፈቃድ ስለሆነ እስከዛሬ ድረስ በርሱ ቸርነት አልተቋረጠም፡፡ አሁንም ማንም በማንኛውም የሥልጣን ደረጃ ላይ ያለ ሰው ለማውገዝም ለማገዝም በግልጽ የሚካሄደውን ጉባዔ የማካሄድበት ቤ/ክ ድረስ በመምጣት መከታተል እና ችግር ካለ በመረጃ መንቀፍና መተቸት ይችላል፡፡ ይህ ባልሆነበት መልኩ አንድ ቀን እንኳን ጉባዔው ላይ በግልጽም ይሁን በስውር ሳይገኙ መተቸትና መንቀፍ ራስን ከግምት ውስጥ ይጥላል፡፡ ለነገሩ ሰካራም ያለበት ቤትና ባዶ በርሚል መጮኸ ያበዛሉ፡፡ ብዙ ጽሁፎችን ተመልክቼአለሁ፡፡ አንብቤአለሁም ከርዕዬተ ዓለመኞቹ ርዕዬተ ዓለመኞ ነህ ከማርክሲስቶቹ ማርክሲስት ነህ ፣ ከተቃዋሚዎቹም ተቃዋሚ ነህ በጣም ደግሞ የሚገርመው ከመንፈሳዊዎቹ መንፈሳዊ ነህ እንዲህ ስልህ ግን በፀጋ አይቼ አይደለም፡፡ የምትጽፋቸውን ጽሁፎች አንብቤ ነው፡፡ እንደ አኔ አሁን ሳይህ ግን ተራ ጋዜጠኛ ነህ ይህን ያልኩበት ምክንያት 1ኛ ሕዝቡ ውስጥ ያለውን ህይወት ችግርና መከራ አጠቃላይ የሆነውን የክፉ መንፈስ ጉዳት ምን ያህል ወገኖች እንደተሰቃዩ ለመረዳት በጎ ህሊና የለህም በ2ኛ ደረጃ አንተ አስተምረዋለሁ ብለህ በወንጌል የምትሰብከው ሰይጣን ከአንተ እውቀት በላይ አልፎ እንደሄደ መረጃው የለህም ስለዚህ መረጃ በሌለህ ነገር ላይ የፃፍከው ነገር ሁሉ ባዶነትህን ያሳይብሀል፡፡ ቅድሚያ የሚሰጠው ለመሆኑ ለህዝብ ወይም ለምዕመናን ችግር መፍትሔ በመስጠት ነው ወይስ ለብቻ ተሰውሮ በዋሻ ውስጥ እድሜ በመጨረስ ነው፡፡ክርስቶስ እኮ ያለው ወደ አለም ሂዱ ነው፡፡ ይህን የወንጌል ቃል ወዴት አደረስከው የዮሐንስ ወንጌል 7 ፡- 4 ላይ ለጌታ እንኳን ሐዋርያት ያሉትን ከዚህ ወንጌል ተረዳ፡፡ አሁንም አንተ እውነታውን ለማወቅና ለመረዳት ጉባዔው በሚካሄድበት ቤተክርስቲያን መጥተህ ብትከታተልም ብታስተምርም መላከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በፍፁም ፈቃደኛ እና ደስተኛ መሆናቸውን እያረጋገጥኩልህ ምናልባት አንተ ገና ስለሆንክ መንፈሳዊ ውጊያ ስላልገባ በውስጥህም ያለው ክፉ የሰይጣን መንፈስ ወደ ጉባዔው እና ወደ ወንጌል እውነት እንድትመጣ ካልፈቀደልህ እኔ የምመክርህ በመምህሩ የተፃፉትን በማለዳ መያዝ ቁጥር 1 እና 2 ትን በደንብ አንብብ የመምህሩን የአገልግሎት ሁኔታ እና ትምህርት የሚያሳየውን በቪሲዲ ከቁጥር 1 እስከ 36 ያለውን ካሴት ተመልከት፡፡ ወንድሜ ከተዋህዶ እውነት ከወንጌልና ከዓይናችን በላይ ማንንም አስመሳይ ያለፀጋ እግዚአብሔር የሚጮህ የወንጌል አስተማሪነኝ ባይና ሁለገብ ተራ መልስ ሰጭን አንቀበልም እግዚአብሔር አምላክ ማስተዋሉን ይስጥህ ፀጋ እግዚአብሔር ያላቸውን የቤተክርስቲያን አባቶች አያሳጣን አሜን ፡፡
    ከነቃጥበብ ዘወንጌል

    • Yihe Daniel Kibret haymanot min endehone yalgebaw mehonun yasayal. Memhr Girma qualifies to be the better candidate by many standards as compared to the current priests. God can choose any person if that is His intent. There should be something wrong with Daniel for his comments that needs to be investigation. Probably he is trying to hide the drug (etse fars) he took when he was a diakon. Remember that he came from a place where the debteras erect a rope.

  16. ወገኖቼ ይህኝን አባት ብንከባከባቸው ነው የሚሻለው ምክንመያቱም ከእግዚሀብሄር በተሰጣቸው ፀጋ የሰውን ልጅ ክፉመናፍሥት ወይም ዳቢሎስ ስራ እየፈወሡ ነው የሚገኙት የሚገርመው ደግሞ የትኛዉኘንም እምነት ተከታይ ሢፈውሱ በቪጀዲዮ ላይ አይተናል። ስለዚህ በዝሁ ቤተክርስታናችን አሀልጋይ የሆናችሁ ብትደግፉቸው መልካም ነው። እኔ በበኩሌ እደኚ አባት በህይወቴ ሀይል ከእግዚአሀብሄር አግኘቶ የሚፈውስ በአይኔ አላየሁመም። ልኡል እግዚሀቤሄር አባት እድሜና ጤና ይስጥልን። በተጨማሪ አባታችን ከሚሉት ት ልቅ አንዱ ” የተነካው, የደረሰበት ነው የሚያውቀው ያልተነካው ለመረዳት ብዙ ጊዜ ይፈጃል ። የዳቢሎበስን ክፉ ስራ ከውስጣችን ለማስወገድ መፆም, መስገድ እና መፀለይ እንዳለብን በሰፊው ያስተማሩን ድንቅ አባት ናቸው። ለአባታችን እኛ የሰው ልጆች እድንድን በፀሎታቸው ጥንካሬ ቸሩ መድሀንያለም እየሱስ ክርስየቶስ አመላዕከ መንክራት ግርማ ወንድሙን ስለሰጠን ከፍ አድርጌ አመሰግነዋለሁ። በተረፈ ወገኖቼ መድሀንያለም እንደ መምህር ግርማ ያሉ አባቶች አብዝቶ ይይስጠን። ለአባታችን መፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ ካሉ ታላላቅ እድሜ አብልጦ ይስጥልን። ዛሬም ዘወትርም እግዚአሀቤሆር የተመሰገነ ይሀን። አሜን!

  17. Enanete setaweru, setefetefetu abete sentu dane. Abatachene Egziabeher Amlak Edemewene, Tenawene, Tsegawene abezeto, abezeto chemero yesetote, Amen! Nurulene egna enfelegotalene!

  18. ye Daniel kibret enkuwan aygermem !

    Awde,Negestam hulu Memhir Girman yeqawemal eko

    le kibir ,,le meweded,, le GirmaMoges letesemenet eyalu be Debtera yemeyasmetitut Metet yegaletal belew yeferaluwa !! kkkkkkkkk be Qenat bereket yelem !!

    Long live Memher GIrma !!

  19. I don’t think u read or heard wat Daniel kibert trying to say very logical.every single word of z article is based on Bible and mesafe deguwa…which we orthodox follow.so if u disagree with his words then just like he did explain us why u disagree with him.other wise it looks like u r just fan of memeher grma.but as far as I am concerned wat most important is z our orthodox church serat ena kenunawa new not an individual. We all should care abt our church more than anything… Coz this is z hardest time ever for orthodox church, attacked by inside and outsiders.

  20. እኔ የምናገረው ለምህር ቴፎዞ ሁኜ አይደለም፡፡ የማውቀው ግን እንዲህ ነው፡-
    1) ስለ አገልጋዮች
    ሀ) በመርህ ደረጃ በክርስቶስ ስም ሀይል ማድረግ ይቻላል ይላሉ፡ ተረት ዐይነት በሀዋርያት ዘመን ብቻ የነበረ አንደማለት ነው፡፡
    ለ) በተግባር ግን ታዓምርና ድንቅ የሚደረገው በዓጋንንት ነው ብለው ከልብ ያምናሉ፡
    ሐ) ገቢረ ተዓምራትንም የሰለሞን ጥበብ ብለው በዐጋንንት ሀይል ሲሰራ ያያሉ፡
    መ) ለአብነት/ትምህርት፡ ለመወደድ፡ ለሞገስ፡ ለሹመት፡ ለድምፅ፡ ወዘተ ብለው መተት ያስደርጋሉ
    ሠ) ለደብተራወች ክብር ይሰጣሉ ያጎበድዳሉ፡
    ረ) ክብር ፈላጊወች ፡ ገንዘብ ወዳጆች ፡ ይሁዳን የሚመስሉ፡ አስመሳዮች ናቸው፡
    ሰ) ቅ/ቁርባን አይወስዱም፡ አይሰግዱም፡ የፀሎት ቤት የላቸውም፡፡
    2) መምህር ግርማን የሚወዱ፡
    ሀ)በመተት ታስረው የሚሰቃዩ
    ለ)በደብተራ የተጭበረበሩ
    ሐ)ከዘር በመጣ በዐድ አምልኮ በዛር በውቃቢ የሚሰቃዩ፡
    መ) በመናፍቃን የውሸት ክርስትና የተታለሉ፡
    ሠ) በሀጢያት መኖር የሰለቻቸውና ክርስቶስን የተራቡ
    ረ) በባዶ የነጋዴወች ስብከት የተሰላቹ፡
    ሰ) በአጠቃላይ ፅድቅን የሚሹ ናቸው፡፡

    በክርስቶስም ዘመን እንዲሁ ነበር፡፡ ካህናት፡ አገልጋዮች፡ ገዥወች ከሳሾች በትምህርት በውቀት በክብር ከፍ ያሉና ለእግዚአብሄርም የሚቀኑ ይመስላሉ ፡ ግን ክፋትን ያግዙ ነበር፡፡

    ድሆች፡ የታሙት፡ በአጋንንት የተያዙት፡ ግን ክርስቶስን መከተል ብቻ ሳይሆን፡ ጌታ መሆኑንም ያውቁና ይመሰክሩ ነበር፡፡

    ጥያቄ ለኦርቶዶክስ ልማዳዊያን፡-
    1) መናፍቃንን የሚመልስ
    2) አህዛብን የሚሰብክ
    3) ጠንቋዮችን፡ ደብተራወችን፡ መተተኞችችን የሚቃወም፡
    4) የተቸገሩትን የተጨነቁትን የታመሙትን የሚፈውስ የሚረዳ
    5) በክፋ መንፈስ ላይ ንቁ፡ ንስሀ ግቡ፡ ፀልዩ፡ ፁሙ፡ ስገዱ፡ አስራት አውጡ፡ የሚል
    6) ፍቅር ያለው፡ የማይዋሽ፡ በሚናገረው ቢመረመር እንከን የማይገኝበት ሰው፡
    7) ከሁሉም በላይ ክርስቲያኑን ቤ/ክርስቲያን በክርስቶስ ስም እንደምታድን ያሳየን

    እንዴት ጠንቋይ ነው ይባላል???????

    ማስታወሻ፡-
    1)በዘመናችን ያሉ አገልጋዮች በቤተክርስቲያን እንዲፀና ካደረጉት ሰው መናፍቅ ያረጉት ይበዛል፡፡ በሀገራችን ከ25 ሚሊዮን በላይ ጴንጤ እንዳለ እወቁ፡፡
    2) በዝርፊያ፡ በክስ፡ በፀብ፡ በጉቦ፡ በድብድብ፡ በክፋት ወዘተ አገልጋይ ነን የሚሉትን የሚያክክል የለም፡፡
    3) ለአምላክ ሳይሆን ለሰው በመሰገድም፡ አገልጋዮች ችሎታቸው ልዩ ነው፡፡
    4) አገልጋዮች፡ እነሱን በመጥላት ሰው ቤ/ክርስቲያንን ጥሎ ሲሄድ 8ኛው ሺህ ነው፡ ይሂድ ፡ የቀረው ይበቃል ብሎ በመሸንገል ልሂቃን ቢባሉ ያንሳቸዋል፡፡

    …. ይበቃል፡፡፡

    ልብ ማለት ጥሩ ነው፡፡ ቅን መሆንም ጥሩ ነው፡፡ ማስተዋልም ፍቅርን ማብዛትም እንዲሁ፡፡ ከቅናት መራቅም በጎ ነገር ነው፡፡

    አገልጋዮች አስተውሉ፡፡ ቢያንስ በየፀበሉ አጥማቂ እንኳ አልታመን ብሉ መላእክት፡ ሰማእታት እራሳቸው እያጠመቁ ክርስቲያኑ ሲገለገል አታዩም፡፡ አንድ መምህርን ብናገኝ ክስ አበዛችሁ፡፡ የእግዚአብሄርን ማዳን የአጋንንት ነው አላችሁ፡፡

    እግዚአብሄር ሁላችንንም ይርዳን፡፡

  21. አብዛኛውን ኮሜንት አንቢባለው። እኔ የኦርቶክስ ቤተ ክርስቲያን አማኝ ነኝ እንደ አማኝነቴ አንድ ልበል። በነገራችን ላይ እንደዚ አይነት መወራረፍ አልደግፍም ምክንያቱም ከስር ያለው ምእመን ይጐዳል ወይም ወዳልተፈለገ መከፋፈል ይሄዳል።
    ለነገሩ መከፋፈል በቤተ ክርስቲያን ሠዎች ይብሳል።

    እኔ እንደውም ለወደፊት ምፈራው የትግሬ፣የወሎ፣የጎንደር፣የጎጃም፣የጉራጌ፣የኦሮሞ…ወዘተ ቤተ-ክርስቲያኖች እንዳይኖር ነው። ም/ቱም አልጣመኝም በትንሽ ነገር ጀርባ ለጀርባ መሠጣጠቱ…

    በተጨማሪ ምእመኑን የምለው እባካቹ የሠው ሀሳብ ደጋፊ ለመሆ አትሯሯጡ እባካቹ ምክንያታዊ ሁኑ።

    በሌላ በኩል ሂስ በግልፅ መሠጣጠቱ ጥሩይመስለኛል ነውም። ጥሩ የሚባለውን ሀስብ ለማመንጨት ግን ስርአት ባለው መልኩ/ቋንቋ/።

    የኔ ሀሣብ ከላይ ወንድሚ ያለውን ሀሣብ እጋራለው። በምሳሌነት፦

    እኔም እስማማለው እናም እንዳለው ካላገኛሀቸ ልታገኛቸው ብትሞክር እላለው ዲ/ን ዳንኤል ክብረት…

    እውነት ነው፤በተደጋጋ ተገኝቼ አይቻለው። ሌላው ሌላው ይቅርና የህሙማን ቤተሠቦች ደስታቸውን በእንባ ነው ሚገልፁት።እናም ሌላም ሌላም…

    ወንድሚ እንዳለው ዲ/ን ዳንኤል ክብረት እውነት እውነት በቦታው ተገኝተ ያልፃፍከው ከሆነ በጣም ያሣዝናል ካንተ አልጠብቀውም…

    ብዙ ብዙ ማለት ይቻላል ለኔ ስለ መምህር ግርማ ምስክር አያስፈልገኝም ዲ/ን ዳንኤል ክብረት እንኳን ብትሆን። በጣም ሚያሣዝነኝ በመምህር ግርማ ፀጋ የተፈወሣቹ ሠዎች የት ገባቹ ቢያንስ ቢያንስ እንደዚ አይነት ነገር ላይ ከጎናቸው ብንቆም
    ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ወንድሚ ያነሳቸው ሀሳቦች በጣም አማካኝ አማካኝ ጥያቄ/አስተያየቶች ናቸው። ስለዚ መልስ ብትሠጥበት ይሻላል ም/ቱም ምእመኑ ባንተ ላይ ያለውን እምነት ይሸረሽረዋል ያንተንም ብቻ ሳይሆን ባንተ ደረጃ ያሉትን ሁሉ፤ይህ ደግሞ በጎቹን ለአውሬ ማስበላት አይመሥልህም ዲ/ን ዳንኤል ክብረት አንባቢያንስ ምን ትላላቹ??

Comments are closed.

Share