October 13, 2024
5 mins read

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

89999hjkhhkበአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ነው መስለኝ፣ ከተሳሳትኩ አርሙኝ፣ ረዳት ፕሮፌሰር ጌታ አስራደ፣ ከአማራ ፋኖ በጎንደር አመራር አንዱ ሲሆን፣ ሌላው የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል ሰብሳቢና የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ፋኖ ጠበቃ አስረስ ማረ ዳምጤ ነበር፡፡

እነዚህ ሁለት የፋኖ መሪዎች አንድ አይነት ነገር ነው የተናገሩት:: የአንድነትን አስፈላጊነት ነው በአፅንዎት የገለፁት::

“የአማራ ህዝብ ካለው አቅም አጻንር፣ የፋኖ ሓይል ካለው አቅም አኳያ ከዚህ በላይ መስራት እንችላለን፣ ይገባናል” ያለው አስረስ ማረ ዳምጤ፣ የዓላማ የግብ የአካሄድ የስትራቴጂ የታክቲክ ልዩነት በምንም ተዓምር በፋኖ መካከል እንደሌለና፣ ፋኖ ከታች ወደ ላይ እያደረገ የመጣ እንደመሆኑ ፣ አሁን በቅርጽ በአደረጃጀት ጉዳይ መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች እንዳሉ አምኗል፡፡ ከሌሎች የፋኖ አደረጃጀቶች ጋር ውይይቶች፣ ንግግሮች እየተደረጉ እንደሆነ የተናገረው አስረስ፣ የ”ችርቻሮ ድል” ብሎ ከጠራቸው ከታክቲካል ድሎች ወደ ወሳኝ፣ ጦርነት በአሸናፊነት ወደ ሚያጠናቅቁ ስትራቴጂክ ድሎች መሸጋገር የግድ እንደሆነ አሳስቧል፡፡ በአንድነት እንነሳ ሲል ጥሪ አቅርቧል፡፡

ፋኖ ጌታ አስራደም በበኩሉ፣ ከሌሎች ወንድሞቻችን ጋር ውይይቶች እያደረግን ነው፣ በቅርቡም አንድ ሆነን መልካሙን ዜና ለህዝብ እናበስራለን ሲል ትልቅ ተስፋ ሰጥቷል፡፡ የአማራ ፋኖ አንድነት ድርጅት ውስጥ ያለን፣ ከሌሎች ጋር ተነጋግረን፣ ሁሉንም አሸናፊ፣ አንዱ የበላይ ሌላው የበታች ያልሆነበት አሰራር ለመዘርጋት አበክረው እንደሚሰሩ ገልጿል፡፡

ፋኖ ጌታ አስራደም ሆነ ፋኖ አስረስ፣ የሰጡትን አስተያየቶች ላዳመጠ ሰው፣ ከዘመነ ካሴና ከ እስክንድር ነጋ በተጨማሪ፣ ፋኖ ተዋጊዎች ብቻ ሳይሆን እጅግ በጣም ብዙ የፖለቲካ ብቃት ያላቸው፣ ብዙ ወገኖች ውስጡ እንዳሉትም በግልጽ ያመላከተ ነው፡፡

ወደ አንድነት እስከመጡ ወይም ወደ አንድነት ለመምጣት እየሰሩ እስከሆነ ድረስ፣ ሁሉንም ልናግዝ፣ ልናበረታት እንጂ ወደ ማበላለጥ መሄድ የለብንም፡፡ ማንም ይሁን ማንም፣ ለህዝብ የሚጠቅም ነገር ከሰሩ መደገፍ አለብን፡፡ ፋኖ ጌታ አስራደ የተናገረው ነገር አንዷም ነገር ጠብ የምትል አይደለችም፡፡ አስረስም የተናገረው እንደዚሁ፡፡ ጎራ ይዘን አስረስን እያሳነስን ጌታ አስረዳን ማሞገስ፣ ጌታ አስራደን እያሳነስን አስረስን ማወደስ ነውር ብቻ ሳይሆን ጸረ ፋኖነት ነው፡፡ ፋኖዎች እንድ እንዳይሆኑ የማድረግ ተግባር ላይ እንደመሰማራት ነው፡፡

ይህን ስል የፋኖ መሪዎች ስህተት ሲሰሩ መተቸት፣ ጥሩ ሲሰሩ መመስገን የለባቸውም ማለቴ አይደለም፡፡ ከዚህ በፊት አስረስን ተችቼ ጽፊያለሁ፡፡ ከዚህ በፊት ከነ ጌታ አስራደ ጋር ያለን ፋኖ እያሱን ተችቼ ጽፊያለሁ፡፡ ከሁለቱም አሰላለፎች፡፡ አሁንም ደግሞ ከሁለቱም ጥሩ ነገር ስሰማ፣ ደስታዬ ገልዣለሁ፡፡ ሁለቱም ጥሩ እያደረጉ፣ አንዱን አሞግሶ ለሌላ ዝም ማለት ግን ትክክል አይደለም፡፡

1 Comment

  1. Well, the message is straightforwardly clearly constructive!
    It may seem not big deal , but the way we frame or set the topic is so important . It is from this point of mine that the phrase “Yechrcharo Dil” sounds very ugly if we’re talking about the very justified but extremely challenging struggle being conducted by Fano Amhara and other freedom- loving compatriots!!!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

194059
Previous Story

የምርኮኛ ጎርፍ ”ወንድሞቻችን ናቸው፥ እንኳን ሳይሞቱ ከእኛ እጅ ገቡ። የምንበላውን ይበላሉ። ጊዜው ሲደርስ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ይገናኛሉ”

amhara
Next Story

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

Latest from Blog

blank

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ
blank

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ
blank

አርበኛ አስረስ ማረ እና ምርኮኞቹ | ስለ ፋኖ የብሔራዊ ባንክ ገዥው ያልተጠበቀ ንግግር |

#ሰበር_ዜና #AmharaFano ➢መሰከረም 29/01/2017 ዓ.ምብዙ ድሎችን አግኝተናል፣➢1️⃣115 ምርኮኛ ➢2️⃣70 እስረኞችን አስለቅቀናል➢3️⃣ 7 ብሬን➢4️⃣2 ድሽቃ➢5️⃣ 4 ስናይፐሮችን➢ለትግል የሚጠቅሙ የነፍስ ወከፍ ክላሾችንተተኳሾችን መኪኖችም ገቢ… pic.twitter.com/GbYaOAtFtr — ትዝብቱ🔔 (@Geteriew1) October 12, 2024 በፋኖ የተማረኩት ኮሎኔል
Go toTop