መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ
ዛሬ እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር ጥር 1ቀን 2025 ዓ/ም ነው ። አውሮፓውያኑ አዲስ ዓመትን “ሀ” ብለው ጀምረዋል ። አዲሱን ዓመት ሲጀምሩም ከልክ ባለፈ ፈንጠዚያ ነው ። ርቺቱ ፣ ምጉቡና መጠጡ ብቻ ሳይሆን ሰዎቹ እራሳቸው ፣ እንደክሪስሜስ ዛፍ አሸብርቀው ፣ አምረው ና ተውበው ፣ ወርቅ መስለው ፣ ዝንጥንጥ ብለው በደስታ እየተፍከነከኑ አዲስ ዓመትን ተቀብለዋል ። ይህንን እውነት ዕድሜ ለሶሻል ሚዲያ በቀጥታ ሥርጭት አይተናል ። እርግጥ ነው በእኛው ሻራተንም ” በ20ሺ ብር ብቻ መፈንጠዝ ተችሏል ። ” ማን ከማን ያንሳል ? …
ሰው በመሰረቱ በቀላሉ የሚደሰት እና በቀላሉ የሚያዝን ፍጡሩ ነው ። ፍንጥዝያና ጭምትነት ፤ ለቅሶና ሳቅ ደግሞ በጉያው ያሉ የስሜት ነውጦቹ ናቸው ።
እነዚህ የስሜት ነውጥች ዘወትሮዋዊ ቢሆንም በአውሮፓው ዜጋ እና በአፍሪካው ዜጋ የሚስተዋለው የስሜት ነውጥ ግን በእጅጉ ይለያያል ።
አውሮፓዊው ዜጋ የስሜት ነውጡ ፤ ፈንጠዝያው ና ሐዘኑ ከመንፈስ ደስታ ከማግኘት ጋር የተቆራኘ ነው ። በአመዛኙ ። አፍሪካዊው ደግሞ ሐዘኑ እና ፈንጠዝያው የተቆራኘው ከዕለት ጉርሱ ከአመት ልብሱ ጋር የተቆረኘ ነው ። ያ ማለት አፍሪካዊው ገና መሰረታዊ ፍላጎቱን ያላረካ ምስኪን ሰው ነው ማለት ነው ። ለመሆኑ ይኽ ምስኪንነት ከፍ ሲል ደሞ ምንዱባንነት ( ዘመን በአዲስ እየተቀየረ የትየለሌ ደርሶ እንኳን ) እስከዛሬ እንዴት ሊቀረፍ አልቻለም ?
ይኽ ጥያቄ በጥበብ የሚመለስ ጥያቄ ቢሆንም በዋነኝነት ፖለቲካዊ ምክንያት አለው ።
መቼም የፖለቲካ ሳይንቲስቶች እንደምታውቁት ዓለምን የሚገዛው ፖለቲካ ነው ። ፖለቲካ የህዝብ የአስተዳደር ዘይቤ ነው እስካልን ድረስ ኢኮኖሚውንም ሆነ ማህበራዊ ጉዳዩን የሚያሽከረክረው እርሱ ነው ። ይላሉ የዘርፉ ልሂቃን ። )
እርግጥ ነው አለምን የሚገዛው ፖለቲካ ነው ። ይሁን እንጂ ይህ ገዢ ፖለቲካ ፈጣሪ እንዳለው አንዘንጋ ።…
“ፖለቲካው ዓለምን ይገዛል “ ስንል የፖለቲካ ፈጣሪዎች የፖለቲካውን መሪ ይቆጣጠራሉ ። እነሱ እንዳሻቸውም ይዘውሩታል ። እንደፈለጋቸውም ያሽከረክሩታል ማለታችን እንደሆነ ይሰመርልን ።
ለመሆኑ እነዚህ የፖለቲካው ዘዋሪዎች እነማን ናቸው ? መልሱ ግልፅ ነው ። በኢኮኖሚ የፈረጠመ አቅም ያላቸው አገሮች ሁላ ናቸው ።
አሜሪካ ፣ ቻይና ፣ ሩሲያ ፣ እንግሊዝ ፣ ጀርመን ፣ ፈረንሳይ ፣ ኢጣሊያን ፣ ሳውዲአረቢያ ፣ እስራኤል ፣ …ቱርክ ። ወዘተ። የፈረጠመ የኢኮኖሚ ያላቸው ናቸው ።
እነዚህ አገራት ለሀገራቸው የሚጠቅም ፖለቲካን በዴሞክራሲ ፣ በ’ሪኦተ ዓለም እና በኃይማኖት ሥም በአፍሪካ አገራት ላይ ያራምዳሉ ።
ፓለቲካቸውን የአፍሪካ መንግስታት ተቀብለው እንዲተገበሩም በሞኖፖል በያዟቸው የኢኮኖሚና የኃይማኖት ተቋማት አማካኝነት እጅ ይጠመዝዛሉ ። ( ወርልድ ባንክን እና አይ ኤም ኤፍን መጥቀስ ይቻላል ። )
ይህ ብቻ አይበቃቸውም ፣ ህዝቡም በአጠቃላይ እውቀት እንዳይበለፅግ አንድ መግባብያ ቋንቋ ኦንዳይኖረው ያደርጋሉ ። አንድ አይነት ፍጡር ፤ ያውም ክቡር ሰው ሆኖ እያለ በሚነገረው ቋንቋ እንዲጠራ በማድረግ ሰውነቱን ያስረሱታል ። እርስ በእርሱም እንዳይገባባ በቋንቋው ብቻ እንዲማር ያስገድዱታል ። ብሔራዊ ቋንቋ እንዳይኖረው ያደርጉታል ። ወደ 14ኛው እና 15ኛው ክፍለ ዘመን የወረደ አስተሳሰብን የሚያራምድ ግብዝና ተራ ሰው ያደርጉታል ። በዚህ ሰበብ እኔ ትግሬው፣ እኔ አማራው ፣ እኔ ኦሮሞው እኔ …እያለ ባላዋቂነት ውስጥ እየዳከረ ፣ቅልጥ ባለ ግብዝነት ተወጥሮ ፣ ተራ ሟችነቱን ረስቶ ሲያቅራራ እዛም እዚህም ይስተዋላል ።
አውሮፖና አሜሪካ ብቻ ሳይሆኑ ሩቅ ምሥራቅ እና የአረብ አገራት በሙሉ የሰው ማንነቱ ሰው መሆን ብቻ መሆኑንን ጠንቅቀው ያውቃሉ ። የሰውን ክቡርነትም በየህገመንግስታቸው አውጀዋል ።
ሰው የተለያየ የመግባብያ ቆንቋ ቢናገርም በተፈጥሮው አንድ ነው ። በቋንቋው ንግግርም ነባራዊ ተግባባቶች አይቀየሩም ። በፈለከው ቋንቋ ተናገረው ፤ሙገሳ ሙገሣ ስድብ ስድብ ነው ። የተለያየ ቋንቋ መናገር ተፈጥሯዊ እንጂ እርግማን አይደለም ። እርግማን የሚሆነው አንድ ሉአላዊ አገር አንድ ብሔራዊ ቋንቋ ከሌለው ብቻ ነው ።
የአንድ አገር ዜጋ እርስ በእርሱ እንዲግባባ አንድ መግባቢያ ቆንቋ መማር ያስፈልገዋል ። እንዳይግባባ ቋንቋውን ከፋፍሎ አንድ ብሔራዊ ቋንቋ በህግ ወስኖ ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እንዳይማር ማድረግ እርግማን ነው ። ( በበኩሌ የባቢሎን ግንበኞች ፈጣሪን እናገኛለን ብለው ወደሰማይ ግንብ መገንባታቸው ታላቅ ጅልነት እና ፍጹም ቂልነት መሆኑንን ፈጣሪ ያውቃልና እነዚህ ሰዎች በለመግባባት የተነሳ ተበታትነው በየግላቸዎ ወደ ሥራ እንዲሰማሩ በመሻት ቋንቋቸውን እንደከፋፈል አምናለሁ ። )
እርግማንነቱም ዛሬ ላይ እየታየ ነው ። ኢትዮጵያ ዛሬ በማያባራ የእርስ በእርስ ጦርነት የተዘፈቀችው አንድ ብሔራዊ ቋንቋ ስለሌላት ነው ። የዛሬ ሥመ ጥር ፖለቲከኞች እኮ በአማርኛ በጣፈጠ አንደበት የሚናገሩት ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ የአማረኛ ቋንቋ ትምህርት ሥለተማሩ ነው ። ይህ እውነት መሆኑ ቢታወቅም ይህንን ሃቅ ማንም ትንፍሽ አይልም ።
ኃያል አገራትም ይህንኑ የትምህርት ሥርዓት ይከተላሉ ። እናም ዜጎቻቸው ሁሉ በዚህ ብሔራዊ ቋንቋቸው መግባባት ይችላሉ ። እኛም ይኽንን እውነት በጥሞና እንድገነዘብ ጥረት ሲያደርጉ ግን አይስተዋሉም ። ከራሳቸው ህገመንግስት ተመክሮ በመነሳት ሩሲያም ሆነች አሜሪካ ስለ ብሔራዊ ቋንቋ አስፈላጊነት አበክረው ሊመክሩን ይገባ ነበር ።
የእነሱ አገር ዜጎች አንድ መግባቢያ ቋንቋ ያላቸው ና ሰው መሆናቸውን የተገነዘቡ ከመሆናቸውም በላይ ፣ ነገ ተራ ሟችነታቸውን ጠንቅቀው የሚያውቁ እንዲሆኑ በብሔራዊ ቋንቋቸው አስተምረዋል ።( ጥቂቶች ከአፍሪካ ወደ አሜሪካ እና አውሮፖ የፈለሱ እና ዜግነት ያገኙ ኢትዮጵያዊያን ግን ከነድንቁርናቸው የተቀመጡ ፣ የሰውን ሰውነት የካዱ እና በሰው ደም የማቆምሩ ሆነው እናገኛቸዋለን ። )
የኢትዮጵያ ዜጎች ግን ዛሬም በቋንቋ ልዩነት ብቻ ሰው መሆናቸውን ረስተው እርስ በእርስ ሲሰዳደቡ ፣ ሲታኮሱ እና ሲገዳደሉ ይስተዋላል ። ሰው ሰውነቱን በመዘንጋት ብቻ ሳይሆን በቋንቋ ተቧድኖ አንዱ ቋንቋ ሌላውን ቋንቋ ካልገዛ የሚል አስተሳሰብ የነገሰባት አገር ኢትዮጵያ ብቻ መሆኖ በእጅጉ ያስገርማል ። “ አይ ወያኔ ! “ ማሰኘቱም አይቀርም ።
ለምን ? ወያኔ ይኽንን አደረገች ? ይኽ እኮ በፈለከው ጋዜ በጊዜ መቆጣጠሪያ ተጠቅመው የምታፈነዳው ቦንቡ ነው ። ” ለምን ? ለምን ?… “ለምን የተሰኘ ጥያቄ በበስንቱ ድራማ ላይ ተደጋግሞ ቢሰማም ፤ ለምን ? የሚባል ጥያቄ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የማወቅ ጥማትን ለማርካት የሚጠየቅ ጥያቄ ቢሆን ደስ ይለኛል ።
ወያኔ ይኽንን ታይም ቦንብ ያስቀመጠችው እንደአቀደችው ቢያንስ 40 ዓመት በኢትዮጵያ የመሪነት ወንበር ለመሰኖበት አቅዳ ነውን ? ይህስ እቅዷ በአልነቃ ማህበረሰብ ውስጥ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል ። ብላ መገመት ሞኝነት አልነበረም ወይ ? ዜጎች ከድህነት አንፃር ያለ ስጋት በአገራቸው ሰርተው ዳቦ ማግኘት እንጂ ከዳቦ የዘለለ ወቅታዊ ጥያቄ እንደሌላቸው እንዴት ዘነጋች ? ወይስ በሶና ስኳር እየበጠበጠች በመጠጣት ምኒልክ ቤተመንግስት እንደገባች ዘነጋችው ?
የአውሮፓ ፣ የአሜሪካ ፣ የቻይና እና የሩሲያ መንግስታት የሥጋ ጥቅምን ወይም መሠረታዊ ፍላጎታቸውን አሸነፈው በአመዛኙ ከቁሥ ሰቀቀን ወጥተው በእምሮአዊ እርካታ ላይ የደረሱት እኮ ዜጋቸውን በትምህርት አንድ በማድረግ ነው ። የተለየ የየራሱ ቋንቋ ይኑረው በአገራቸው የሚማር ዜጋ ሁሉ ብሔራዊ ቋንቋቸውን የማወቅ ግዴታ አለበት ።
ባለፀጎቹ ይህንን ያህል ለብሔራዊ ቋንቋቸው ዘብ ሲቆሙ እኛ ግን በሃሳብ የሚያግባባንን ብሔራዊ ቋንቋ ለምን ናቅን ? ለምን ? ለምን ? ለምን ?
የለምን ጥያቄ መልስን የሚሰጡን የዓለምን መንግሥታት ፖለታካ የተቆጣጠሩት ከላይ የጠቀስኳቸው መንግስታት ናቸው ። አፍሪካን ለመለወጥ ቢችሉም በእያንዳንዱ አገር ያለው የመሬት ውስጥ ሀብት ለተራ ሟቹ ግድ እንዳይኖራቸው አደርጓቸዋል ። ተራ ሟቹ አፍሪካዊ ህዝብ በቋንቋ አለመግባባት ፣ በአላዋቂነት እና አምሳያውን የነቃ ፖለቲከኛ በማመን ሰበብ ለምን ሲገዳደል ውሎ አያድርም ?
ተራ ሟቹ አፍሪካዊ እኮ ከእውቀት የራቀ ነው ። ” ለምን ” ብሎ አይጠይቅም ። ከ ለምን በፊት ዳቦ ነው ጥያቄው ። የሚያበለው ፣ የሚያለብሰው ፣ መጠለያ የሚሰጠው ካገኘ ዘንዳ የታዘዘውን ይፈጽማል ። በኃይማኖት ፣ በጎሣ እና በወንዝ ልጅነት ተቧድኖ እርስ በእርሱ ይታኮሳል ። ይገዳደላል ።
የዓለምን ፖለቲካ የሚዘውሩትም በሳተላይታቸው እንደ ድራማ ያዩታል ። ምናልባትም ከ50 ዓመት በኋላ በፊልም መልክ አቀነባብረው ቢዚነስ ይሰሩበት ይሆናሉ ። ከ50 ዓመት በኋላ የዛሬዎቹ የአፍሪካ መሪዎች አይኖሩምና ።
ከ0001 ዓ/ም እሰከ 2025 ዓ/ም በቢሊዮን የሚቆጠሩ የዓለም ህዝቦች በተፈጥሮ ፣ በጦርነት ፣ በበሽታ ፣ በአደጋ ፣ወዘተ ። መሞታቸው እርግጥ ነው ። በምትካቸው በቢሊዮኖች ተወልደው ይኸው ለዛሬው አዲስ ዘመን ትውልዳቸው በቅቷል ። ምንም በጊዜ ብዛት በ0001 ዓ/ም በየአህጉሩ የነበረውን ዝርያቸውን ቢረሱትም ፣ እጅግ ከሚያውቁት በላይ ወድማማችና እህትማማች ሆነው ለዛሬ በቅተዋል ። ይሁን እንጂ አንዱ አውሮፓ ና አሜሪካ እንዲሁም እሩቅ ምሥራቅ እና መካከለኛው ምሥራቅ በመኖሩ ብቻ ሥጋነቱን በዘመን ብዛት ረስቷል ። ወይም አላወቀም
ይኽ ብቻ አይደለም የሰው የክፋት ምንጭ አለማወቅ ነው ። የዓለም ሰው በሙሉ ከክርስቶስ ልደት በፊት 3000 ዓመት ተጉዞ በምድር ላይ ሥንት ሰው ነበር ብሎ ያለመ ጠየቀ ነው ።
የዛሬ 5025 ዓመት አፍሪካ ውስጥ 1000 እሰከ 30,000 እንደሚኖር ይገመታል ። ምክንያቱም ጎግልን ብጠይቁት በዛን ዘመን በዓለም የሚኖረው ህዝብ ከ1 ሚሊዮን እስከ 10 ሚሊዮን ነበርና የአፍሪካ ኮታ ከዚህ ቁጥር አያልፍም ። እናም ወገን ከፖለቲካው ባሻገር እውቀትን ገንዘባችን ካላደረግናት እና ከጥበብ ከራቅን አፍሪካዊያን ለዘላለም እርስ በእርሳችን መጋደላችን አያባራም ።
አውሮፓና አሜሪካም የምንተላለቅበትን ዘመናዊ መሳሪያ በገፍ እያመረቱ መሸጣቸውን ይቀጥላሉ ። በዙረቱ ሳይመጣ የማይቀረውን አዲስ ዓመታቸውን እስከ ዓለም ፍፃሜ በታላቅ ፌሽታ ይቀጥላሉ ። እኛም መልካም አዲስ ዓመት እንላቸዋለን ። ዓለም በዝንጋታ ገመድ እየጎተተች ወደ ሞት እንደምታደርስ ግን ልናስታውሳቸው እንወዳለን ።
Well, it is the right thing to tell what we do feel and the way we fell about the situation in our country in any way we can !!!
But, especially after so many years of untold sufferings, our focus must be on the question of why we terribly failed to get our country the country of rights and freedoms , and what should be done now and tomorrow instead of keeping the same stories of horror because of our political stupidity and moral clumsiness !!!
What are we going to answer if our children and gran children ask and challenge us with a very tough argument of “Do not Just Tell Us , Show Us!”?