May 8, 2024
5 mins read

ታሪክ ራሷን ደገመች ኢትዮጲያ በሌላ ግፈኛ መሪ መዳፍ ስር ወደቀች

The Two Oromo Leadersበሃገራችን ኢትዮጲያ ከጥንት ከነገስታቱ ዘመን ጀምሮ  በጎ ታሪኮችም ክፉ ታሪኮችም  በመሪዎች ሲካሄዱ ኖረዋል:: ጸሃፍቱና መገናኝ ብዙሃን/ ሚዲያን የሚቆጣጠሩት  መሪዎች በመሆናቸው የመሪዎቹ ታሪክ ጸሃዩ ንጉስ ቆራጡ ፕሬዚዳንት ብልሁ አስተዋዩ ጠቅላይ ሚንስትር እየተባለላቸው ዛሬ ደርሰናል  ግፉም  እንዲሁ  ካንዱ መሪ ወደሌላው ታሪክ ተደገመች  ሆኖብናል::

በደርግ መንግስት  ቀይሽብር በተባለው ዘግናኝ  ጭፍጨፋ  ተጠያቂ የነበሩትን ለህግ የማቅረብ ሂደት ቀጥሎ አትሌት  ሻምበል ማሞ ወልዴ የኪነጥበብ ባለሙያ አስር አለቃ ተዘራ ሃይለሚካኤልና መሰሎቻቸው ሳይቀሩ ተይዘው ምርመራው ሲቀጥል ጥቆማው  ወደሁሉም የደርግ ሃላፊዎችና ባለስልጣናት ሲያመራ የዝግ ችሎቱን ያካሂዱ የነበሩት አፈንጉስ ተሾመ ቅጣው  ጉዳዩን በይደር እያቆዩ  ደርግ ተጠያቂዎቹን በሙሉ ማቅረብ  ያለመፈለጉን ሲረዱ ያንዳንዶቹም ምርመራ እንዳይካሄድ ሰሞኑን ዶ/ር  አብይ ባዘዙት መልክ ሲያግድ አፈንጉስ ተሾመ በጤና ምክንያት ብለው ከሃገር ተሰደው በዚያው ቀርተዋል::

አፈንጉስ ተሾመ በክፉ ቀን መሸሸግ እንደሚሻል “ክፉ ቀንና ቅምዝም ዱላን ዝቅ ብሎ ማሳለፍ ነው” በሚል ምሳሌያቸው የሚታወቁ ሲሆኑ  ትክክለኛው  የፍትህ መንበር ቅምዝሙን ሳይፈራ  ፍትህን የሚዳኝ መሆኑን በታሪክ በቅን ፍርዳቸው የተጋዙ የተገደሉ የተሰደዱ የሃገራችንም ሆነ የሌሎች ሃገሮች  ዳኞች ወርቃማ ምስክርነት ይገኛል:: በዚህ አጋጣሚ የወያኔን የካንጋሮ ችሎት ሳትፈራ  ወያኔ በግፍ ያሰራቸው የራሱን ባልደረቦች እነስዬ አብርሃን በነጻ ያሰናበተች ክብርት ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳን ከወቅቱ የፖለቲካ ምልከታዋ  በማይገናኝ መልኩ ሙያዊ ብቃትዋን ላደንቅ እወዳለሁ::

የመቂው ጎልማሳ ባቲ ባልተለመደ ከኦነግ ፖለቲከኛንና ምሁራን በተለየ በመድረክ ውይይት ከሌሎች የኢትዮጲያ ፖለቲከኞች ጋር የሚወያይ ባለተስፋን ሰው ግድያ ዶ/ር አብይ ከፎከሩበት በፓርቲያቸው ላይ የሚነሳ አመጽን ከኢሃአፓ ጊዜ በበለጠ እጥፍ እንበቀላለን ያሉትን ለመጀመራቸው ማረጋገጫ  ሲሆን  የሚያሳዝነው ግን በዚህ መልኩ ለግል ስልጣን የሰዎችን ደም የሚያፈሱ መጨረሻቸው ለራሳቸውም ለልጆቻቸውም ሃፍረት መሆኑን  ምንም የተማረች ሃገሯን የትምትወድ ቢሆንም የደርጉ ጨፍጫፊ ኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማርያም ልጅ ዶክተር ትእግስትን በየሚዲያና በየመደረኩ የሚደርስባት ወከባ ማዋረድ ምስክር ነው:: የሌሎቹ አምባገነኖች ልጆች የስታሊን ልጅ እንዳደረገችውን ወላጅ አባትዋን ክዳ  ከሩሲያ ህዝብ ጎን በመቆም ለስደት የተዳረገችው ትገኛለች::

ስለዚህ ዶ/ር አብይ የሰው እድሜ ቢበዛ ሰባ ሰማንያ በሚለው ቅዱስ መጽሃፍ ግማሹን በሰላም ይፈጽሙ ዘንድ  የሰው ደም በፖለቲካ ሴራ  ፈስሶ እንዳይቀር  የሚቻልዎትን ያድርጉ በክፉ የዘር ፓለቲካ ወክለዋለሁ በሚሉት የኦሮሞ ክልል ጭምር የሚያልቀው ህዝባችን   ጉዳይ ግድ ብሎት ባፋጣኝ ስልጣኑንን የኔታ ፕሮፌሰር መስፍን  ለደርግ በሰጡት ምክር ለህዝብ ባላደራ በቶሎ ያስረክቡና ከምድራዊም ከዘላለምዋም ቁጣ ይተርፉ ዘንድ ምክሬን ለግሳለሁ:: የኤቤል ደም በከንቱ ፈስሶ እንዳልቀረ ሁሉ የወገኖቻቻን  ደምም  በከንቱ ፈስሶ እንደማይቀር መጽሃፉ/ ኪታቡ ታሪክም ባህላችንም ምስክር ነው

 

ፓስተር ዲጎኔ ሞረቴው

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ “ይድረስ ለእገሌ” ማለቱ ሰለቸኝና ተውኩት እንጂ ዛሬም መጻፍ የፈለግሁት የአማራን ዕልቂት ለመታደግና የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር እየተዋደቁ ላሉት ወገኖቼ ነው – በፋኖም ይሁን በሌላ ስም፡፡ ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ለመመለስ የነገድና

ጀልባዋ አትሰምጥም፤ የሚሰምጥ ግን አለ!

[ማስታወሻ ከፍል አንድ፣ በዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ኦፍ ጃዋር አንድ ኢትዮጵያ ተብሎ በእንግልዝኛ ወጥቷል] (https://zehabesha.com/of-jawar-and-ethiopia/) ባለፈው ሰሞን፣ ጃዋር መሐመድ ከደረጀ ኃይሌ ጋር  በነገራችን ላይ ክፍል ሁለት ባደረገው ቃለ ምልልስ ላይ ተመስርቼ ገንቢ አስተያየት ጽፌ በኢንግሊዝኛው ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ አሳትሜ ነበር። አስተያየቴ በዚህ ቃለ ምልልስ

ስለ ጃዋርና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

Go toTop