March 18, 2024
7 mins read

እስክንድር ነጋ እመራዋለሁ የሚለው የአማራ ህዝባዊ ሰራዊት የሚባል አለ ወይ?

ግርማ ካሳ

ይህ ድርጅት፣ በወረቀት እንጂ በተግባር ያለ አይመስለኝም ብዬ ጽፌ ነበር፡፡ “ተሳስተሃል፣ መረጃው ስለሌለህ እንጂ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው” ተብያለሁ፡፡ እርማቱን ተቀብያለሁ፡፡ በመሆኑም “አላውቅም” ከማለት ውጭ “ያለ አይመስለኝም ወይም የለም” ብሎ መነገር አልችልም፡፡ ስለዚህ ብዙ መረጃ ስለሌለኝ እንዲህ ነው እንዲያ ነው ብዬ ለመናገር ይከብደኛል፡፡

ሆኖም ግን መረጃ ስላገኘሁበት ጉዳይ ግን መናገር እችላለሁ፡፡ በነ ሻለቃ መከታው ማሞና መምህር ምንተስኖት የሚመራው የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ፣ ከዚህ “የአማራ ህዝባዊ ሰራዊት” ከሚባለው ጋር ግንኙነት የለውም፡፡ ወንድም እስክንደር ነጋ ፣ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ወታደራዊም ሆነ ፖለቲካዊ አመራር ውስጥ አንዱም፣ ጋር የለበትም፡፡ ከጎጃም ወደ ሸዋ ሲመጣ፣ የህዝብ ልጅ፣ የአገዛዙ ታርጌት በመሆኑ ጥበቃ ለርሱ መድበው የርሱን ደህንነት ከመጠበቅ፣ አልፎ አልፎ አንዳንድ ህዝባዊ ስብሰባዎች ላይ ፣ እንደ ታዋቂ በህዝብ ተወዳጅ ሰው፣ የሸዋ ፋኖዎችን ወክሎ ሳይሆን ራሱን ወክሎ ንግግሮች እንዲያደርግ ከማመቻቸት ውጭ፡፡

ከዚይ ባለፈ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ መሪዎች፣ ሌሎች እንደሚያደርጉት፣ በየቱቡና ሜዲያ ወጥተው የህዝብ ልጆች፣ ታጋዮች ላይ አስተያየት እንዲሰጡ ተፈልጎ ከሆነ አያደርጉትም፡፡ ልዩነቶች፣ ክፍተቶችም ካለ የውስጥ ጉዳይ ነው በሚል ችግሮችን በውስጥ፣ በውይይት ለመፍታት ይሞክራሉ እንጂ፣ በየሜዲያው ለአገዛዙ ግባት የፖለቲካና የፕሮፖጋንዳ ትርፍ የሚስጥ ስራን አይሰሩም፡፡ የነርሱ ትኩረት አገዛዙ ላይ እንጂ ሌሎች ፋኖዎች፣ ሌሎች ለህዝብ የሚታገሉ ወገኖች ላይ አይደለም፡፡

ከዚህም የተነሳ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝን፣ ከአማራ ህዝባዊ ሰራዊት ከተባለው ጋር በማገናኘት፣ የአማራ ህዝባዊ ሰራዊት የተባለው ስብስብ አመራሮች ለሰሯቸው ወይንም ለሚሰሯቸው ስህተቶች፣ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ጋር ማገናኘት ተገቢ አይደለም፡፡

በተቃራኒው ደግሞ አንድ ዋሺንገትን ዲሲ ያለ ወንድም አለ፡፡ አገሩን የሚወድ ታጋይ ነው፡፡ ቢያንስ በውጭ፡፡ ግን የፖለቲካ ብስለት የሌለው፣ ምን አልባት የጤና ችግር ያለበት፣ ስራ ፈት ሰው ነው የሚመስለው፡፡ ሺመልስ ለገሰ ይባላል፡፡ ይህ ሰው የ እስክንድር ነጋ የቅርብ ሰው ነኝ ባይ ነው፡፡ ሆኖም የእስክንድር ነጋ የቅርብ ሰው ነው ማለት፣ እስክንድር ነጋ ነው ማለት እንዳልሆነ በትልቁ ሊሰመርበት ይገባል፡፡ ብዙ ፣ ካድሬ ይመስል፣ “እስክንድር፣ እስክንድር” የሚሉ አሉ፡፡ ይህም ሰው እንደዚያ ነው፡፡ ይህም ሰውም ሆነ በዳያስፖራ ያሉ ቢጤዎቹ፣ ሌላ የራሳቸው አጀንዳ ይኖራቸዋል፡፡ እነርሱ በሚያደርጉት ነገር ግን እስክንድር ነጋ ላይ ማላከክ ተገቢ አይመስለኝም፡፡

እነዚህ ሰዎች “የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ” በዳያስፖራ የድጋፍ ማሰባሰብ እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ፣ ለእስክንድር ነጋ ጥበቃ ሲያደርግ የነበረና ምን አልባትም ወደሌሎች ጠቅላይ ግዛቶች እስክንድር ካልሄደ፣ ለእስክንድር አሁንም ጥበቃ እያደረገ ያለ መሆኑን ሳያውቁ ቀርተው አይደለም፡፡

ታዲያ፣ ” የእስክንድር ነጋ ደጋፊዎች ነን”፣ እያሉ፣ እስክንድር ነጋን እየጠበቀ ያለ ኃይልን አለመደገፍ ፣ እዙ እያደረገ ያለውን የድጋፍ ማሰባሰቢያ ለማጨናገፍ መሞከር ምን ሊባል ይችላል ?? ጸረ እስክንድርነት፣ በእስክንድር ስም የሚደረግ የአብይ አህመድና ዘረኛው አገዛዝ ጥቅም የሚያስጠብቅ ፣ ብልጽግናዊ፣ ኦህድዳዊ አሳፋሪ ስራ ካልተባለ በቀር !!!!

ወገኖች እኔ ይሄንን በምጽፍበት፣ እናንተም በምታነቡበት ጊዜ ፣ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ውስጥ ያሉ ፍከለ ጦሮች ከአገዛዙ ጋር አንገት ለአንገት እየተናነቁ ነው፡፡ ህይወታቸውን አወራረደው፣ ለአገር፣ ለህዝብ ትልቅ ዋጋ እየከፈሉ ነው፡፡ እነርሱን አለመደገፍ፣ ከነርሱ ጎን አለመቆም አይቻልም፡፡

ከዚህ በታች ያለውን ማስታወቂያ እናንንብ፡፡ ባር ኮዱን በስልካችን ስካን በማድረግ እንዴት መደገፍ እንደሚገባ ወደ ሚያሳይ ገጽ ይሄዳሉ፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

Go toTop