May 24, 2023
17 mins read

“ ድምፅና ቁንጫ ባዶ ቤት ይወዳል ። …” አዳም ሀይለአብ

Sinodos 1 1

ፕሮፊሰር መሥፍን እንዳሉት ” በዶ ቤት በቁንጫ ይወረራል ። ” እናም ሀገሬ ዛሬ በየትኛውም ተቋም ፤ በመንፈሳዊ ተቋማት  ጭምር ፤ ምሁራኑ በሰበብ አስባብ ተጠርገው እየወጡ ፣ አሰስ ገሰሱ የአገልግሎት መድረኩን ይዞ  መሪነትን የልጅ መጫውቻ ሲያደርገው እያሥተዋልን ነው ።

እስቲ ዓለማዊ ተቋማቱን ተመልከቱ ። በህግ አውጪው ፣ በህግ ተርጓሚው እና በህግ አሥፈፃሚው የመንግሥት ሥልጣን ተቋም ውሥጥ ያሉ ሰዎችን በአንክሮ አሥተውሉ ፣ 98%  ለሆዳቸው የተገዙ ፣ ከራሥ በላይ ነፋስ በማለት ” ጎመን በጤና ! ” በማለት የሚሞዝቁ አይደሉምን  ?

ህዝብ በየዕለቱ በሚያሻቅብ የዋጋ ንረት የተነሳ መኖር  እያቃተው ነው ። በጣም ጥቂቱ በቀን ሦሥቴ የሚበለው ወደ ሁለቴ መብላት ተንከባሏል ። ጥቂቱ  ሁለቴ ይበላ የነበረው ደሞ  አንዴ  መብላት ግዴታ ሆኖበታል ።  የዕለት ጉርሱን ለማግኘት ተቀጥሮ የሚሰራ እና በቀን ሥራ የተሰማራው የሚያገኘው ለቤት ኪራይም አልበቃውም ። “… ባገኝም በልቼ ባጣም ተደፍቼ …” በማለት በገሃድ በለቅሶ ሲያዜም ውሎ ሲያዜም ማደሩን ቀየቀበሌው ያለ ካድሬና አጫፋሪ ወይም አሥገፋፊ ያውቃል ። ከአጠቃላይ ህዝቡ  እጅግ በጣም ጥቂቱ ብቻ ነው  ፤ በአፓርታይድ ፓለቲካዊ  ሆያ ሆዬ እየዘረፈ ፣ ያለአግባብ ተጠቃሚ ሆኖ ያለፋበትን እየበላ በቁንጣን እየተቸገረ መኖሩን ዘወትር የምንመለከተው ።

አገሬ ፈፅሞ ኃላፊነት በማይሰማቸው በነዚህ እፍኝ  በማይሞሉ የፓለቲካ ፣ የኢኮኖሚ የማህበራዊ ኑሮ ፅንሥ ሃሳብ ያልሰረፀባቸው ፤  ሆዳቸው ጭንቅላታቸው በሆነ ሰዎች እየተመራች ወደ መፍረስ እየተቃረበች ነው ። ታላቋ አገር ታሪክ ለመሆን እየተደረደረች ነው ።

ይኽንን ድርዳሮት ዛሬ የተነቃቃው አዲሱ ትንታግ ትውልድ ( በመከላከያ ውስጥ ያለውን ይጨምራል ) እንደሚቀለብሰው ባምንም ያለመሰዋትነት ሠላምሟዴሞክራሲ፣ፍትህ፣ነፃነት እና እኩልነት እንደማይመጣ ግን እገነዘባለሁ ።

በምጣኔ ሀብት አገር እየደቀቀች ፤ ዜጎች “ አገራቸው አገራችሁ አይደለችም “ እየተባሉ ከቀያቸው ሲባረሩ ፤ ሰውነታቸው ተዘንግቷ በቋንቋቸው ሲገደሉ ፤ የአፓርታይድ ሥርዓታችን ማን እንደሚኖርበት ና እንደሚዝናናበት የማይታወቅ የቅንጦት መዝናኛ ይገነባል ። ቤተ መንግሥትም  በትሪሊዮን ብር ልሥራ ነው ብሎ በማንአለብኝነት ይነሳል ።

ዜግነት በዲንጋይ ራሥ ፓለቲከኞች ተክዶ በነፃ አውጪ ሥም አጋንንቶች በማህል አገር ተሠማርተው በጠራራ ፀሐይ ሰው የሚረሽኑበት ፣ የሚያርዱበት ምቹ ሁኔታ ከእውቀት በፀዳው  መንግሥት ተመቻችቶላቸው ሣለ እና ህዝብ ጎመን አሮበት በረሃብ እየተሰቃየ ሣለ ፣ አምባገነኖቹ ፣ ህዳሙን የፓርላማ አባልና ሚኒስትር በሥጋ ምቾት ጠፍረው  በቅንጦት ቤተ መንግሥት ግንባታ ላይ ለመሠማራት ዳር ሯ ዳር እያሉ ነው ። ይኽ ድርጊት የሚያሳየን  አእምሮ ቢሥነት ብቻ አዬደለም ፣ ማን አለብኝነትን እና  የህዝብ ንቀትን ነው ። ህውብ ተንቋልም ተዋርዷልም ።

እግዜር ያሳያችሁ ፣ ወታደራዊ ተቋማቱ አንዳችም ሎጀስቲክ ሣይኖራቸው ፣ የተከበረው ወታደር ህይወቱን ለህዝብ ለመሳዋት በሲኖ ትራክና በአይሱዙ እንደ እቃ እየተጫነ እያየን ፣ ህዝብን ካልናቁ እንዴት በቀን አንድ ጊዜ ህዝብን  ማብላት  ያቃተው መንግሥት ፣   በዘጠኝ ቢሊዮን ብር ቤተ መንግሥት ለመሥራት ተነስቻለሁ ብሎ ይለፍፋል ። ይኼ ያለማፈር ነው ። የሚኒሥቴሮች ምክር ቤት እንደሌለ እንቁጠረውና    ? ፓርላማው ( የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ) እንዴት ዝም ብሎ በህግ ያልተደገፈ ተግባሩን ይመለከታል  ? ( ጠቅላዩ እናንተን አይመለከትም ለምኜ ነው ፣ ያገኘሁት እያሉ ሲናገሩ ፣ የመለመን ፈቃድ ማነው የሰጣቸው ? ህገ መንግሥቱ ላይ የፀደቀ የልመና ህግ አለን እንዴ ? ጠቅላዩ ራሳቸውን ንጉሥ ካላደረጉ በሥተቀር ፓርላማው ሳይፈቅድላቸው  ህግ ፣ መመሪያና ደንብ ሳያግዛቸው በአምባገነንነት በኢትዮጵያዊያን ምድር እንደአሻቸው ከህግ ውጪ የመጋለብ መብት የላቸውም ። )

በገልባጭ “ ሲኖ ትራክ “ እና በጭነት  አይሱዙ  የሚጓጓዙ ፣ በቂ አልባሳትና ሥንቅ የሌላቸው የመከላከያና የፖሊስ  አባላት እያሉን ፣ “ በ9 ቢሊዮን ዶላር የፊደራል መንግሥት ቤተ መንግሥት እሠራለሁ ። “ ማለት እብደት አይገልፀውም  ። ከዚህ አንፃር “ ቀዳማዊ ኃይለሥላሤ ከዛሬው የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ወይም “ ራሱን ንጉሥ ካደረገው “  ከአብይ አህመድ የባሰ ግፍ በወታደሩ ላይ አልፈፀሙም ማለት ይቻላል ። “ ብለን ብንናገር ሐሰት የሚል አንድም ሰው በዓለም አይገኝም  ። ንጉሥ ቀዳማዊ ግርማዊ ጃንሆይ  “ በሥንቅ ፣ በትጥቅ ፣ በሎጀሥቲክ ወታደሩን አልበደሉም ። ወታደሩን እንደ ዕቃ በሲኖ ትራክ እና በአይሱዙ አልጫኑም ። በደረቅ ኮሾሮ ለቀናት አላስራቡም ።   የተጋነነ ኢ ሰብዓዊነት በአገዛዛቸው የታየው በሥልጣናቸው ለመጡባቸው ብቻ ነበር ። “  አቶ ሽመልሥም ቢሆን የኦሮሞ ህዝብ በችጋር ውሥጥ እያለ ፣ በመጠጥ ውሃ ችግር ጉሮሮው እየተቃጠለ እና ከእንሥሣ ጋር እየጠጣ ፣ የ3 ቢሊዮን ቤተ መንግሥት ለመገንባት መነሳታቸው ፣  ማንን  ለማሥደሠት አስበው ነው ? በውስጡ የመኖር ህልም ያላቸው ከቶ እነማን ናቸው ?

አቶ ሽመልሰሰ  ለመሆኑ “ ሚዶ ለመላጣ ምን ይሰራለታል ? “ ብለው ነው ?

ሃቁ ሁለቱም ህዝብ አገልግሉን ያላቸው መሪዎች  ፣ ከህዝብ አሁናዊ ፍላጎትና ዘላቂ  ጥቅም አንፃር ሣይሆን ከውጪ ሀብታሞች የወደ ፊት ህልም አንፃር ነው ቤተመንግሥት ለመገንባት ያቀዱት ። ቤተመንግሥታቸው በዛሬው የአፓርታይድ ሥርዓት እውን ከሆነ ግን  ” የአውሬ መፈንጫ ” ይሆናል እንጂ ወደፊት ሰው ሊኖርበት አይችልም ።

በበኩሌ ወታደሩ ሮቦት ካልሆነ በሥተቀር የአብይንም ሆነ የሽመልስን የእብድ ፕሮጀክት እውን እንዲሆን አይፈቅድም ። በሠላም ጊዜ ፣ የተሟላ መቀመጫ የሌለው ።… በቂ ማደሪያ ቤት ንፁህ አንሶላና ፍራሽ ይቅርና ፣ ምግብ ፣ መጠለያ ና ልብስ በወቅቱ የማያገኘው መከላከያ በተቀደደ ዩኒፎርም አገርን እያገለገለና ፤ እየተራበና እየተጠማ ፣ በሲኖትራክ እየተጫነ ፣ ይህንን የዕብድ ሥራ በዝምታ በማለፍ ቢሊዮን ዶላሮችን እነአብይ ሲያቃጥሉ ዝም ብሎ ያያቸዋል ብዬም አላሥብም  ። መቼም አገር በቁንጫና በትሆን መወረሯን የሚያጣው አይመሥለኝም ።

ሌላው የዚች አገርን በቁንጫ እና በትሆነ  መወረር የሚያሣዩን የእምነት ተቋማት ናቸው ። በተለይም ዛሬ የኦርቶዶክስ ኃይማኖት በአንዳንድ  ፃድቅ ፣ ብፁዕ በተሰኙ በተግባር ግን የዳቢሎስ ልጅ በሆኑ ፣ በዓለማዊ ሥልጣን ጥም በናወዙ ፣ እግዚብሔርን በካዱ ዘረኞች ክብሯ እየተደፈረ ብቻ ሣይሆን ዓለማዊ እንድትሆን እየተገደደች ነው ።

እነዚህ ጳጳስ ነን ፣ ሥልጣነ ፈጣሪ አለን የሚሉ ሆኖም ግን በሥልጣነ ዳቢሎስ የሚመሩ ዘረኞች የሰውን በዘፍጥረት አንድነት በመካድ በጎሳው ከፋፍለው ገንዘብ መሰብሰቢያ ሊያደርጉት ቆርጠው ተነሥተዋል ። በትግራይም ፣ ኦሮሚያ በተባለው ክልልም ።

የትግራዮቹ እሥከ አሜሪካ ድረሥ ጳጳስ እንሾማለን ብለዋል ። የኦሮሚያዎቹ ደግሞ እሥከ ደቡብ የኦርቶዶክስ አገረሥብከት ጳጳሳትን  ለመሾም አሥበዋል ።

እኔም እላለሁ ፣”  እውነተኞቹ ለእግዚአብሔር የተገዙ የኦርቶዶክስ ኃይማኖት ልጆች ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቅዱስ ፓትርያርክ እውቅና ባልተሰጣቸው ጳጳሶች በሚመሩ ቤተክርስቲያናት ውስጥ  እግራቸው ለመግባት እንደሚጠየፍ ይወቁት ። “ ይኼ  ከወዲሁ ሊነገራቸው  ይገባል ። ምእመናኑ የሤጣን መሥቀል የሚሳለምበት አንዳችም ግዴታ የለበትም ።

በዛሬው ዓለም ሴጣን ዘመናዊ ሆኖ መምጣቱንም በዚህ አጋጣሚ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ልጆች ሁሉ ተገንዘቡ ። በዚህቺ ምድር  የምትኖሩት አንዴ እንጂ ሁለቴ አይደለም ። ለፈጣሪ ታምነን ለመሞት እና የድል አክሊል ለመጎናፀፍ እንነሣ !!

አብይም ሆነ ሽመልስ ሰዎች ናቸው ። ትላንት ህፃን ነበሩ ። እድገታቸውም እንደብዙዎቻችን ደሃ ኢትዮጵያዊያን መሆኑ ይታወቃል   ። ከሰማይ የወረዱ መልዕክት አይደሉም ።    የመንግሥት ሥልጣን ላይ በአጋጣሚ … ሥለወጣ ማንም መለኮታዊ ኃይልን አይጎናፀፍም ። ዘላለማዊ ህይወትም የለውም ። ፈረሽ ገላ ተሸክሞ የሚዞር ነው ። ሞት አይቀርለትም ።

“ከቶ  አይቀርም ሞቱ ፣ ምንም ቢታክቱ ፣ ምን ቢሰነብቱ ! … “ ከመሞታቸው አስቀድሞ ግን አሁን እንደሚያደርጉት ፣ ጥቂት  ለሆዳቸው ያደሩ ፤ እንደ ቀኃሥ የአገዛዝ ዘመን አይነት “ ባሮች “ ከጎናቸው አሠልፈው አብይና ሽመልሥ ሊመፃደቁ ይችላሉ ። ነገ እነዚሁ  ባሮች መጠቀሚያነታቸውን ያወቁ ጊዜ ግን አፈሙዙን ወደ እነሱ እንደሚያዞሩ አልጠራጠርም ። በትግራይም እንዲሁ ነው የሚሆነው ። የአፍሪካ “ ማን ከማን ያንሣል ? “ ጫዎታ በኢትዮጵያም ይጀመራል ። ዛሬ ጨዋውን የትግራይ ሰው ፕሬዝዳንት ሆኖ  እየመራ ያለው ማን ነው ? በእምነትስ እንደትግራዋይ ያለ ኩሩ ነበር እንዴ ? ዛሬ ፈጣሪን ክዶ ካድሬ የሆነ ጳጳስና ቄስ ምን ይባላል ? ይኽ ለትግራይ ህዝብ ሞት ነው ። ከእምነት ታሪክ አንፃር ፣ ፈጣሪውን ዘግይቶ  ካወቀው ይልቅ ፣ የቁጣ እሣት  የሚዘንበው በትግራይ ህዝብ ላይ መሆኑን መገንዘብ መልካም ነው ።

በበኩሌ እጅግ የማዝነው “ ጊዜ የሰጠው ቅል ዲንጋይን ሲስብር “ በማየቴ ብቻ ሣይሆን ኃቀኛ የሆነ ፣ ምሁር ፣ ጥበበኛ ና አዋቂ ከኢትዮጵያ ተቋማት ቁልፍ ቦታ ሁሉ ድርሽ እንዳይል ተደርጎ ፣ ቤቱን ማሥተዳደር የማይችል ግብዝ ሁሉ ከቀበሌ ጀምሮ በመንግሥት ሥልጣን ላይ ተቀምጦ ፣ ዘወትር ለከርሱ ብቻ በማሠብ ደሃን ሲበድል ፣ሲዘርፍ ፣ ሲያሥለቅስ ና ሲገድል በማየቴ ነው ። ኢትዮጵያ በዚህ አምሥት ዓመት ብቻ 40 ዓመት ወደ ኋላ ሄዳለች ። ከሞራል አንፃር ደግሞ ከደርግም ከወያኔም የባሱ ጥቂት እፍረተ ቢሥ አመራሮችን አፍርታ ወደፊት አምጥታለች ።  ይኽንን ግን በሚሊዮን የሚቆጠረው ጨዋና ኩሩው ወጣት ኢትዮጵያዊ ! በቃ ! ሊለው ይገባል ።

እውነት ነው ፣ ” በዶ ቤት የቁንጫ መራቢያ ነው ። ” ደሞም በበገና ዝማሬ   ድምፅና ቁንጫ ባዶቤት ይወዳል ፤ ያትልቅ ወንበርም በትሆን ተሞልቷል ። ” ተብሎ ሲዜም ሰምተናል  ። እናም ቤታችንን ከቁንጫና ከትሆን ለማፅዳት ሳይረፍድብን መነሳት አለብን !!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop