እስክንድር ነጋ እመራዋለሁ የሚለው የአማራ ህዝባዊ ሰራዊት የሚባል አለ ወይ?

ግርማ ካሳ

ይህ ድርጅት፣ በወረቀት እንጂ በተግባር ያለ አይመስለኝም ብዬ ጽፌ ነበር፡፡ “ተሳስተሃል፣ መረጃው ስለሌለህ እንጂ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው” ተብያለሁ፡፡ እርማቱን ተቀብያለሁ፡፡ በመሆኑም “አላውቅም” ከማለት ውጭ “ያለ አይመስለኝም ወይም የለም” ብሎ መነገር አልችልም፡፡ ስለዚህ ብዙ መረጃ ስለሌለኝ እንዲህ ነው እንዲያ ነው ብዬ ለመናገር ይከብደኛል፡፡

ሆኖም ግን መረጃ ስላገኘሁበት ጉዳይ ግን መናገር እችላለሁ፡፡ በነ ሻለቃ መከታው ማሞና መምህር ምንተስኖት የሚመራው የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ፣ ከዚህ “የአማራ ህዝባዊ ሰራዊት” ከሚባለው ጋር ግንኙነት የለውም፡፡ ወንድም እስክንደር ነጋ ፣ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ወታደራዊም ሆነ ፖለቲካዊ አመራር ውስጥ አንዱም፣ ጋር የለበትም፡፡ ከጎጃም ወደ ሸዋ ሲመጣ፣ የህዝብ ልጅ፣ የአገዛዙ ታርጌት በመሆኑ ጥበቃ ለርሱ መድበው የርሱን ደህንነት ከመጠበቅ፣ አልፎ አልፎ አንዳንድ ህዝባዊ ስብሰባዎች ላይ ፣ እንደ ታዋቂ በህዝብ ተወዳጅ ሰው፣ የሸዋ ፋኖዎችን ወክሎ ሳይሆን ራሱን ወክሎ ንግግሮች እንዲያደርግ ከማመቻቸት ውጭ፡፡

ከዚይ ባለፈ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ መሪዎች፣ ሌሎች እንደሚያደርጉት፣ በየቱቡና ሜዲያ ወጥተው የህዝብ ልጆች፣ ታጋዮች ላይ አስተያየት እንዲሰጡ ተፈልጎ ከሆነ አያደርጉትም፡፡ ልዩነቶች፣ ክፍተቶችም ካለ የውስጥ ጉዳይ ነው በሚል ችግሮችን በውስጥ፣ በውይይት ለመፍታት ይሞክራሉ እንጂ፣ በየሜዲያው ለአገዛዙ ግባት የፖለቲካና የፕሮፖጋንዳ ትርፍ የሚስጥ ስራን አይሰሩም፡፡ የነርሱ ትኩረት አገዛዙ ላይ እንጂ ሌሎች ፋኖዎች፣ ሌሎች ለህዝብ የሚታገሉ ወገኖች ላይ አይደለም፡፡

ከዚህም የተነሳ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝን፣ ከአማራ ህዝባዊ ሰራዊት ከተባለው ጋር በማገናኘት፣ የአማራ ህዝባዊ ሰራዊት የተባለው ስብስብ አመራሮች ለሰሯቸው ወይንም ለሚሰሯቸው ስህተቶች፣ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ጋር ማገናኘት ተገቢ አይደለም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  Hiber Radio: አማራው ተደራጅቶ ራሱን ከህወሃት ጥቃት እንዲከላከል ጥሪ ቀረበ

በተቃራኒው ደግሞ አንድ ዋሺንገትን ዲሲ ያለ ወንድም አለ፡፡ አገሩን የሚወድ ታጋይ ነው፡፡ ቢያንስ በውጭ፡፡ ግን የፖለቲካ ብስለት የሌለው፣ ምን አልባት የጤና ችግር ያለበት፣ ስራ ፈት ሰው ነው የሚመስለው፡፡ ሺመልስ ለገሰ ይባላል፡፡ ይህ ሰው የ እስክንድር ነጋ የቅርብ ሰው ነኝ ባይ ነው፡፡ ሆኖም የእስክንድር ነጋ የቅርብ ሰው ነው ማለት፣ እስክንድር ነጋ ነው ማለት እንዳልሆነ በትልቁ ሊሰመርበት ይገባል፡፡ ብዙ ፣ ካድሬ ይመስል፣ “እስክንድር፣ እስክንድር” የሚሉ አሉ፡፡ ይህም ሰው እንደዚያ ነው፡፡ ይህም ሰውም ሆነ በዳያስፖራ ያሉ ቢጤዎቹ፣ ሌላ የራሳቸው አጀንዳ ይኖራቸዋል፡፡ እነርሱ በሚያደርጉት ነገር ግን እስክንድር ነጋ ላይ ማላከክ ተገቢ አይመስለኝም፡፡

እነዚህ ሰዎች “የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ” በዳያስፖራ የድጋፍ ማሰባሰብ እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ፣ ለእስክንድር ነጋ ጥበቃ ሲያደርግ የነበረና ምን አልባትም ወደሌሎች ጠቅላይ ግዛቶች እስክንድር ካልሄደ፣ ለእስክንድር አሁንም ጥበቃ እያደረገ ያለ መሆኑን ሳያውቁ ቀርተው አይደለም፡፡

ታዲያ፣ ” የእስክንድር ነጋ ደጋፊዎች ነን”፣ እያሉ፣ እስክንድር ነጋን እየጠበቀ ያለ ኃይልን አለመደገፍ ፣ እዙ እያደረገ ያለውን የድጋፍ ማሰባሰቢያ ለማጨናገፍ መሞከር ምን ሊባል ይችላል ?? ጸረ እስክንድርነት፣ በእስክንድር ስም የሚደረግ የአብይ አህመድና ዘረኛው አገዛዝ ጥቅም የሚያስጠብቅ ፣ ብልጽግናዊ፣ ኦህድዳዊ አሳፋሪ ስራ ካልተባለ በቀር !!!!

ወገኖች እኔ ይሄንን በምጽፍበት፣ እናንተም በምታነቡበት ጊዜ ፣ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ውስጥ ያሉ ፍከለ ጦሮች ከአገዛዙ ጋር አንገት ለአንገት እየተናነቁ ነው፡፡ ህይወታቸውን አወራረደው፣ ለአገር፣ ለህዝብ ትልቅ ዋጋ እየከፈሉ ነው፡፡ እነርሱን አለመደገፍ፣ ከነርሱ ጎን አለመቆም አይቻልም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል ተጫዋች ጌታሁን በደቡብ አፍሪካ እየተሳካለት ነው

ከዚህ በታች ያለውን ማስታወቂያ እናንንብ፡፡ ባር ኮዱን በስልካችን ስካን በማድረግ እንዴት መደገፍ እንደሚገባ ወደ ሚያሳይ ገጽ ይሄዳሉ፡፡

5 Comments

  1. ክቡር አቶ ግርማ ካሳ
    በታጋይ እስክንድር ጉዳይ ያንተ ምልከታም ሆነ አስተያየት በጣም የወረደ መሆኑንን የምመስክረው መጀመሪያ ደረጃ በክፉ ትርክት አምራ ነፍጠኛ በሚል በዘር የተደራጁ ቡድኖች ላላፉት አርባ አመታት የነበርኩበት ኢህአፓም ቀና ታጋዮቹ እነ ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ያለዘር ልዩነት ለኢትዮጲያ የተሰዉለት በጠማምውው ትርክት ተባባሪ በመሆን አማራይዜሽን በሚል የጥቃቱ ተባባሪ መሆኑ ይታወቃል:: ስለዚህ ፋኖ የለም የምትል ሰው ዛሬ ተመልሰህ ስለፋኖ ትግል ከምትገንረን የህዝብ ተወካይ በሃቅ ከሆንክ ለሚተረደው ህዝብ ሞግት:: ሸዋ ጎንደር ወሎ ጎጃም በሚል የምትከፋፍለውን የሚሰማ የለም:: የወያኔና የብልግናው ተልእኮህን ማስፈጸም ከሆነ በተበላ እቁብ ማለቅለቕን አቁም ግፈኛች ሲያርዱት አማራ ብለው እንጅ ጎንደሬ ወለዮ ጎጃሜ ሸዋ ብለው አይደለም አትከፋፍልያንተና የልደቱ አየነቶቹ የፓርላማ ማዳመቂያዎች ለህወቱ ሳይሳሳ በረሃ ወርዶ የሚታገለውን ታጋይ እስክንድር ለመተቸት ብቃት ሞራል የላችሁም::
    ታጋይ እስክንድርም በውጭ ያለነው ድጋፍን ባግባቡ ከሃገር ቤት የፋኖ ታጋዮች ጋር በማቀናጀት የውጭው ትግል ከፕሮፓጋንዳና ከፋይናንስ ውጭ በፋኖ በረሃ በሚዋደቀው የትግል ሂደት ጣልቃ ሳይገባ በአፍሪካ ምክር ቤትANC በተባበረ ዘይቤ ያለውን ዘረኛ ጸረ አማራ ጸረ ኢትዮጲያ ስርአት ከሁሉም የኢትዮጲያ ህዝቦች ጋር በማቀናጀት ይፋለሙ ዘንድ ምክሬን ሰጣለሁ::
    ጨቁዋኙን ፈርኦንን ባህር ያሰመጠ ትእቢተኛውን ናቡከደነጾርን ሳር ያሰበላ የግፉአን አምላክ ከሃዲውን አብይና ግፈኛውን ኦሮሙማ ተብዬ በኦሮሞ ወገናችን ስም የሚጨፈጭፈውን ግፈኛ ይፍረድበት::
    ፓስተርዲጎኔ ሞረቴው

  2. ግርማ ካሳ ብዙ አስተምረኸናል እስክንድር ላይ እንዲህ ያለ ዘመቻ ምክንያቱ ምንድነው? እስክንድርን ካንተ በላይ የሚያውቀው የለም ብልጽግና አትለው ግምቦት 7 ወይም ኦነግ እኛ የተመቸ ጊዜ እየመረጥን የምንተኩስ ሰዎች ሁነን ቤተሰብና ልጁን ምቾቱን ለሃገር ሲል የተወውን ጀግና ለምን አትጨነቁለትም? ከናንተ አስተሳሰባችሁ እንኳን ባይዛመድ ለምን በተለየ መልኩ ሃሳብችሁን አታቀርቡም? ከትግሬዎች ተማሩ እንጅ። አንድ ሚልዮን ትግሬ ያስፈጁ ህወአቶች ትግሬዎች ምንም ሳይሏቸው እስክንድር ላይ የሚዘመተው ማንን ለማስደሰት ነው? እስክንድር አድርባይ ቁሳዊ ናፋቂም አይደለም ስለዚህ አንተን ብቻ ሳይሆን ሌሎችም ረጋ በሉ። መቼም ይሄ ዩ ቲዩብ እያለ ኢትዮጵያ ሰላም ታገኛለች ማለት ዘበት ነው። ቢያንስ አታስቁብን ፖለቲካንና የፖለቲካ አካሄድንም እወቁ እንጅ። ነገ ደግሞ ማን ሊኮነን ይሆን? አማራ በዚህ መንገድ መከራው ገና ነው ማለቂያም የለውም። አብረሃ በላይ ሚኒስቴር ሁኖ ይሄን ሁሉ ሲያሳልጥ ዝም ብላችሁ ዮሃንስ አብረሃ ለነ ባይደን የተሳሳተ መረጃ ሲሰጥ እዛላይ ሳትበረቱ አንድ ምስኪን ላይ ይሄ ሁሉ ውርጅብኝ አስፈላጊ አይመስለኝም።

  3. አቶ ግርማ፣ የጽሁፍህ ዓላማ ምንድን ነው ? ለመከፋፈል ? ለማዳከም ? ለመሆኑ እስክንድርን ታውቀዋለህ ? ከቅንጅት ዘመን ጀምሮ የእሱን ውለታ ታውቃለህ ? የአንተን ስም ያየሁት በቅርቡ በበጎ ነበር። ሌላ ዓላማ ከሌለህ በስተቀር ባደረግኸው አስተዋጽኦ ከእስክንድር ጋር የምትወዳደር አይመስለኝም። ግሩም በሳል ወጣት፣ ግሩም ዜጋ፣ ሰፊ ሕዝባዊ አመለካከት ያለው፣ ከመንደርተኛነት የጸዳ ኢትዮጵያዊ መሆኑን በሚሊዮን የሚቆጠረው የአዲስ አበባ ሕዝብ ይመሰክራል። በነገራችን ላይ፣ አባቱም አቶ ነጋ ፈንታ ጥሩ ምሁር ኢትዮጵያ እንደነበሩ ሲወራ እሰማለሁ። ግድ የለህም፣ እስክንድር ላይ ትችቱ ይቆይ ! እንደ ስሜ፣ የምመርጠው የኢትዮጵያውያንን አንድነት ነው። በአንዲንነት አገራችንን ገነት ማድረግ እንችላለን፣ ተከፋፍለን ግን ለጠላት ሲሳይ እንሆናለን። እንደሰማሁት፣ ይህን ማየት አያስቸግርህም። አንተም ለሠራኸው በጎ ሥራ ምስጋና ይድረስህ ! የሰውን በጎ ስራም አትንካ !

  4. እንዴ ይሄ ሰው ፎርጅድ ግርማ ካሳ ነው እንዴ? የትግሬ አመጣጡ ብዙ ነው።

  5. “እስክንድር ነጋ እመራዋለሁ የሚለው የአማራ ህዝባዊ ሰራዊት የሚባል አለ ወይ?”

    አጭር መልስ፤

    የለም! የለም!የለም!የለም!የለም!የለም!የለም!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share