June 21, 2024
3 mins read

ኣንድ የፋኖ ድርጅት ወይንስ ኣንድ የፋኖ መሪ? ኣንድ መሆን ለምን ኣቃታን ዘመነ ካሴ?

Fano
ኣንድ የፋኖ ድርጅት ወይንስ ኣንድ የፋኖ መሪ?
ኣንድ መሆን ለምን ኣቃታን ዘመነ ካሴ?

ፋኖ ታምራዊ እድገት ኣሳይቷል:: ግዙፍ  ድርጅት በኣራቱም የኣማራ ክፍለ ሀገራት ፈጥሯል::  ነገር ግን ኣራቱ ኣንድ ለመሆን ጊዜ ወሰደ:: የህዝቡንም መሰዋትነት ጨመረ::  ኣማራ ጠሉ መንግስት ግልፅ የሆነ የዘር ፍጅት እየፈፀመ ነው:: ፋኖን መመክት ሲያቅተው ፋኖ ሲያጠቃው መደዳውን የኣማራን ህዝብ መጨፍጨፍ ቋሚ ኣካሄድ ኣድርጎታል:: ይህ ኣካሄድ በኣስቸኯይ መቆም ኣለበት::

ፍኖ ኣንድ መሪ መምረጥ የበለጠ ያስቸገረው ይመስላል::  ኣንድ መሪ ቢመርጥም ለምን ጎጃም ለምን ወሎ ለምን ሽዋ ለምን ከጎንደር በሚል ኣኩራፊ ሊበዛ ይችላል:: ኣኩራፊዎች ደግሞ ትግሉን ሊጎትቱት ይችላሉ::
ስለዚህ ፋኖ ኣንድ መሪ ሳይሆን ኣንድ ድርጅት ነው የሚያስፈልገው:: የቡድን ኣመራር ማለት ነው::  ኣራቱ ክፍላተ ሀገራት በጋራ ለመስራት  ምንም ችግር የለም:: ስለዚህ ቀጥሎ መምጣት ያለበት በመጀመሪያ የስራ ዘርፎችን መለየት ማለትም የጦር መሪ ምክትል መሪ ህዝብ ግንኙነት ምክትል ፀሐፊ የውጭ ጉዳይ ስትራቴጂስት የፖለቲካ ሃላፊ  ሎጂስቲክ ወዘተ በማለት የስራ ዘርፎችን ማውጣት::ለምሳሌ ኣስራ ስድት የስራ ዘርፎች ካሉ ከኣራቱ ክላፋተ ሀገራት ኣራት ኣራት ፋኖዎች በመምረጥ ኣስራ ስድት የስራ ዘርፎች ላይ መመደብ:: መሪ የሚባል ሳይኖር በቡድን መምራት::
ለምሳሌ ኣብይ የሚባል ጠቅላይ ሚንስቴር ባይኖር ኢትዮጵያ ይህንን ያህል እልቂት ኣይደርስባትም ነበር::  ሰራዊቱን መካላከያ ሚንስቴር ቢመራው ግብርናውን ግብርና ሚንስቴር ጤናውን ጤና ሚንስተር  ወዘተ ሆኖ በቡድን ቢመሩ ኣምባ ገነን ኣብይ ኣይኖርም ነበር:: ስለዚህ ኣንድ መሪ የሚለውን ኣጥፎቶ ፋኖ ኣንድ ድርጅት የሚለው ላይ ቢያተኩር ጥሩ ነው  ምን ትላላችሁ?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበረው እና አሁን ላይ በአማራ ፋኖ በጎጃም የሁለተኛ (ተፈራ ) ክፍለጦር ሰብሳቢ የነበረው ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ በክብር ተሰዋ። የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህሎና አደጋ ለመቀልበስ ያለ

ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ የሐዘን መግለጫ ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል !

January 22, 2025
ዳግማዊ ጉዱ ካሣ “ይድረስ ለእገሌ” ማለቱ ሰለቸኝና ተውኩት እንጂ ዛሬም መጻፍ የፈለግሁት የአማራን ዕልቂት ለመታደግና የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር እየተዋደቁ ላሉት ወገኖቼ ነው – በፋኖም ይሁን በሌላ ስም፡፡ ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ለመመለስ የነገድና

ጀልባዋ አትሰምጥም፤ የሚሰምጥ ግን አለ!

[ማስታወሻ ከፍል አንድ፣ በዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ኦፍ ጃዋር አንድ ኢትዮጵያ ተብሎ በእንግልዝኛ ወጥቷል] (https://zehabesha.com/of-jawar-and-ethiopia/) ባለፈው ሰሞን፣ ጃዋር መሐመድ ከደረጀ ኃይሌ ጋር  በነገራችን ላይ ክፍል ሁለት ባደረገው ቃለ ምልልስ ላይ ተመስርቼ ገንቢ አስተያየት ጽፌ በኢንግሊዝኛው ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ አሳትሜ ነበር። አስተያየቴ በዚህ ቃለ ምልልስ

ስለ ጃዋርና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

Go toTop