በቤተልሄም የወሲብ ጉዳይ ‹‹ዴሞክራት›› ለመባል የፈለጉት አቶ አብርሃም ደስታ

ከበልዩ

የአቶ አብርሃም ደስታን ፅሁፍ ስመለከት ጆርጅ ቡሽ ልክ በ2008 ከስልጣን ሲለቁ ስለእሣቸው ሕብረተሰቡ ይገነዘብ ዘንድ አንድ ፊልም ተሰራ፡፡ይህንን ፊልም የሰራው ታዋቂው የፊልም ዳይሬክተር ኦሊቨር ስቶን ነበር፡፡የፊልሙ ርእስ “W ” ይባላል፡፡ በዚህ ፊልም ላይ የጆርጅ ቡሽን እድገትና ወደ ስልጣን አመጣጥ የተመለከተ ሁሉ ይህ ሰው ይሄ ነው እንዴ ብሎ በቃ በእሣቸው ላይ ቂም ከመያዝ ይልቅ መተው ነው ብሎ አለፋቸው፡፡ ይህንን በመግቢያነት ለመጠቀም የፈለኩት አቶ አብርሃም ደስታ በተደጋጋሚ በፖለቲካዊ ትንታኔ ዙሪያ የሚያወጧቸውን ፅሁፎች አነባለሁ፡፡ ጥሩ አድናቂያቸውም ነኝ፡፡ ግን ምን ታዘብክ ብትሉኝ የፖለቲካ ተንታኝ ከዛ ወጥቶ ሌላ ትንታኔ ላይ ሲገባ ምናልባትም በእሱ ውስጥ ያለው አስተሳሰቡ የሚታይበትና የሚጋለጥበት ሁኔታ ይፈጠራል ማለት ነው፡፡
እንደሚታወቀው ባለፈው ሰሞን “ቢግ ብራዘር አፍሪካ” ላይ ኢትዮጵያን ወክላ ወደዛ የተጓዘችው ቤትልሄም ተሾመ የፈፀመችው ወሲብ ለፕሮግራሙ ትልቅ ስም ሲያሰጥ ለእሷና በተለይም ለኢትዮጵያዊያን ደግሞ ውርደትንና እፍረትን አከናንቧል፡፡ አቶ አብርሃም የዚህ የእሷን የተዋረደ ተግባር ያዩበት አንግል በአንድ አቅጣጫ ነው ብሎ ለመናገር የሚከብድ ከመሆኑም በላይ የኢትዮጵያዊያን ባህል የራሣችን አስተሳሰብ፣ የራሣችን የሆነ ልማድ እንዳለም የዘነጉ ይመስለኛል፡፡ በተለያዩ ሀገራት ኢትዮጵያዊያን በሩጫው በሚያመጡት ውጤት ባንዲራችን ከፋ ብሎ እንዲውለበለብ አድርገው ያጨበጨብንላቸው አትሌቶች ታሪክ እያለ ኢትዮጵያዊቷ በዚህ ውድድር ላይ ወሲብ ፈፀመች የሚል ስም ሲበረዝበት ምን ያህል እንደሚያሣፍርና እንደሚያሸማቅቅ የተረዱት አልመሰለኝም፡፡
አቶ አብርሃም ሁሉንም ነገር ከወሲብ ጋር የተያያዘ አድርጐታል፡፡ ከወሲብ ጋር መያያዙ አይደለም ከኢትዮጵያዊነት ስነ ምግባር አንፃር ነው መታየት ያለበት፡፡ይህቺ ሴት በዚህ ውድድር ላይ ስትካፈል እኮ ወሲብ ለመፈፀም አይደለም የገባችው፡፡ በምትቆይበት ጊዜያት ውስጥ በተመልካች ትኩረት የሚሰጥ ወይም የሚመስጥ ነገር ማድረግ ነው፡፡ አላማው የወሲብ ከሆነማ ለምን ቤቲ ወሲብ ፈፀመች ብለን እንቃወማለን፡፡ እሷ ግን ከዚህ አላማ በመውጣት ሌላ መንገድ ውስጥ ገብታለች፡፡ ይህ ማለት ለስሜቷ የተገዛች ሆናለች ማለት ነው፡፡ ትልቁ ነገር እራስን መቆጣጠር ነው፡፡ራሷን መቆጣጠር የማትችል ለስሜቷ የምትገዛ ከሆነች በዚህ ውድድር ላይ መሣተፍ ፈፅሞ የለበትም ነበር ማለት ይቻላል፡፡ አቶ አብርሃም በዚህ ዙሪያ ለምሣሌነት የተጠቀሟቸው ነጥቦች ደግሞ ይበልጥ ያሣቀኝና ያስገረሙኝ ናቸው፡፡ ለምሣሌ “ሀሺሽን ጠልተን የቦምባርሌን ፎቶ የሰቀልነው” ሲሉ ገልፀዋል፡፡ለመሆኑ ቦብማርሌ በድምፃዊነቱ ነው የሚታወቀው ወይስ በሃሺሽ አጫሽነቱ ለመሆኑ ቦብማርሌ ድምፃዊ ብቻ ሣይሆን የነፃነት ታጋይም ነው፡፡አፍሪካ በቀኝ ግዛት ስር በነበረችበት ወቅትና ከዛም በኋላም የፈፀመው ነገር ትልቅ ቦታና ታሪክ ያለው ነው፡፡ ምናልባትም የአለማችን ታላቁ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማን ሄደው ስለቦብማርሌ ቢጠይቁ የሚሰጠዎት ምላሽ በተመስጥኦ የታጀበና ለእሱ ያላቸውን ክብር የሚያመለክት ነው፡፡ እናም የቤቴልሄምን ተግባር ፈፅሞ ሊገናኝ በማይችል መልኩ ከቦብማርሌ ጋር ማገናኘቱ ምናልባትም ከላይ በመግቢያዬ ላይ ስለጆርጅ ቡሽ ማንነት ወይም ስብእና ለማወቅ ፊልም እንዲሰራ እንደተደረገ ሁሉ የአቶ አብርሃም ደስታን አስተሳሰብ ለመረዳት ደግሞ የቤተልሄም ጉዳይ ተፈጠረ ማለት ነው፡፡
በርግጥ አንድ ችግር አለ ሁሉም ሰው የሆነ ተከታይና ደጋፊ ማፍራት ይፈልጋል፡፡ አቶ አብርሃምም እንደፖለቲከኛነቱ የሆነ የዘመናዊው ፖለቲከኛ ወይም “ዴሞክራትነታቸውን” ለማሣየት የፈለጉና ቤቲ መብቷ ነው በራሷ ምናምን እያሉ ዘመናዊ ነን የሚሉ ወገኖችን መንገድ በመከተል ስምና ዝናን ለማግኘት የፈለጉ ይመስላል፡፡ ይህ ግን የዘመናዊነት ምልክት አይደለም፡፡ ወይም በመብት ላይ ለማሣወቅ መጣርም አይደለም፡፡ ካላወቅንና ነገሩ ካልገባን ዝም ማለት ይቻላል፡፡ የፕሮሞሽን ስራ ይመስል በሁሉም ነገር ላይ ጥልቅ ካሉ ኋላ ላይ እንደቡሽ ጭንቅላት ይመረመርና ከዚህ ቀደም ይታወቁበት በነበረው ነገር ላይ ጥርጣሬ እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡ ይህቺ ልጅ የፈፀመችው ነገር ስህተት ነው፡፡ ምናልባት አቶ አብርሃም እንደበሰለ ፖለቲከኛ ሲሆኑ የሆነው ነገር ጥሩ አይደለም፡፡ ግን ሆኗል መታረም ይገባዋል በማለት ቢገልፁት ምንኛ ባማረ ነበር፡፡
ግን ከዚህ በመውጣት እርስ በእርሱ የሚጣረዝና ጠለቅ ብሎ የፕሮግራሙ ወይም የውድድሩ ሂደትን በደንብ ሣይረዱ በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየት ካልሰጡ ችግር ይገጥማል የተባሉ ይመስል ዝም ብሎ ዘባርቆ መፃፍ ግን ዝናን ናፋቂና ዘመናዊ ነኝ ባይ ከማስባል ያለፈ አይሆንም፡፡ አቶ አብርሃም ኢትዮጵያዊያን እኮ የራሣችን ባህል አለን ያልኩት በሀገራችን ወንድ ልጅ ወንድን ቢያቅፍ ችግር የለውም፡፡ አሜሪካ ግን ይሄን ቢያደርግ ሌላ ስያሜ ያሰጠዋል፡፡ በሀገራችን ሚስቱን እንኳን በአደባባይ ከንፈር ላይ የሚስም የለም ይህ የኛ ባህል አይለምና፡፡ በሌላ ሀገር ግን ይደረጋል፡፡ ቤተልሄምም ቢሆን ከዚህ አይነቱ ሕብረተሰብ ነው የወጣችው ይህን ስሜትም ይዛ ነው የኖረችው፡፡ ስለዚህ በዚህ መልኩ የሄደ ሰው ደግሞ እዛ ላይ ኢትዮጵያዊ ሲያየው ምን አይነት ስሜት ሊፈጥርበት እንደሚችል መረዳት ይኖርብናል፡፡ እሷ እኮ መምህር ናት፡፡ ለተማሪዎቿ አርአያ የምትሆን፡፡ ከዚህ በኋላምን አይነት መምህር መሆን ትችላለች፡፡ አቶ አብርሃም ይህን ሁሉ ነገር ማሰብ ከማውራት በፊት ግራና ቀኝ ማየት ያስፈልጋል፡፡ ወጣት ስለሆኑና ወጣት ስላጠፋ ማስተባበል የዘመናዊነት ምልክት አይደለም፡፡ እናም በቤቲ ጉዳይ በግልዎ ፅፈው ቢያነቡት ወይም ቢያልፉት በተሻለ ነበር፡፡ እናም አቶ አብርሃም በቤተልሄም ጉዳይ ዴሞክራት ለመባል ያሰቡት ነገር ፈፅሞ አልተሣካም፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢትዮጵያ ነፃ ጋዜጠኞችንና ጦማርያንን ማን ይፈራቸዋል?

11 Comments

  1. ጎበዝ፡ ምን ነካችሁ? እዚያ ትግራይ ደደቢት እሚባለው የመሬት ቤርሙዳ ተለክፎ የሚናገረው አንደበት፡ እውን በጸበል የሚድን ይመስላችኋልን?
    አቶ አብርሃም የሚባለው ሰው፡ ቤቲ የምትባለው ወራዳ እንኳንስ በኢትዮጵያዊነት ልቅ በሚባሉት ምእራባውያን ሳይቀር PROSTITUTE የሚል ርካሽ ስም እንደሚያሰጣት የምታውቀው ከቢግ ብራዘር እስር ቤት ስትወጣ የምታውቀው ሃቅ መሆኑን ባወቁ።
    ቦብ ማርሌይ ከመሞቱ 7 ወራት በፊት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ከርስትና ትምህርት በአቡነ ይስሃቅ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ተምሮ የተጠመቀና፡ የክርስትና ስሙም ” ብርሃነ ስላሤ ” መሆኑን እናውቃለን። ካለፈው ስህተቱ ንስሃ ገብቶ አልቅሶ ስለጥቁር ነጻነት ታግሎ፤ የተጣሉትን አስታርቆ ይህችን ዓለም የተሰናበተ፡ የዓለማችን ክቡር ሰው ነው። እርግጥ ነው በነበረበውት የራስ ተፈሪያን እምነት ማጫጫሱ ታይቶበታል፤ ያኔ የተቀረጹ ፊልሞችንም እስካሁን የሚጠቀሙበት ራስ ተፈሪያኖች አሉ። ቤቲ ወይም ቤተልሔም በሚል መጠሪያ ኢትዮጵያን ወከለች የምትሏት፡ ወያኔን ወከለች በሚለው እንስማማለን።

  2. ato belyu betam ameseginalehu betiru geltewtal abreham tebyawnim anibbewalehu yemaygenagn neger new yetafut bcha 10q

  3. Yiqerta talaq newu. Yiqer enbabal hulachenm Lehagerachen Kalen Melkam hilm Yetenesa Asteyaytu Negeru betam slekerere Lemargeb Lihon yechelale Yih Ybilih sewu sera newu sewu siyatefa neger ayaganenm yaberdal. Tifatu Manm Ethiopiawi yasdesete aydelem.

  4. Thank you Beleyou, You have explained it well. I have one question to Abraham Desta: What would be your response if Beti was your sister?
    Nobody said sex is wrong but when you do it live on TV show in the name of Ethiopia (Ethiopian Flag) it is definitely wrong.

  5. well said! i was the one who was given him big respect for what he has been written previously. but i don’t know why did he say that because the film what we saw is not porno film that she still could have done it to make money if she run for money on top of that making sex on public media is freedom? or is that civilization? i don’t get it what’s Mr abraham going to tell us::

  6. Good point, Belyu

    I think, we seem to have lost most of our traditional values since Wayanne came to power. We try keep our social norms with us as part of who we are. Since Weyannes came to stage, they try to impose their “culture of the jungle” to impose on Ethiopian people : the culture of “Yilugnta Bissenet”, “Hafrete Bissenet”, “Ayen Yawetta Wushet”, “Raas Wedadenet”, “Sew Teffunnet”. So, Betty and her-likes are victims these social reengineering projects on Ethiopian people.

  7. Beti has done a sin and a shame. She has to repent. But all of us are sinners and she has to be forgiven.

  8. Beliyu I appreciate all point specially the way Abreha involve with the issue he misses the Value of our culture may be this will the final clearly articulated speech to all of us if he is good at lesson learning topics this is the end period.thanks again Beliyu.

  9. Arife new …yes you are write she better to ask apology with any public media ……
    I don’t have much enough info about the program and how it works here in addis. but The goverment shouldn’t put them asid those facelitators if there any one as an agent for next time. It matters when she is called “Ethiopian” rather Betiy.
    Stay safe!

Comments are closed.

Share