ቋሚ ሲኖዶስ አላወግዝም አሳስባለሁ እንጅ አለ

ሰሞኑን አቡነ ሉቃስ እንዲወገዙ የሚጮኹ የብልጽግና ገላግልት በርከት ብለው ነበር። ቤተ ክህነቱ በቤተ መንግሥቱ በኩል ይቀልለናል ያሉት ውትወታቸው በዝቶ ሰነበተ።
ቋሚ ሲኖዶስ ግን ዛሬ ባወጣው መግለጫ
“በወንድማማችነት መካከል ጠብን ከሚዘሩ ጥላቻንና መራራቅን ከሚያሰፉ ንግግሮችና ድርጊቶች በመቆጠብ ኹሉም የማኅበረ ሰብእ ክፍል እግዚአብሔር ለሀገራችን ፍጹም ሰላምን ይሰጣት ዘንድ በጸሎት እንዲተጋ” አሳስባለሁ ብሏል፡፡
“ከምን ጊዜውም በላይ ሰላምና ፍቅር በሀገራችን እንዲሰፍን በአንድነት ኾነን የምንሠራበት ወቅት ላይ በመኾናችን በመጪዎቹ ዐበይት በዓላት፣ በዘወትሩ መንፈሳዊ አገልግሎት ኹሉም በየደረጃው ያላችሁ የቤተ ክርስቲያናችን አባቶችና አገልጋዮች . . . በየዐውደ ምሕረቱ ሰላምንና እርቅን በመስበክ በሀገራችን ኢትዮጵያ ያለው ችግር እንዲወገድ፣ ማኅበራዊ ሰላም እውን እንዲኾን የበኩላችሁን ጥረት እንድታደርጉ ቋሚ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል” ሲልም መግለጫውን ደምድሟል።
በዚህም የቤተ መንግሥቱ ፍላጎት ሙሉ በሙሉ ከሽፏል። አሳስባለሁ አለ እንጅ አውግዣለሁ አላለማ። ደግሞም እኮ ለኹሉም የተላለፈ እንጅ ለእገሌ ብቻ አይደለም። ውግዘት ሲጠብቁ ማሳሰቢያ ኾነባቸው። ፊት የሚያጮል መግለጫ።

ዓባይነህ ካሤ – ዲን

ተጨማሪ ያንብቡ:  ግርማዊ ቀዳማዊ ሃይለስላሴ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ፊልድ ማርሻል

1 Comment

  1. እረ ጎበዝ ፍርሃት አይሸብበን እንጅ የበዛ ምስጋና የሚገባቸው ለሆዳቸው ያላደሩ አባት በአቶ ዳንኤል ክብረት አማካይነት እንዲሸማቀቁ ሲደረግ የአንድነት ሃይሉ የት ነው ያለው? በተገኘው የመገናኛ መስመር አድናቆትን ከማጉረፍ ባሻገር አለንሎት ሊባል ይገባል።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share