ማንኛውም ፖለቲከኛ ነኝ ባይ ባለኝ የሚሊተሪ ኃይልና የተወሳሰበ የጦር መሳሪያ ሌላውን አንበረክካለሁ የሚል አርቆ-አሳቢነት የጎደለው የመጋፋትና ሌሎችን አሳንሶ የማየት የውጭ ፖለቲካ የሚያሰከትለው አደጋ!!
“የልጄን አስከሬን ትቸ ከምወጣ እኔ ልሰዋ!” ~ አርበኛ አረጋ አለባቸዉ March 23, 2024 ዜና Facebook X Linkedin Pinterest Telegram Whatsapp Email ሞቷል የተባለውን ልጁን ከነ ህይወቱ ከጠላት መንጋጋ መንጭቆ አውጥቶታል በሸዋ ጠቅላይ ግዛት እሸቴ ሞገስ የተባለ አርበኛ ልጁ ይታገሱ እሸቴ ስለቆሰለበት የልጀን እስከሬን ትቸ አልሄድም “ሚካሄልን ይታገሱን ትቸ አልወጣም” በማለት የአማራን ህዝብ የአባትነት ታሪክ በዚህ ዘመንም ያለ እውነታ መሆኑን ሰምተን አንብተናል: ክብር ለአባታለም ብለናል:: በትላንትናው እለት በደቡባዊ ጎንደር ክፍለ ሃገር እብናት ግንባር ይህ ታሪክ ተደግሟል:: በጎንደር ክፍለ ሃገር ስመጥሩ አርበኛ ኮማንደር አረጋ አለባቸው ሁለቱ ልጆቹ ማለትም ጌታው አረጋና ክንድየ አረጋ አብረውት ይታገላሉ:: በትላንትናው እለት ጌታው አረጋ እብናት ከተማን ለመያዝ በተደረገ አወደ ውጊያ ይቆስልና ይወድቃል: በወቅቱ የትግል ጏዶቹ ተስውቷል ብለው ለጊዜው የጠላት ትጽህኖ ስለነበር ወደ ውጊያው ያተኩራሉ:: በሌላ አቅጣጫ ሲዋጋ የነበረው አርበኛው አባቱ ኮማንደር አረጋ አለባቸው ልጁ እንደተመታ ይነገረውና ልጀን ትቸ ከምወጣ ሽህ ጊዜ ልሰዋ ብሎ ዘሎ ወደ ውጊያ በመግባት ከአንድ ሰዓት በላይ እልህ አስጨራሽ በሆነ ውጊያ ተዋግቶ ለጁን ከእነ ህይወቱ ተሽክሞ ለማውጣት ችሏል:: ተስውቷል የተባለው ልጁም በአሁኑ ሰዓት ህክምና እየተደረገለት በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛል:: ጀግናው ኮማንደር አረጋ አለባቸውን ቃለ መጠይቅ አድርጌ ዝርዝር ይዠ እመለሳለሁ!!! በጎንደር ምድር የአባትና የልጅን ፍቅር በዚህ መልኩ በተግባር ላሳየኸው የስሜነኛው አርበኛ ኮማንደር አረጋ አለባቸው ክበርልን! Facebook X Linkedin Pinterest Telegram Whatsapp Email Leave a Reply Cancel replyYour email address will not be published. Δ Previous Story በዘረኞች ጥላቻ እየፈረሰች ያለች ከተማ – አዲስ አበባ Next Story በማርያማዊ መርሆዋ በአድዋ ጦርነት ላይ ኢትዮጵያን ለቅድጅት ያበቃቻት ኦቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ናት
ማንኛውም ፖለቲከኛ ነኝ ባይ ባለኝ የሚሊተሪ ኃይልና የተወሳሰበ የጦር መሳሪያ ሌላውን አንበረክካለሁ የሚል አርቆ-አሳቢነት የጎደለው የመጋፋትና ሌሎችን አሳንሶ የማየት የውጭ ፖለቲካ የሚያሰከትለው አደጋ!!