June 7, 2011
2 mins read

ዩናይትድ ኤንሪኬን ፈልጎታል

ethiopia coffe and st george

ማንቸስተር ዩናይትድ የኒውካስል ዩናይትድን የግራ መስመር ተከላካይ ሆዜ ኤንሪኬን ለማስፈረም ከሊቨርፑል ጋር ትግል ለማድረግ ቆርጧል፡፡ የሜርሲሳይዱ ክለብ ደጋፊዎች አሰልጣኝ ኬኒ ዳልግሊሽ ስፔናዊውን ተጨዋች እንደሚያስፈርመው እርግጠኛ ሆነዋል፡፡ ሆኖም ሰር አሌክስ ፈርጉሰንም ወደ አንፊልድ ያቀናል የሚለውን ዘገባ ያስተባበለውን ተጨዋች እየተከታተሉት ይገኛሉ፡፡ ባየር ሙኒክም 15 ሚሊዮን ፓውንድ የተገመተውን የ25 ዓመቱን ኤንሪኬ በቻምፒየንስ ሊግ የሚያሳትፈውን ዕድል እንደሚያቀርብለት ገልፆለታል፡፡ ኤሲ ሚላኖችም ኒውካስል በ2007 ከቪያሪያል ላይ በ6.3 ሚሊዮን ፓውንድ ያስፈረመው ተጨዋች አድናቂ ናቸው፡፡ ምንም እንኳን የ30 ዓመቱ ፓትሪስ ኤቭራ በኦልድ ትራፎርድ የሚቆየውን አዲስ ኮንትራት ቢፈርምም ፈርጉሰን በኤንሪኬ ላይ ያላቸው ፍላጎት አልቀነሰም፡፡ የኒውካስሉ አሰልጣኝ አለን ፓርዴው ግን ከክለቡ ጋር ተጨማሪ የአንድ ዓመት ኮንትራት የሚኖረው ተጨዋች በሴንት ጀምስ ፓርክ እንደሚቆይ ገልፀዋል፡፡ ይሁን እንጂ እንደ ፒፕል ዘገባ ተጨዋቹን ከአሁኑ እንደሚያጡት በመፍራት ለፈረንሳይ ከ21 ዓመት በታች የሚጫወተውን የ22 ዓመቱን የቱሉዝ ተከላካይ ሼይክ ምዜንጉዋን በተተኪ እጩነት ይዘውታል፡፡

samuel etoo
Previous Story

Ethiopia 2 Nigeria 2, Saladin Seid scored twice

Next Story

ከአቶ ገብሩ አስራት ጋር አጭር ቆይታ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop