“እርሱን ስሙት” ለሰይጣናዊ ዘረኛ መሪ ሲጠቀስ ዝም ማለት አልችልም

አስቀድሜ  ለተባረከው የጌታችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት አክባሪዎች መልካም በአል እላለሁ::  የጌታው የመሰሪ አጭበርባሪ የወያኔ ኢንሳ ስለላ ቢሮ ጀምሮ ባልደረባው ተመስገን ጥሩነህ  የተቀደሰው የጌታን ቃል ለዚህ ከሃዲ በሃገራችን ከታዩ መሪዎች ሁሉ የከፋ ሸፍጠኛ አብይ አህመድን ስሙ ብሎ የጌታን የሰላም የፍቅር ቃል ከማቅረብ የበለጠ  በሃይማኖታችን ላይ ማፌዝ  ማሳት የለም::
ባለፈው ይህ አሰመሳይ አብይ ኣሀመድ በሙስሊሞቹ አረፋ በአል የተሰዋልን  ብሎ ኢስማኤልን ምሳሌ ሲጠቅስ  ከሃገር ቤት የአብይ አጫፋሪ ፓስተሮች አንዳቸውም ምላሽ ያልሰጡ ሲሆን የራሱ ሙሉ ወንጌል ወጣት ፓስተር ብቻ  ተገቢ ሙግት ሲያቀርብ ደግፈነዋል::
ዛሬም  በየስፍራው ያላችሁ የሃይማኖቱ መሪዎች ፓስተሮች ቀሳውስት  ይህን ዘላባጅና ምንደኞቹን ህዝባችንን የሚያባሉትን  በሃስተኛ ፊት ለፊት በሚታይ ማጭበርበሪያ ሲያስቱ ዝም ብትሉ ከፈጣሪም ከታሪክም    ፍርዳችሁን ታገኛላችሁ::
ናዚ ሂትለርን ፋሽስት ሙሶሎኒን ያልገሰጹ ጭራሽ የተባበሩ ዛሬ ድረስ ቤተሰባቸው ዘመዶቻቸው ሲሸሸማቀቁ እንደሚኖሩት የአናንተም እድል ፈትና ይህ ነውና ዛሬ ሳይመሽ በጊዜ በወቅቱ ይህን ጨካኝ  አታላይ ዘረኛ ግፈኛ ኣአጭበርባሪ አብይ አህመድን በማውገዝ ለሚታረደው ህዝባችን  ድምጽ ሁኑ::
ዲጎኔ ሞረቴው ፓስተር ከሚድ ዌስት ኣአሜሪካ
ተጨማሪ ያንብቡ:  አወዛጋቢው የመንግስት ውሳኔ - ፋሲል የኔዓለም

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share