“ሁለቱ ታላላቅ ዕቅዶች” ክፍል 3 (ዮፍታሔ)

በመጀመሪያዎቹ ሁለት ክፍሎች ከ1983 ዓ.ም ወዲህ ጎሳን መሠረት በማድረግ ከተዘጋጁ ሁለት የተለያዩ “የኢትዮጵያ ካርታዎች”  በመነሣት የሕወኀት ሁለቱ ታላላቅ ዕቅዶች ተጠቅሰዋል። የመጀመሪያው ከትግራይ ክልል ጋራ የቤንሻንጉል ጉሙዝና የጋምቤላ  ክልሎችን በመቀላቀል ከኢትዮጵያ ተለይቶ አገር መመሥረት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ይህን ለማስፈጸም ከፍ ያለ ግጭት በቀሪዎቹ  የኢትዮጵያ ጎሳዎች (ይልቁንም በአማራና በኦሮሞ ጎሳዎች) መካከል መቀስቀስና እነዚህ ቀሪዎቹ ጎሳዎች ዕቅዱ እንዳይፈጸም፤ ቢፈጸምም  እንዳይዘልቅ በማድረግ ሊኖራቸው የሚችለውን ተጽእኖ ማስወገድ ናቸው። ከካርታዎቹ አንዱ መነሻ ቢሆንም የመጀመሪያውን ዕቅድ  ለማስፈጸም በትግራይና በሁለቱ ሌሎች ክልሎች እስካሁን የተደረጉና እየተደረጉ ያሉ ሌሎች ዋና ዋና ዝግጅቶች በአጭሩ ተጠቅሰዋል።  የአፋር፣ የጅቡቲና የሱዳን አስተዋጽኦ ምን ሊሆን እንደሚችል በአጭሩ ቀርቧል። ሁሉም መንገዶች ወደአንድ መድረሻ የሚወስዱ ሆነው  ይታያሉ። የሁለተኛው ዕቅድ በገሀድ መከናወን እንደጀመረ የሚያሳዩ ድርጊቶች ከመቸውም ይልቅ ዛሬ ለሁሉም ግልጽ ናቸው።–— [ሙሉውንለማንበብእዚህይጫኑ]—-

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  ብአዴን ሆይ! ነፍስ ይማር!!

3 Comments

Comments are closed.

Share