May 25, 2023
5 mins read

በኢትዮጵያ “ኢህአዴግ አስካለ ” የመከራ ቀንበር ይኖራል !

ኢህአዴግ ስል “የሞተዉን አያ ይለዋል ” እንደሚለዉ የአገራችን ብሂል ከየት የመጣ ወይም የት ነበርክ  ብሎ አንዳንድ አንባቢ እንደሚደመም እገምታለሁ ፡፡

እኔ ግን ድሮዉንም ቢሆን ከዕባብ ቅርጫት ሙሉ ዕንቁላል ርግቦች እንዴት አሉ ብየ ተገረምኩ እንጂ ኢህአዴግ እንዳልተቀየረ ግን የዘመናት ብሄራዊ ችግር እና ብሄር መር ዘረኛ አገር እና ህዝብ ጠል ድርጂቱ  ኢህአዴግ እንደነበረ ከአንዱ ጉልቻ በቀር ድመት መንኩሳ….እንዲሉ ቆዳዉን ለዉጦ ፤አመሉን ዉጦ ከህዝብ ስሜት ጋር ማዋኃዱን ነዉ የምናዉቀዉ ፡፡

ኢህአዴግ በዉስጡ የፀነሰዉ በጥላቻ እና በስጋት የተረገዘ አግላይ እና በዳይ የፖለቲካ ትርክት በመሆኑ  ቆዳዉን ቀርቶ ቢጣድ የማይበስል የአህያ ጭንቅላት መሆኑ ካለመረዳት ሳይሆን ለራሱ ሲል በአገር እና በህዝብ ላይ ለሶስት አሰርተ ዓመታት ያደረሰዉን ፈርጀ ብዙ ጥፋት እና ክህደት አምኖ ህዝብን ይቅርታ ይጠይቃል ለዚህም ተገቢዉን የሞራል እና የቁሳአካል ካሳ የሚያደርግ ሆኖ ላደረሰዉ ወንጀል ህዝብ ምህረት አድርጎለት  አገሪቷን እና ህዝቧን ከጥፋት ለማዳን በሚደረግ ብሄራዊ ጥረት ከአናቱ  አስከ ቀርጭምጭሚቱ በንስኃ ታጥቦ መንገድ ይለቃል የሚል ግምት ነበር ፡፡

ዳሩ “ድመት መልኩሳ ዓመሏን አትርሳ” ሆኖ ለአመታት በብሄራዊ አንድነት ፣ በህዝቦች ሉዓላዊነት ፣ በዜጎች በአገራቸዉ ሰርቶ የመኖር ፣ በማንት ተኮር ጥቃት ፣ ስደት ፣ ማፈናቀል …በማፋፋም ቀጥሎበት ዛሬ ላይ ተደርሷል፡፡

ርግጥ ኢህአዴግ አስካለ  ግንቦት ፳ ቀን አስራ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ሶስት ዓ.ም. ጀምሮ በአዋጂ የተተከለዉ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን የማናጋት እና የማጥፋት ሴራ መቀጠሉ  ዕንግዳ ባለመሆኑ የሚገርም ባይሆንም ይህን የጥፋት እና የሞት አዋጂ እንደ ድል ቀን ተቀብሎ በዚህ ምክነያት በኢትዮጵያ ዳር ድንበር መደፈር ፣ በኢትዮጵያዉያን በጦርነት ፣ በርሀብ ፣ በግጭት ፣ በዘርፍጂት …በመሳሰሉት ወንጀሎች ራሱ ስርዓቱ ተጠያቂ መሆን ሲገባዉ እና በስርዓቱ ቸልተኝነት እና ይሁን ባይነት በማንነታቸዉ እንዲሞቱ ፣ እንዲሰደዱ ፣ እንዲፈናቀሉ ፣እንዲገለሉ….ወዘተ ለሆኑት የሠላሳ ዓመት ሰማዕታት መታሰቢ እንዲደረግ ባለመጠየቁ  ዛሬም ይህ ሠባዊ እና ብሄራዊ ጥፋት በዓይነት እና ፍጥነት  ዕጥፍ  እንዲቀጥል ፈቃድ ተሰጥቶታል ፡፡

በመጨረሻም በማንኛዉም መመዘኛ በተድበሰበሰ እና በጥገናዊ ለዉጥ የስልጣን ልዉዉጥ እና መገለባበጥ ካልሆነ በቀር የዚች አገር እና ህዝብ መከራ  እንደ ተራራ ሲገዝፍ እንጂ ሲቀረፍ ማየት የጨለማ ሩጫ ስለሚሆን ኢህአዴግ ከግንባሩ አስከ ስሩ ካልተመነገለ የአገር እና ህዝብ መከራ አለ ፡፡

ዕዉነተኛ  የኢትዮጵያ ትንሳኤ  ዕዉን ሚሆነዉ  በመገለባበጥ ለዉጥ ሳይሆን   በዕዉነተኛ  የዜጎች የነፃነት እና አንድነት ላይ የሚቃኝ ዕዉነተኛ  የለዉጥ እና ዕድገት ሀዲድ ብቻ ነዉ ፡፡

 

አንድነት ኃይል ነዉ !

Allen .T. Selassie!

 

“In order to have real change that is progress, reform has to begin from the top and ends to the bottom.”

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop