ይናገረው ዘመን – ይዳኘው መንገዱን! (ሥርጉተ ሥላሴ)

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ

ከሥርጉተ ሥላሴ 20.06.2014 (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

…. ለቀጣዩ ቀናት

…. ውል ብሏል ለ

…. ሽውታ ለናፍቆት

              ሕትምት!

አደራውን ልኳል

ወገኑን – ተማምኗል

አርበኝነት ሆኗል፤

           ተጥዷል!

የብዕር አባቱ

80 ነው ባቱ

ብራና እትብቱ

ትህትና ነው ቤቱ

          በኽረነቱ!

የቁምነገር ሃብቱ

ፍልስፍናው በርቱ!

ጽናቱ – ስበቱ

ትዕግስቱ – ውበቱ

ማሰብ ነው ዕለቱ

ቀን – ተሌት፣ –  ህብስቱ፤

ተስፋ  – ማ –  ሟተቱ

ያሥራቱ!

ይናገረው – ዘመን

ይዳኘው – መንገዱን፤

ይሄው ነው ዕውነቱ፤

ድርጊት ባለቤቱ

          ችሎቱ!

የግንባር ሥጋ ነው

ለሃቅ ያደረ ነው።

መሠረተ – ህብር

የሥጦታው – ደንበር

የመከራ ገበር።

ጥማቱ …

ፍጥረቱ —

ፈቅዶ – ህማማቱ

ፍቅረ – መለኮቱ

ህይወቱን – ለናቱ

ውስጡን – ለልዕልቱ

           መክሊቱ!

አልፋ ነው መለከት

ኦሜጋማ – ስብከት

             አብነት!

ተግባሩ ነው ልፍል

ፏፋቴ ለፈል

ተናግሮታል ወለል

ዓለም መስክሮታል፤

መንፈስ – መዝኖታል

ምርጥ ሰው ብሎታል።

ሰማይም ሰጥቶታል

ቀድሞ ቀብቶታል፤

ሁሉን ሽልሞታል

ቅብዕ —– ሰክኖለታል!

                                                  ለአባ ትርጉም ለጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የእንኳን ደስአለህ ሥጦታ፤ 19.06.2014 ዙሪክ ሙዚዬም – ፓርክ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኢትዮጵያዊያን ቆም ብለን የምናስብበት ወቅት ዛሬ ነው - መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

1 Comment

  1. በነካካ የግጥም እጅሽ ለጨካኞቹ የወያኔ መሪዎችም መረገመ መቅሰፍቱን አውርጂባቸው የኛ ቆንጂት ኢትዮጵያዊት።

Comments are closed.

Share