እስራኤልን እንዳሰብክ ኢትዮንም አስባት (አዳነ መኮነን)

ግፍና መከራው ሲፈራረቁባት

እያየህ ዝም አትበል ተሎ ድረስላት
እስራኤልን እንዳሰብክ ኢትዮንም አስባት።
በዓለም ተበትነው ሲገቡ ከእስር ቤት
አንገታቸው ሲቀላ በሌላቸው እምነት
የፊጥኚም ታስረው ሲቃጠሉ በእሳት
ከፎቅ ተወርውረው ሲጣሉ ከመሬት
ይህነን እያየህ ምነው ጨከንክባት
እስራኤልን እንዳሰብክ እሷን አስባት
በተናገርከው፤ በቃልህ መሰረት።
እንጀራ ፍለጋ ከተሰደዱበት
ልጆቿን ሰብስበህ መልሰህ አምጣላት
ከሞት የተረፉትን የአሉትን በሕይወት።
እንደ በግ መታረድ ለክርስቲያን ሰው
ዛሬ አዲስ አይደለም ድሮም የነበር ነው
አባቶች አልፈዋል ሰማእ-ት ተቀብለው።
የውጭ ጠላትማ ጥንትም የነበር ነው
አሁን እያረደን ያለ የውስጥ አይሲስ ነው
ቆዳው እኛን መስሎ ልቡ ግን ሌላ ነው።
በአለፈው ዓመት መምህሩን ስትወስድ ተማሮች ትተሃል
እስከ መጨረሻው መቼም አይማሩ ደጋግመው ወድቀዋል
የንጉሦች ንጉሥ የኃያላን ኃያል
እነሱን አንስተህ አሳየን ዘንድሮ ክፍል አጣበዋል።
ቦታውም ይለቀቅ ለቆጠረ ፊደል
ለተማረ ሰው እውቀት ለሚያካፍል።
ተማሩ ተማሩ እያለ ህዝቡ ቢነግራቸው
ከማንስ ያዩትን ትምህርቱ ይግባቸው
ሃያ አራት ዓመት ተደፍኖ ልብና አንጎላቸው።
እጃቸውን ይዞ ሰው ሲያስተምራቸው
ትምህርቱን የሚያቁት ያኔ ነው ያኔ ነው
ከነሱም ሲደርስ ከሰው የደረሰው።
ጠላት አሰፍስፎ ዙሪያውን ቢከበን
የቅዱሳን አምላክ የአባቶቻችን
እኛን ይጠብቃል ሆኖ በጎናችን
የሚያስፈራን የለም እግዚአብሔር አለልን።
እኛ አንጠብቅም ከሰዎች እርዳታ
አለልን ፈጣሪ ችግር የሚፈታ
እልል በይ ኢትዮጵያ በትንሣኤ ለታ
አንችን ለመቀደስ ሊመጣነው ጌታ።
ከትቢያው አንስቶ ዙፋን ላይ ሊያስቀምጥሽ
መላእኩ ይመጣል ምስራች ሊያበስርሽ
ጥቁሩን አውልቂና ነጩን ልብስ ልበሽ
ከፍ ብለሽ ተቀመጭ ዓለምም እንዲያይሽ።
ኢትዮጵያ ሀገራችን ወድቀሽ ትነሻለሽ፤
ልክ እንደ እስራኤል አችንም አይረሳሽ፤
ጠላትሽን አጥፍቶ አንችን ይባርካል፤
የፈጠረሽ አምላክ የኃያላን ኃያል።
ግንቦት፤፯ቀን፡ ፪ሺ፯ ዓ/ም (15/05/2015)

ተጨማሪ ያንብቡ:  UN: 9 million need aid in drought-hit East Africa
Share