May 26, 2013
2 mins read

በጄ/ል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ በሚኒሶታ ሕዝባዊ ስብሰባ ጠራ

olf ethiopia

(ዘ-ሐበሻ) በብርጋዲየር ጄነራል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ ዓመታዊ ስብሰባውን በሚኒሶታ ጁላይ 7 ቀን 2013 እንደሚያደርግ ለዘ-ሐበሻ በላከው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቀ። ድርጅቱ ጁላይ 7 በሚያደርገው ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ዘርና ጾታ ሳይለይ ማንኛውም ኢትዮጵያውያን እንዲታደሙ ጋብዟል።
ድርጅቱ በላከው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የዘንድሮውን ስብሰባ ልዩ የሚያደገውን ምክንያት ሲገልጽ “ይህንን ስብሰባ ካለፉት ልዩ የሚያደርገው ማንኛውንም ኢትዮጵያዊ ወይም ብሔር እና ብሔረሰቦች እንዲሁም ሕጋዊ ከሆኑ ተቃዋሚዎች ጋር በመተባባር የወደፊት የኢትዮጵያን ህልውና እውነተኛ የዲሞክራሲ የሕግ በላይነት የማንኛውም ግለሰብና ድርጅት መብት የሚከበርባት አገር ለመመስረት እንደሆነ ከኦነግ የፖለቲካ ለውጥ መረዳት ይቻላል” ብሏል።
“በዚህ ስብሰባ ላይ የሚገኙ ፡ የሐይማኖት አባቶች ፡ የፖለትካ ድርጅቶች ፡ መካሪ አዛውንቶችና ፡ ታዋቂ ግለሰቦች በወቅታዊ ኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ ለመመካካር በዚሁ ታሪካዊ ጥሪ ላይ ይገኛሉ፡፡” ያለው ኦነግ “ስለዚህ ፡ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ፡ ይህ ጉዳይ ይመለከተኛል የሚል ሁሉ ጁላይ 7 2013 ከቀኑ 1፡00 ፒኤም እንድገኙልን በትህትና እንጋብዛለን። ብሏል።
በብርጋዲየር ጀነራል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ ሕዝባዊውን ስብሰባ የሚያደርግበት አድራሻ የሚከተለው ነው።
አድራሻ : Best Western / Kelly Inn
161 St. Anthony Ave.
St. Paul , MN , 55103

July 7 , 2013 @ 1:00 Pm
አዘጋጅ ኮሚቴ
ጁላይ 7 የኦሮሞ ሰሜን አሜሪካ የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል በሚኒሶታ የሚደረግበት ሰሞን በመሆኑ ከሌሎች ስቴቶች እና ሃገራት የሚመጡ እንግዶች በዚህ ስብሰባ ላይ እንዲታደሙ እድሉን ይፈጥርላቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።

7 Comments

  1. Thank you. This is a big blow for weyane.
    HUMANITY BEFORE ETHNICITY
    NO ONE IS FREE UNLESS WE ALL ARE FREE
    One question, sure many non-ormo Ethiopians will come to the meeting, what about the language?? If it is all in Oromifa, how can we follow the meeting? Just for clarification

    • ante demo yechegerew erguz yagebal honobik new! ye honk mededenja nehe! ebaik ene alimetam-keweyane gar sitseru koyetachu ahun demo yazunge likekunge tilalachu! Demo ye oromo netsa awiche hono manjawim ethiopiawi nuna tademu yilal ende-sintu maferiya ale bakachu-enja masgentelun weyim netsa mawitatun endinagizik new? ewnetem geltu nehe!

  2. Belu sabaara iqaa sebsibu. min inde miyamexu inaayalen.

    Inde Fiyel iqaa baadoachewun yeqeru.

  3. We should all move to forming a united front. Ethnic based organiation, concerned only on issues of one ethnic group cannot lead the Ethiopian people of 80 different ethnic groups.

    Simply copying Tigre people liberation front and forming ethnic organisations is the same as treading on the same failed ideology. Tigre liberation front created ethnic organisations not out of good will but as a tool to divide and rule the population by causing and inciting inter-tribal inter ethnic rivalries and divisions and eventually tribal and ethnic wars.

  4. hahahaha
    ye oromo tagaye hono manijawim ethiopiawi yisatef yilal-enja ye ante ahya nene? litgaliben feligek new-sintu kizebe ale ebakachu! ye ethiopia netsa awiche bilek tenkesakes ena gabezen!

Comments are closed.

ali birra
Previous Story

የአሊ ቢራ 50ኛ ዓመት የሙዚቃ አገልግሎት ሊከበር ነው

Next Story

ዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 51 (PDF)

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop