ድሮስ ፤  ከእባብ እንቁላል እርግብ ይገኛልን ??? – ሲና ዘ ሙሴ

Abiy Ahmed
ድሮስ ፤  ከእባብ እንቁላል እርግብ ይገኛልን ?

“በሲና ተራራ
በዛ በከፍታ
በዙፋንህ ሆነህ
ክብርህን አየነው ”

ያኔ ከሲና ተራራ የመጣው አይነት መልዕክት ፤ ለዛሬው ዓለም በእጅጉ ያሥፈልጋል ።

ስለ ተራ ሞቹ ሰው ማን ደንታ አለው ? መንግሥታት እንደሆነ አእምሮአቸው የተያዘው በዝና ነው ። ያውም በሞላጫ ዝና ። ዝና ሞላጫ ነው ። ትላንት ለህዝብ  ያሥተዋወቀህ ፣በከፍታ የናኘው  ዝናህ  ነገ ምደር ላይ ተከስክሶና አልባሌና መሳቂያ ሆኖ ታገኘዋለህ ። ነገ ሥልህ በዘመን ብዛት እጅግ የራቀውን ፣ የነጎደውን  ነገ ነው ። ከ10 ትውልድ በኋላ  ያለውን ነገ ። በዛ ነገ ፣ የማንኛውም መንግሥት ዝና ይረሳል ። …

በነገ ዕይታ ፣ ህይወት እንቆቅልሽና ድራማዊ ናት ።

ደሞም ተገንዘብ ፣ በህይወት ዑደት ውስጥ  ሰው ከትንሾ ትል የሚለይበት የህይወት ዕደት የለም ። ሰው እና ትል በህይወት ዑደት ተመሳሳይ ሽክርክሪት ነው ያላቸው ። ይወለዳሉ ፤ ያድጋሉ ፤ ይምታሉ ። ( ሳያድጉ የሚሞቱ ወይም የሚቀጩ ህይወቶች በሁለቱም ወገን እንዳሉም ይታወቃል ። )

በመወለድ ፣ በማደግ እና በመሞት ደረጃ ሰው ከትል እኩል ነው ።

ይኽ እውነት ቢሆንም በማህበራዊ ኑረው የበለጠ ትል የሚያደርጉት እውነቶች ደግሞ አሉ ።

አንደኛው እንደትል  ተነጂነቱ ነው ። ልምጭ እና እሥር ቤት ያለው መንግሥት ሰውን በየቀኑ እንደትል ሲነዳው እናያለን ።

ለምሣሌ ፣ በሚያሳዝን መልኩ ከፊሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ፣ ከደርግ ሥርዓት ጀምሮ ሳይወድ በግዱ በየጎጡ መንግሥት እያስፈራራው ለድጋፍ እና ለተቃውሞ ሰልፍ እንደ ትል ወጥቶ ይርመሰመሳል ። በተለይም በኦሮሚያ ክልል ። ተራው ህዝብ ካድሬዎች የፃፉትን ወረቀት ይዞ በግድ በአደባባይ እንዲወጣ እና በማይገበው ቋንቋ ከቲባዎቹ ዘፍነውበት ወደ ቤቱ ይመለሳል  ። በነሱ ቤት የቀደመን ጭቆና እና ትምክህት በተመሳሳይ መልኩ መመለስ ፍትሃዊ ና ዴሞክራሲያዊ ነው ።  ። ይጮኻል ። ምንም ባልገባውና በማያውቀው ጉዳይ ውስጥ ገብቶ እንዲፈተፍት ይደረጋል ።  ባልገባው ጉዳይ “ በግንቦት ሃያ “  ለመከላከያ ድጋፍ ለማድረግ ሰልፍ ወጣ ይባላል ።

ይህ የለየለት ሸፍጥና የጅላንፎ ፕሮፓጋንዳ ነው ። ዛሬም “ አብይ መራሹ ፣ የብልፅግና  መንግሥት “ እንደ ወያኔ እና እንደ ደርግ በውሸት ፕሮፓጋንዳ የሚያምን  መንግሥት የሆነው ከሥሪቱ የተነሳ እንደሆነ አውቃለሁ ። ያልተዘራ አይታጨድምና !  ( መቼም አብይ አህመድ በአንድ እጁ ማጨብጨብ አይችልም ። )

በአንድ እጅ ማጨብጨብ ባይቻልም ፣ ጠ/ሚ  አብይ አህመድ የአገር መሪ በመሆኑ ሁሉም አካባቢ ፣ ጎጥና ቀበሌ ውስጥ ሳይቀር ፤ በሚጠፋው ጥፋት ጣታችንን ወደ ሰውየው  መቀሰራችን አይቀርም ። የህግ አሥፈፃሚው ቁንጮ በመሆኑ !

ዛሬ አብይ አህመድን በመልካም የሚያነሰው እጅግ ጥቂት ሰው ነው ።  በተደጋጋሚ ከህዝብ ፍላጎት ውጪ በወሰነው ውሳኔ የተነሳ ከህዝብ ጋር ተጣልቷል ። አንዳንድ ክልሎች ውሥጥ ያለው ህዝብም   ከወገኖቹ ሥደተሰ ፣መፈናቀልና ምት የተነሳ   አምርሮ ጠልቶታል ።  እርሱ ግን ዛሬም ህዝብን በግዳጅ ( ለቅንጥብጣቢ ሲሉ በሚጮሁ ምሥኪነሰ ህድ አደሮች እየታገዘ … ) በኦሮሚያ ክልል በግድ  ሰልፍ በማሶጣት ፣ “ ህዝብ ለመከላከያ ያለውን ድጋፍ ገለፀ “ ቀማለት ፕሮፖጋንዳ ይሰራል ።

ህዝብ የአገር መከላከያን መቼ ጠልቶ ያውቃል ? ” መከላከያ ማለት የኢትዮጵያ ህዝብ ልጅ ማለት አይደለም ወይ ? ”

በእውነቱ መንግሥት ውሥጥ ከትል ያልተሻሉ ሰዎች ናቸው የተሰገሰጉት ማለትም ይቻላል ። ዛሬ አሰስና ገሰሱ ነው መንግሥት የሆነው ። ይህንን የምታረጋግጡት ስራዬ ብላቸሁ የኦሮሚያ ከተሞች ምሽቶች ምን አሰንደሚመሥሉ ስታዩ ነው ።

“ በኦሮሚያ  ክልል ከተሞች  በምሽት ፣ ዘራፊዎች ሥለዘረፋቸው ሳያፍሩ በየመሸታ ቤቱ  ያወራሉ ።  እጅግ ጉድ የሚያሰኝ የዘረፋ ፣ የመሬት እና ቤት ሽያጭ  ታሪክ ያወራሉ ። ከሁሉም የመንግስት ተቋማት በጨረታ ሥም ፣ በግንባታ ሥም  በተሽከርካሪ ጥገና እና ነዳጅ ሥም  ረብጣ ብሮች ተሞጭልፈው  የሚመነዘሩት ና የቃል ኪዳን ውል የሚፈረምባቸው  በፍየል ቀርጥ ቤቶች እና በትልልቅ ሥጋ ቤቶች ውሥጥ ነው  ። ነጋዴዎች በሥጋ እና በመጠጥ ሥም እጅግ የሚዘገንን ዝርፊያም ያካሂዳሉ ። … ( የአገር ውሥጥ ገቢ ሰብሳቢ ቀረጡ ላይ በደንብ ይያዝልን ። እንላለን ። )

ባይገርማችሁ ፣ አንዳንድ እጅግ ያጌጡና በመብራት ያሸበረቁ  የፍየል ሥጋ መሸጫ ቤቶች   ፣   ጥብሥ  ብቻ ሳይሆን  ዝሙትም  ያቀርብላችኋል ። አንዳንዴም ካላሥተዋላችሁ ፣ የፍየል ጥብስ ብለው የሚሸጥላችሁ   ፤  የከረመ የበሬ ሥጋ ነው ። በሥካር ልብ ልታውቁ አትችሉምና ! !  እንኳን የበሬ ሥጋ ይቅርና ጨጓራ የበዛው የበሬ ሥጋ ቢቀርብላችሁ ወይም አንጀት ተቀላቅሎ በደበዘዘ መብራት ቢሰጣችሁ ከመብላት ውጪ አማራጭ የላችሁም ። (  አይጥ ጠብሰው ቢሰጧችሁም በፍየል ጥብስ ሥም በስካር መንፈስ እንክት አድርጋችሁ ትበላላችሁ ። )

በአንዳንድ   የመዝናኛ ቤቶችም የመጠጡ  ጥራት እጅግ የሚያጠራጥራችሁ …ለጤና ማጣት የሚዳርጋችሁ …በውስኪ ሥም የተቀላቀለ አረቄ የሚቀርብላችሁ ። በቢራ ሥም ከዚህ እና ከዛ የተበወዘ ጭላጭ የያዘ ጠርሙስ በግርግር የሚቀርብላችሁ መሆኑንን አታስተውሉም ። …

ይኽንን ማጭበርበር መቆጣጠር ያለበት ህግ አሥፈፃሚው  ግን የዕለት ከዕለት ሥራውን አይከውንም ። በህግ ማሥከበር ሥምም  ከሁለት ሰዓት በኋላ  ኪሱን ለማስከበረ በትጋት የተዘጋጀ ፣ ፖሊሥ ከጎጥ ሲቪል ግብረ ሃይልና በህዝብ  መዋጮ የተቀጠረ ሚሊሻ ጋር በየአሥፓልቱ ተሰማርቶ ይገኛል ። …

በየቀበሌው ሁሉም ሚሊሻ ና ፖሊስ ከወዶ ገቡ ሲቪል ሴትና ወንድ ጋር በአብረቅራቂ ልብስ ተከፍኖ    ወጪ ወራጁን በመፈተሽ ፣ መኪና አሥቁሞ በመበርበር መንገደኛን ያንገላታል ። ባሥ ሲልም ፣ ” የውሃ መግዣ ፤ የብርድ መከላከያ ፤ ስጡኝ ። ”  እያለ ይቀፍላል ። ( አይደረግም ካልክ ድርጊቱ ያጋጠማቸውን የብሾፍቱ ባለሥልጣናት ጠይቅ ። የብሾፍቱ ከተማ መግቢያ ፍተሻ ከአዳማ የተሻለ እና በፖሊስ ብቻ የሚደረግ መሆኑንንም እወቅ ። )

አንዳንዱን ከተማ በተለይም ከአዳማ ጀምሮ ያለውን ሥታሥተውል ፤ ይኽ አገር የአልሻባብ አገር ነው እንዴ ? በሰላማዊ አገር አሥፓልት ላይ የሚፈጠር ህገ ወጥነትን በእንደዚህ አይነት ፍተሻ መከላከል ይቻላል እንዴ ? ህገ ወጦችስ ፍተሻ መኖሩን እያወቁ በአሥፓልት መንገድ እንዴት ደፍረው ይጓዛሉ  ? ህገ ወጦችን ፣ ሌቦችና ዘራፊዎችን የሚቆጣጠር  የሚያድን …ልዩ ግብረ ሃይል መንግሥት ፣ እንደመንግሥት እንዴት ማቋቋም አቃተው ? ብለህም ትጠይቃለህ ።

ምላሽህም ድሮስ  የጃጁና ያውና አንድ የሆኑ ፣  ሆዳም ና ዘረኛ ካድሬዎችን ሰብስቦ ፣ ይኽንን ታላቅ ና በለምጡቅ አእምሮ ህዝብ በድፍረት  የሚመራ ፓርቲና   መንግሥት ከዚህ በላይ ምን ማድረግ ይችላል ? የሚል ጥያቄ አዘል መልስ ይሆናል ?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop