August 3, 2011
2 mins read

ተስፋ (ከዘላለም ገብሬ)

በሃሳብ ተኝተሽ
ሃሳቡን ጸንሰሽ
ጽንሱን አሳድገሽ

የሃሳብ ልጅ አርገሽ

እርግዝናው ሞቆሽ እናትነት ሰቶሽ

የእናትነት ፍቅርን ሃሳብ አስረክቦሽ

ጭንቅ ብሎሽ እርግዝናው ከብዶሽ

መራመድ አቅቶሽ

መውለጃሽ ሲቃረብ

ምጡ ሲጠናበሽ ጩኽትሽ በርትቶ

መውለድም ሲከብድሽ

ተወለድ! አልወለድም ክርክሩ ገጥሞሽ

የእናትነት ጥማት ልጅሽን ተጠምተሽ

የተስፋ ልጅ ይዘሽ ከቶ ማያገኙት

ወልደው የማያዩት ምጡንም አመጠው

በሃሳብ ተክዘው በጭንቀት ተጠበው

የተስፋ ልጅ ይዘው

ነገን ተስፋ አድርገው

በተስፋ ላይ ታዝለው

ተ…….ስ……ፋ…. እያሉ ሲያቆለጳጵሡት ሲያሞጋግሱት

እውነት ህይወት መስለሽ እንዲህ ያደረገሽ

የነገን ሰንቆ ዛሬ ህልም አስይቶሽ

ባዶነት መኖሩን ምኑንም ሳይነግርሽ

ልብሽን ወጥሮ አእምሮሽን ሰብሮ

በደስታ ፍሬ የዘርፍሬ አጭደሽ

በተስፋ ማእበል የህልም ጉዞ ሄደሽ

መቼም ላትመለሽ አስፍሮ አስኮብልሎሽ

በባዶ ሜዳ ላይ ይሄው አንጓሎ ጣለሽ !

ተስፋ `ያሉ ሚሉት ካንቺው ጋር ተጣብቶሽ

ከአንቺው ተወልዶ

አንቺን አስጨንቆ በምጥ አሰቃይቶ

የነገን ላትኖሪ በነገ ተስፋ ነገን አሳይቶሽ

ተስፋ

ይህ ጽሁፍ የተጻፈው ለሜሮን አባተ ለጻፈችው የግጥም ጽሁፍ መልስ ስለሆነ እሱዋን እንድጽፍ ስላደረገችኝ አመስግኑልኝ !

Previous Story

‹‹99.9% አሰልጣኞች የባርሴሎናን አጨዋወት ለመቅዳት እየጣሩ ነው›› ሉዊስ ሴዛር ሜኖቲ

28691
Next Story

ለእማምዬ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop