June 23, 2013
6 mins read

ፕ/ት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የሌባ ተባባሪነት ለመደባቸው

haile and girma

ከጥቂት ሳምንታት በፊት ዘ-ሐበሻ የጥንታዊት ኢትዮጵያ አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ሊቀትጉሃን አስታጥቄ አባተ አቅመ ደካማ ለሆኑ አባት አርበኞች የፈቀዱላቸውን 25 ኮንዶሚኒየም ቤቶች ለግል ጥቅም አውለዋል፣ ከሚያከራዩዋቸው ሕንፃዎች ከሚያገኙት ገቢ ላይ የአከራይ ተከራይ ግብር አለመክፈል፣ ያላግባብ ወጪ ማድረግና በመሳሰሉት ተጠርጥረው መከሰሳቸውን መዘገቧ ይታወሳል። ዛሬ አዲስ አበባ ላይ ታትሞ የወጣው ሪፖርተር ጋዜጣ “ፕሬዚዳንት ግርማ የአርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ክስ እንዲቋረጥ ጥሪ ማቅረባቸውን” ያትታል። ዜናውን ለተመለከተ ከዘራፊው የወያኔ ስርዓት ጋር በመተባበር “አበባ የመትከልና አበባ የመቁረጥ ስልጣን” ብቻ ተሰጥቷቸው ቁጭ ያሉት ፕሬዚዳንቱ እኚህን በርከት ያሉ አርበኞች አባቶችን ያስለቀሱትን ሊቀትጉሃንን ክሳቸው ተቋርጦ ይፈቱ ሲሉ በድፍረት መጠየቃቸው የሌባ ተባባሪነቱ ለመደባቸው፤ ወይም ከሌባ ጋር መተባበር ሱስ ሆነባቸው እንዴ? ያስብላል። የሪፖርተር ዜና እንደሚከተለው ነው። አንብቡትና ትዝብታችሁን ጣሉበት።

በከባድ የማታለል ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው የጥንታዊት ኢትዮጵያ አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት፣ ዋና ጸሐፊና የአስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊ፣ የተከሰሱበት ክስ እንዲቋረጥላቸው ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ፣ ለፍትሕ ሚኒስቴር የጻፉት ደብዳቤ ውድቅ መደረጉን ምንጮች ለሪፖርተር አረጋገጡ፡፡

የአርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ ለፕሬዚዳንት ግርማ በጻፉላቸው የመማፀኛ ደብዳቤ አማካይነት፣ ክሳቸው እንዲቋረጥላቸው ወይም በይቅርታ እንዲታለፉ ፕሬዚዳንቱ ደብዳቤውን የጻፉት በፍትሕ ሚኒስቴር የሕግና አስተዳደር ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ለአቶ ብርሃኑ ፀጋዬ መሆኑን ምንጮቹ አረጋግጠዋል፡፡

በከባድ የማታለል ወንጀል ተጠርጥረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ስምንተኛ ወንጀል ችሎት ክስ የቀረበባቸው የኢትዮጵያ አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ፣ ዋና ጸሐፊው ፲ አለቃ ሰጥአርጌ አያሌውና የአስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊ አቶ በቀለ ሻረው መሆናቸው ይታወሳል፡፡

ፕሬዚዳንት ግርማ ተጠርጣሪዎቹ በአገራቸው የጀግንነት ታሪክ ከፍተኛ ቦታ እንዳላቸው፣ ለአገር ልማትም በአሁኑ ጊዜ ከፍተኛ እገዛ እያደረጉ መሆናቸውንና ዕድሜያቸውም የገፋ መሆኑን በመግለጽ፣ መንግሥት ይቅርታ አድርጐላቸው ክሳቸው እንዲቋረጥ በደብዳቤ መጠየቃቸውን ምንጮች አስረድተዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ ግንቦት 29 ቀን 2005 ዓ.ም. በቁጥር መ/818/2005 የጻፉትን ደብዳቤ የተመለከቱት የፍትሕ ሚኒስቴር ባለሥልጣናት ጥያቄው ተገቢ አለመሆኑን፣ ግለሰቦቹም የተጠረጠሩበትን የወንጀል ድርጊት ፍርድ ቤት ቀርበው በሚደረግ የግራ ቀኝ ክርክርና የሕግ ሒደት ብቻ የሚታይ መሆኑን በመግለጽ፣ ጥያቄውን ውድቅ እንዳደረጉት ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

እነ ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ የተጠረጠሩበት ወንጀል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የነበሩት አቶ አርከበ ዕቁባይ፣ አቅመ ደካማ ለሆኑ አባት አርበኞች የፈቀዱላቸውን 25 ኮንዶሚኒየም ቤቶች ለግል ጥቅም አውለዋል፣ ከሚያከራዩዋቸው ሕንፃዎች ከሚያገኙት ገቢ ላይ የአከራይ ተከራይ ግብር አለመክፈል፣ ያላግባብ ወጪ ማድረግና በመሳሰሉት ተጠርጥረው መከሰሳቸውን፣ ዋና ጸሐፊውና የአስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊው እያንዳንዳቸው በ25 ሺሕ ብር ዋስ መለቀቃቸውንና ፕሬዚዳንቱ ባለመቅረባቸው ታስረው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ መሰጠቱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ (ሪፖርተር)

5 Comments

  1. ጉድ፡በል፡ወይሀገሬ!መጫወቻ፡ት ሆኚ፡እንዲህነዉእንጅሽምግልና!በዚህሁኔታ፡ሀገር፡ሲያዘርፉ፡ከርመዋላ፡የተከበሩ፡ሽማግሌዎችማ፡በአመለካከታቸዉ፡በእምነታቸዉ፡ያለአግባብ፡የታሰሩ፡እንዲፈቱ፡አለመግባባት፡እንዲወገድ፡ጥረትያደርጋሉ፡፡እኝህ፡የዘራፊ፡ተባባሪ፡ለመደብ፡ትግል፡እንዲህ፡ነዉእንዴ?ወይስበየትኛዉ፡መንገድ፡ይሁን፡እንደአቂሚቲ፡ትግልትግልነዉአሉ?ሁሉምያቅሙንያንሳ፡”በአርበኛዉም”ስም ያስነሳ፡መሪእዲህ፡ሆነሳ?ሀገሬአበሳ

  2. if the allegation is true it would be great shame for the president . However the whole drama is to show how the judiciary system functioning free of government intervention (if at all there is government in this country)no more and no less. How come one in his right mind write official letter inquire for dismissal of the case unless it is the usual woyane’s gimmick .go and cheat your sheepish supporters and blindly guided followers.

Comments are closed.

Temam Ababulgu
Previous Story

“የሙስሊሙን አቋም ወክለው የሚናገሩት የታሰሩት የእኔ ደንበኞች ናቸው” አቶ ተማም አባቡልጉ

betty bba chase ethiopia
Next Story

በቤተልሄም የወሲብ ጉዳይ ‹‹ዴሞክራት›› ለመባል የፈለጉት አቶ አብርሃም ደስታ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop