ባለፈው ሰሞን ጠ/ሚ አብይ አህመድ የጅብ ቆዳ እጃቸው ላይ አድርገውና የጅብ ግልገል ይዘው እይዞሩ የሚዋጉ የፋኖ ኃይሎች መኖራቸውን ነግረውን ነበር፡፡ ምክነያታቸው ደግሞ ጅብና ቆደው ጥይት እንዳይመታቸው ለመከላከያነት ይሆናል ብለው በማመናቸው እንደሆነ ጠ/ሚሩ ገለጻ ሰጥተውበታል፡፡ጠ/ሚ ጠላት ብለው ያመኑባቸውን ሁሉ ከጅብ ጋር የማያያዝ አባዜ አላቸው፡፡ የትግራዩ ጦርነት ሲጀምር ህወሀቶችን ከቀን ጅቦች ጋር አያይዘው ይናገሩ ነበር፡፡
እኝህ ሰው ከጅብ ትርክት አለመላቀቃቸው ምስጢሩ ምንድን ነው ብይ ስመረምር በልጅነቴ የሰማሁት ተረት ትዝ አለኝ፡፡ አይ ጅቦ ሁለት ወንድና አንድ ሴት ልጅ ነበረው አሉ፡፡ ስማቸውም፣ መዥሩጥ( ቦጭቅ)፣ ማንሾለላ(አውካኪው)ና ዘርማጭት ይበላሉ፡፡
በጅብ አለም በተለይም በእኛ ሃገር በብዛት የሚታወቀው ቢጫ ዳለቻማው በለጥቁር ቡናማ ነቁጥማው ጅብ በመላ ሃገሪቱ በብዘት የሚገኝ የጅብ ዘርያ ነው፡፡ በአስራዎቹ ከፍ ሲልም የዛን አምስት ስድስት እጥፍ የሚደርሰውን የጅብ መንጋ ጎሳ ሲኖረው በትናንሽ ቡድን ይዋቀራል፤ መሪዋ ግን ሴት ነች፡፡ ይህች ሴት ጅብ ከወንዱ በክብደት እስከ 20 ኪ.ግ ድረስ የምትበልጥና ልክ ከወንዱ ጋር ተመሳሳይ የሆነ መራብያ ብልት ያላት ናት፡፡ በዛው ትሸናበታለች፡፡ ታዲያ ነገርዬው ልክ እንደወንዱ ሁሉ የሚቆም ነው፡፡
ለዚህም ይመስላል በአንዳንድ የሃገራችን ክፍል ጅብ እንደወቅቱ ውንድም ሴትም መሆን የሚችል ፍናፍንት ነው ተብሎ የሚታመነው፡፡ የአያ ጅቦ ሴት ልጅ ዘርማጭት የስሟ ትጉምም ይህን የሚያሳይ ነው፡፡ ዘረመጠ-ዘረመጨ ማለት ሰረረ፣ በኃይል አስገባ፣ ወጋ ማለት ነው፡፡ ስለዚህም ሴቷን ዘርማጭት ይሏታል፡፡
የዚህች የዘርማጭት ጅብ የሚቆመው ብልቷ ወንድ ያገኘች ሲመስላትና መራባት ስትፈልግ ሽቅብ በቁመቱ ልክ ወደ ውስጥ ታጥፎ ይገባል፡፡ በዚይም ግንኙነት ትፈጽማለች፡፡ ነገር ግን ሁል ግዜ የጅቡን መንጋ የምትመራው እሷ ነች፡፡ ወንዱ በአመራር ላይ ፋይዳ የለውም፣ መንጋው እማዊ ነውና፡፡
የጠ/መሩን የጅብ ትርክት ልክፍት ለመረዳት ነገሩን ከሰነልቦና፣ሃይማኖት፣ማህበራዊ ውቅርና ስነሰብ…መመለከት ተገቢ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ገጠርም ይሁን ከተማ ነዋሪ ህዝብ ጋር በቅርበት የሚኖሩ አደጋኛ አራዊቶች አሉ፡፡ ከነዚህ መካከከል ነብርና ቀበሮን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ነገር ግን እንደ ጅብ አሰጊ የሆነ የለም፡፡ ሰለዚህም በተለያዩ ባህሎች ውስጥ ጅብን በተመሳሳይ ታሪኮችና አባበሎች ሲገለጥ ይታያል፡፡ጅብ የቤት እንስሳትን እንዲሁም ሰውን በተለይም ህፃናትን በማጥቃትና በመብላት ይታዋቃል፡፡
በሰነልቦና ቀውስ ውስጥ ውስጣችን ሰላም የሚነሳ ተቀርኖ ሲኖረን ምቾት ከማይሰጠንና ፍርሃትን ከሚለቅብን ሃሳብ እራሳችንን ለማራቅ ሳናውቀው በድብቁ ህሊናችን ክፍል የምንፈጥረው እራስን የመከላከል ሂደት አለ፡፡ ይኸውም ፍሩዳውያኑ ሪአክሽን ፎርሜሽን( Reaction Formation Defense Mechanism) ብለው ይጠሩታል፡፡
በዚህ ረገድ አንድ ሰው በውስጡ እራሱ ሆኖ የሚሰማውን ነገር በውገዘት መልክ ሲገልጸው ይሰማል፡፡ ጠ/ሚ አብይም እራሳቸውን ጅብ ሆነው ያገኙት ይመስላል፡፡ ይኸው በሃገሪቱ ውስጥ እየዞሩ ሰው ይበላሉ፣ ይጨርሳሉ፡፡ በተለይም በትግራይና አማራ ክልሎች በደሮን የፈጇቸውን ህፃናትን ቤታቸውና እናቶቻቸው ይቁጠሯቸው፡፡
እሳቸውስ ቢሆኑ ያለ ባህላቸው ወንደ መሪ ያገኙ ሲመስላቸው እንደ እማ ጅቦ-ዘርማጭት ያሽኮረምማቸውስ አይደል፡፡ ይህንን ለፕሬዚዳንት ኢሳያስ ቀለበት ሲያጠልቁና የኤሜሬት ሼኮች አንገት ስር ሲልወሰወሱ ተመልከተናል፡፡ የዘርማጭት መንፈስ ይሉሃል ይሄ ነው፡፡ ጅብ እንደ አንበሳ የሚፈራውና የሚጠላው የለውም፡፡ በየሳፈሪው ፓረክ ወገቡን ሰብሮ ሲጥለው ይታያልና፡፡ ጠ/ሚ አብይም በእርካብና መንበር መጽሐፋቸው ” ሞዐ አንበሳን…” እነዴት አድርገው እንደሚጠሉት አስነብበውናል፡፡
የጅቡ ትርክት ሃይማኖተዊ ገጽታው ደግሞ የሚገርም ነው፡፡ ጠ/ሚ አብይ የሆሳዕናን በአል አሰምልክተው የሰሩትን ንጽጽር አየሁና ምነው በኤአይ የተቀናበረ በሆነ ነው ያልኩት፡፡ እንደው አመት በአል በመጣ ቁጥር ብልጽግናን ቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ እራሳቸውን በክርሰቶስ ቦታ እየተኩ ሲተርኩልን ከረመውልን አይደል መቼ ይህ ይገርማልና እንዳትሉኙ፡፡
ጠ/ሚሩ ክርስቶስን በሆሳዕና እለት ስለተሸከመችው የአህያ ውርንጭላ ነበር የሚተርኩት፡፡ ያው እንግዲህ ሆሳዕና ከለፈ በኃላ ክርሰቶስ የለምና ውርንጭላይቱም ወደ ቤቷ ተመለሰች ፡፡ አብይ እነደነገሩን ከዚያም ያገኘ ሁሉ ይዠልጣት ጀመር፡፡ ምንድን ነው የአመት በአሉ ግዜ ክብር ሰጥታችሁኝ አልነበረም? ዛሬ ምን ተገኝቶ ነው ይሄ ሁሉ ዱላ ብላ ውርንጭላይቱ ብትጠይቅ፣ በላይሽ ላይ ተቀምጦ የነበረው ክብርሽ የለምና ብለው መለሱላት፡፡ እንግዲህ የአህይት ትርክት ከእራሳቸው ከጠ/ሚ አብይ የተቀጠለ ፈጠራ እንጂ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ሰለ ውርንጭላይቱ የሚያወራ ታሪክ የለም፡፡
መቼም ይህንን ታሪክ ከመተረካቸው በፊት ለዚያ ድርሳንና ገድል ጸሐፊያቸው ሳያማክሩት አይቀርም፣ እንደውንም የታሪኩ ደራሲ እራሱ ዲ./ን ዳንኤል ተብዬው ሳይሆን አይቀርም፡፡ ክርስቶስን ዛሬ አየሁት ብሎ ሰለእሳቸው ጽፎላቸውስ አልነበረም፡፡ እንደ ጠ/ሚ አብይ ሃተታ ከሆነ ደግሞ ውርንጭላይቱ ብልጽግና ነች፡፡ ክርስቶሱ ደግሞ እሳቸው ናቸው፡፡ እኔ ከሌለው ብልጽግና ትዠለጫለሽ ብለው ነው እንግዲህ በግልጽ የተናገሩት፡፡
ትንቢት ነገርን ይቀድማል እንዲሉ አበው፣ እውነት ነው የብልጽግና ክርስቶስ አብይ ናቸው፡፡ ይሞታሉ ግን ትንሳኤ የላቸውም፡፡ ክርስቶስ፣ ክርስቶስን መጫወት ይቻላል ይሆናል ግን እሱን መሆን አይቻልም፡፡ መቼም ጠ/ሚ በድርሳናቸው ውስጥ እንዲካተት የተረኩልን የውርንጭላይቱ ታሪክ በፍየል ብራና ላይ ይጻፍላቸዋል ብለን አንጠብቅም፡፡ ያው ውርንጭላይቱን ለመበላት አውው… ባሉበት የዘርማጭት አፋቸው በጅብ ቆዳ(ብራና) ላይ ይጻፍላቸው እንደሆን እንጂ፡፡
ዲ/ኑ(?) ከታቢያቸው መቼም ይህንን ድርሳን ሲጽፍ አንድ ነግር እንዳይረሳ ላስታውሰው አፈልጋለሁ፡፡ የሆሳዕና እለት ህጻናት “ሆሳዕና በአርአያም…” ብለው ዘምረው ነበር፡፡ “ከህጻናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ…” ተብሎም በወንጌል ተነግሯል፡፡ ዛሬ ግን የአማራ ክልል ህጻናትን አንደበት አብይ አህመድ በድሮን እሰከወዲያኛው ዘግተውታል፡፡ የትግሬውንም እንዲሁ፣ እግዚአብሔር አያድርገው እንጂ የኤርትራውያኑም ይቀጥላል፡፡ ዘርማጭት ሴሜናዊ አግአዚያንን ሳታጠፋ መቼ እፎይታ አላትና፡፡ ምናልባት ጠቅላዩ ከፋኖ ጋር የጅብ ትርክት አተካራ ውስጥ የገቡት ልጄን ቀሙኝ፣ ብራናዬን ወሰዱብኝ ብለው ይሆንን? ዘርማጭት!
ክርስቶስ ክርሰቶስን ሲጫወቱ የምናያቸው አብይ ህጻኑ ክርሰቶስን ፍለጋ በቤተልሄም ህጻናትን ከፈጀው ሄሮድስ ጋር የሚመሳሰሉ እንጂ ሌላ ሊሆኑ አይቸሉም፡፡ በቅኔ ቤት አምለክን እንደ ሰው አድርጎ መቀኘት ይቻላል፡፡ ምክነያቱም አምለክ ሰው ሆኗልና፡፡ ሰውን ግን አምላክ መድረግ አይቻልም፡፡ ዛሬ ጅብ ትርክት ውስጥ የከተቱት ጎጃም ፤ ዋሸራና ጎንጅ ይህን ነው የሚስተምረው፡፡ ዳንኤል ግነ ይህንን መሰረታዊ እውነት ከጌታው ፀረ ክርሰቶሱ አብይ ጋር ክዷል፡፡
ሌላወ የጥላቻ ንግግርና ሁን ብሎ አንድን ማህበረሰብ ኢላማ የመድረግ ነገር ነው፡፡ ይሄ በደቡብ አፍሪካ በአዘፓርታይድ ግዜ የተሰራበትና ከዚያም ወዲህ ቀጥሎ ያለ ነው፡፡ አፓርታይድ ከለርድ ተብለው የሚታወቁትን ህዝቦች በሶስተኛ ዜግነት ከጥቁሮቹ በላይ የሚያደርግ ስለ ነበር ጥቁሮቹ ከለርድ ሰዎች የጀርባ አጥን የለሾች፣ እባቦች ናቸው ይሏቸው ነበር፡፡ ይህ ነገር ተደጋግሞ በመነገሩም በእውነት ከለርዶች ሰዎች አይደሉም ብለው የሚያምኑ ጥቁሮች ነበሩ፡፡
ጠ/ሚ አብይ አህመድ ሁን ብለው አቅደውና አስልተው የአማራ ፋኖ ኃይሎችን ከመናፍስት አሰራር ጋር አያይዘው ሲናገሩ ባህላዊ አግባቡን ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ በተለምዶ ጅብ የሚጋልቡ ተብለው ከሚታወቁት ቡዳዎች ጋር ፋኖን ማገናኘት ፈልገው ነው፡፡ ይኽ ደግሞ ከሩዋንዳው ኢንተርሃሞይ ቱሲዎቹን በሁቱዎች ላማስጨረስ በረሮዎቹን ግደሏቸው ቅስቀሳ በምንም አይለይም፡፡ ለሳቸው ተከታዮች በተለይም ለጴንጤዎቹ የሚተላለፈው መልእክት ውጊያው የጅብ መናፍሰቱን ይዞ ከሚጓዘው ሴይጣናዊው ፋኖ ጋር እንደሆነና ምህረትም እንደማይገባው ነው፡፡
የአራት ኪሎው መንግስት ህጻናትን የሚፈጀው ጅብ እሱ ሆኖ ሳለ ለእኩይ አላማው ህዝብን በህዝብ ላይ ለማስነሳት በተለይም ከክልሉ ውጭ ያለውን አማራ ከጅብ ጋር አቆራኝቶ ኢላማ በማስደረግ የዘር ፍጅት ቅስቀሳ እለት እለት ሲያውጅ ይገኛል፡፡
ይህ በስልጣን ላይ በፍጹም መቀጠል የሌለበትን ቡድን በሚገባ ተረድቶ አማራውም ሆነ ሌላው ኢትዮጵያዊ ወግድ ማለት አለበት፡፡ ዛሬ በዚህን ደረጃ እነ ጠ/ሚ ዘርማጭት በአማረው ላይ የከፈቱትን ዘር ማጥፋት ሌላው ኢትዮጵያዊ ችላ ብሎ ካየው ነግ በኔ ነውና በህብረት ልንታገለው ይገባል፡፡
አስቻለው ከበደ አበበ
ሜትሮ ቫነኩቨር፣ ካናዳ