July 10, 2023
5 mins read

ምክር ቢጤ ለዶክተር ደሳለኝ ጫኔ፤ ካሳማ ጋር ትግል አትግጠም

ያሳማ ዋና ፍላጎት ተጨማልቆ ማጨማለቅ ስለሆነ፣ ካሳማ ጋር በጭራሽ አትታገል፡፡

(Never wrestle with a pig.  You both get dirty and the pig likes it.  George Bernard Shaw)

abiy ahmed 4 1 1 1 1 1

አቶ ኤርምያስ ለገሰ በገዛ ራሱ ፈቃድ፣ ራሱን በራሱ የወያኔና የኦነግ አሳማ አድርጓል፡፡  አሳማ ሲባል ደግሞ አረንቋ ውስጥ መጨማለቅ ስለሚወድና ከፍተኛ እርካታ ስለሚሰጠው፣ ዋና ምኞቱ ተጨማልቆ ማጨማለቅ ነው፡፡  ስለዚህም ፀራማሮቹ ወያኔና ኦነግ ላቶ ኤርምያስ ከሰጡት ተልዕኮወች ውስጥ አንዱ፣ ካማራ ሕልውና ታጋዮች ጋር አተካራ ገጥሞ፣ ራሱ ተጨማልቆ እነሱን በማጨማለቅ ባማራ ሕዝብ ዘንድ ያላቸውን ተቀባይነት ዝቅ ማድረግ ነው።

ወያኔና ኦነግ ላቶ ኤርምያስ የሰጡት የመጀመርያውና ዋናው ሥራ ኢትዮ360ን ማምከን ነበር፡፡  ያቶ ኤርምያስ ሙከራ ግን ኢትዮ360ን ከማምከን ይለቅ ስላገነነው አለቆቹ ወያኔና ኦነግ ከመጠን በላይ ቅር ተሰኝተውበታል፡፡  ስለዚህም አቶ ኤርምያስ ቅር የተሰኙበትን አለቆቹን ለማስደሰት የማይፈነቅለው ዲንጋ፣ የማይቆፍረው ጉድጓድ የለም፡፡  ከዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ጋር አተካራ የገጠመውም በዚሁ ምክኒያት ነው፡፡  ዐላማው ደግሞ ራሱ ተጨማልቆ ዶክተር ደሳለኝን በማጨማለቅ፣ ዶከተር ደሳለኝን አራክሶ ያማራ ለምድ የለበሰውን ፀራማራውን በለጠ ሞላን ለማዋደድ ነው።

ያማራ ሕዝብ የሕልውና ጠላቶቹን ወያኔንና ኦነግን በተመለከተ ያሉት ምርጫወች ሁለት ብቻ ሲሆኑ፣ እነሱም ወይ እነሱን ማጥፋት ወይም በነሱ መጥፋት ናቸው፡፡   ወያኔነና ኦነግን በማጥፋት ራሱን ከጥፋት ለማዳን ደግሞ ከወዳጆቹ ጋር ይቅርና ከጠላቶቹ ከራሳቸው ከወያኔና ከኦነግም ጋር ቢሆን መተባበር የግዴታ ውዴታው ነው።  እሾህን በሾህ ነውና፣ ወያኔን በኦነግ ወይም ደግሞ ኦነግን በወያኔ ማጥፋት ከቻለአንድ የሕልውና ጠላት ተነቀለለት ማለት ስለሆነ፣ ዕደሉ ሊያመልጠው አይገባም፡፡

ስለዚህም፣ ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ የኦነግን ጉዳይ በይደር ይዞ፣ ጠመንጃ እንግቦ፣ ዝናር ታጥቆ ወያኔን ሊወጋ መዝመቱ በግልጽ የሚያሳየው፣ እሱ ራሱ እንዳለው “ታማኝነቱ ላማራ ሕዝብና ለህሊናው” የሆነ፣ ያማራ ሕዝብ መዳኛ መንገድ በግልጽ የታየውግቡን (goal) ጠንቅቆ የሚያቅ፣ የተዋጣለት ትልመኛ (strategist) እና ስልተኛ (tactician) መሆኑን እንጅ መርሕ አልባ መሆኑን አይደለም፡፡  መርሕ አልባ የሆኑት የወያኔና የኦነግ ቅጥረኛ የሆነው አቶ ኤርምያስ ደግሞ ስለ መርሕ ቢያወራ ጆሮ /ሊሰጠው/ አይገባም፡፡

ስለዚህም ውድ ወንድሜ ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ፣ ካፈርኩ አይመልሰኝ ከሚለው፣ የጨምላቃ አሳማ ባሕሪ ከተጠናወተው ካቶ ኤርምያስ ለገሰ ጋር እሰጥ አገባ ገጥመህ ተጨማልቆ እንዳያጨማልቅ በትህትና እመክርሃለሁ፡፡  አፍ ሲከፈት ይታያል ማንነት እንዲሉ፣ አቶ ኤርምያስ ለገስ ስድ አፉን በመክፈት “ሱሪውን አውልቆ ቅቤ በጠጣ ዱላ ደበደበው” እያለ ጭራቅ አሕመድን በማሞገስ እውነተኛ ማንነቱን እሱ ራሱ እያሳየ፣ አንተን ያዋረድ ቢመስለውም እሱን ራሱን ይበልጥና ይበልጥ ያዋረደ ስለሆነ፣ ንቀህ ተወው፡፡  አንሶ እንዳያሳንስህ መልስ እንዳትሰጠው፡፡

 

ካልተውት በስተቀር ንቀው ብለው ቀላል

ትንሽ ሰው ትንሽ ነው አንሶ ያሳንሳል፡፡

 

መስፍን አረጋ

[email protected]

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop