March 23, 2024
2 mins read

“የልጄን አስከሬን ትቸ ከምወጣ እኔ ልሰዋ!” ~ አርበኛ አረጋ አለባቸዉ

434082502 7801158559902505 7404445181526337827 n
434082502 7801158559902505 7404445181526337827 n

ሞቷል የተባለውን ልጁን ከነ ህይወቱ ከጠላት መንጋጋ መንጭቆ አውጥቶታል

በሸዋ ጠቅላይ ግዛት እሸቴ ሞገስ የተባለ አርበኛ ልጁ ይታገሱ እሸቴ ስለቆሰለበት የልጀን እስከሬን ትቸ አልሄድም “ሚካሄልን ይታገሱን ትቸ አልወጣም” በማለት የአማራን ህዝብ የአባትነት ታሪክ በዚህ ዘመንም ያለ እውነታ መሆኑን ሰምተን አንብተናል: ክብር ለአባታለም ብለናል::

በትላንትናው እለት በደቡባዊ ጎንደር ክፍለ ሃገር እብናት ግንባር ይህ ታሪክ ተደግሟል:: በጎንደር ክፍለ ሃገር ስመጥሩ አርበኛ ኮማንደር አረጋ አለባቸው ሁለቱ ልጆቹ ማለትም ጌታው አረጋና ክንድየ አረጋ አብረውት ይታገላሉ::

በትላንትናው እለት ጌታው አረጋ እብናት ከተማን ለመያዝ በተደረገ አወደ ውጊያ ይቆስልና ይወድቃል: በወቅቱ የትግል ጏዶቹ ተስውቷል ብለው ለጊዜው የጠላት ትጽህኖ ስለነበር ወደ ውጊያው ያተኩራሉ:: በሌላ አቅጣጫ ሲዋጋ የነበረው አርበኛው አባቱ ኮማንደር አረጋ አለባቸው ልጁ እንደተመታ ይነገረውና ልጀን ትቸ ከምወጣ ሽህ ጊዜ ልሰዋ ብሎ ዘሎ ወደ ውጊያ በመግባት ከአንድ ሰዓት በላይ እልህ አስጨራሽ በሆነ ውጊያ ተዋግቶ ለጁን ከእነ ህይወቱ ተሽክሞ ለማውጣት ችሏል::

ተስውቷል የተባለው ልጁም በአሁኑ ሰዓት ህክምና እየተደረገለት በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛል:: ጀግናው ኮማንደር አረጋ አለባቸውን ቃለ መጠይቅ አድርጌ ዝርዝር ይዠ እመለሳለሁ!!!

በጎንደር ምድር የአባትና የልጅን ፍቅር በዚህ መልኩ በተግባር ላሳየኸው የስሜነኛው አርበኛ ኮማንደር

አረጋ አለባቸው ክበርልን!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

189465
Previous Story

በዘረኞች ጥላቻ እየፈረሰች ያለች ከተማ – አዲስ አበባ

Adwa
Next Story

በማርያማዊ መርሆዋ በአድዋ ጦርነት ላይ ኢትዮጵያን ለቅድጅት ያበቃቻት ኦቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ናት

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop