June 22, 2014
2 mins read

አንድነት ፓርቲ በሀዋሳ ሊያደርገው የነበረው ሰልፍ አመራሮችንና አባላትን በማሰር ከተማዋን በፀጥታ ኃይሎች በመውረር ተደናቀፈ

10478183 742597102465708 4057302345624676295 n
(ፖሊስ ትናንት የአንድነትን ሰልፍ እንዲበተን ያደረገው እንዲህ ከተማዋን በመውረር ነበር)
በዛሬው ዕለት በአዋሳ ከተማ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በሀዋሳ ከተማ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ በቅስቀሳ ላይ የነበሩ የፓርቲው አባላት ከሐሙስ ዕለት ጀምሮ እስከ ትላንት ድረስ ከ30 በላይ በፖሊስ የታሰሩ ሲሆን የሲአን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለገሰ ላንቃሞ ለምን ይታሰራሉ ብለው በመጠየቃቸው እሳቸውንም አስረው ከምሽቱ 3፡30 ለቀዋቸዋል፡፡ በቅስቀሳው ወቅት ወረቀቶች የተበተኑ በመሆኑ ህዝብ በነቂስ ሊወጣ እንደሚችል ስጋት ያደረባቸው የደህዴን ካድሬዎች ትላንት ማታ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ተጨማሪ 7 የአንድነት የሀዋሳ አመራሮችና አባሎች በቁጥጥር ስር አውለዋል፡፡ የደቡብ ክልል የደህዴን ካድሬዎች ከተለቀቁ ነገ ሰልፉን ከማድረግ ወደኋላ አይሉም በሚል ለሁለት ተከፍለው ሲሟገቱ ማምሸታቸውንና አቶ መንድሙ ወታንጎ የተባሉት የደህንነት ኃላፊ መፈታት የለባቸውም መፍታት እንኳን ካለብን የሰልፉ ሰዓት ካለፈ በኋላ ነው በማለታቸው በእስር ቤት እንዲያድሩ መወሰኑና በዛሬውም ዕለት የሀዋሳ ከተማ በፀጥታ ኃይሎች ከፍተኛ ጥበቃ ሥር መሆኗን የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ገልፀዋል፡፡

 

 

819f5b6eb52350a170986a3670177bfb L
Previous Story

ከአሥር ወራት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ያጡ የፍቼ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሠልፍ ሊወጡ ነው

Next Story

ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ተይዘው በቂሊንጦና ቃሊቲ የታሰሩት ፈቲያና ያሲን በወህኒ ቤት ተሞሸሩ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop