May 24, 2023
13 mins read

የጭራቅ አሕመድ መፃኢ ዕጣ፤ በለማ መገርሳ መረሸን

ጭራቅ አሕመድ ያማራን ሕዝብ በልቶ ለመጨረስ ቆርጦ የተነሳ ኦነጋዊ አውሬ ቢሆንም፣ አውሬውን እንደ እንዝርት የሚያሾረውና ባማራ ሕዝብ ላይ የሚያሰማራው ግን ‹‹ቀድሞ የይፋ አሁን የሕቡዕ አለቃየ›› እያለ አለቅጥ የሚሽቆጠቆጥለት፣ በመሠሪነቱ ወደር የሌለው ሸለመጥማጡ ለማ መገርሳ ነው፡፡  አሁን ላይ ግን ጭራቅ አሕመድ ለለማ መገርሳ ከሚሰጠው ጥቅም ይልቅ ጉዳቱ እያመዘነ ስለመጣ፣ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ረሽኖ ያስወግደዋል፡፡  ለምን እና እንዴት የሚለውን ደግሞ ባጭሩ እንመልከት፡፡

በፖለቲካ ብስለታቸው አንቱ የሚባሉትን ጨምሮ አያሌ ሰወች ጭራቅ አሕመድ ለማ መገርሳን ከስልጣን አስወግዶ፣ ከሀገር አስወጥቶ ከጨዋታ ውጭ አርጎታል እያሉ እጅጉን ሲሳሳቱ ይደመጣሉ፡፡  ይህን ትልቅ ስህተት የሚፈጽሙት ደግሞ የለማ መገርሳን የመሠሪነት ጥልቅት ባለመረዳትና፣ ዐላማውን በምን መንገድ እንደሚያስፈጽምና ማስፈጸም እንደሚፈልግ ባለማወቅ ነው፡፡ ጭራቅ አሕመድ ጃዋርን አሰረው የተባለው፣ እስክንድርን ለማሰር ጭራቅ አሕመድና ጃዋር ሙሐመድ የተጫወቱት ቀልድ እንደነበረ ሁሉ፣ ጭራቅ አሕመድ ለማ መገርሳን አባርረው የሚባለው ደግሞ አማራን ለማታለል ጭራቅ አሕመድና ለማ መገርሳ የተጫወቱት ቀልድ ነበር፡፡

ጭራቅ አሕመድን ጨምሮ ሁሉንም ኦነጋውያን በየመደበላቸው የሥራ ድርሻቸው የሚያሰማራቸውና የሚከታተላቸው የኦሮሙማ ፕሮጀክት ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆነው ኦቦ ለማ መገርሳ ነው፡፡  የኦሮሙማ ፕሮጅከት ሊሳካ የሚችለው ደግሞ በኦነግ ጥንካሬ ሳይሆን ባማራ ድክመት እንደሆነ ከለማ መገርሳ በላይ የሚያቅ የለም፡፡  ያማራ ድክመት ደግሞ ካማራነቱ በላይ ኢትዮጵያን ማፍቀሩ ነው፡፡   ስለዚህም፣ ለማ መገርሳ የኦሮሙማ ፕሮጀክቱን ማስፈጸም የሚችለው ኢትዮጵያን የሚያፈቅር መስሎ በመቅረብ ነው፡፡  የወያኔ የደህንነት ኃላፊ ሆኖ ኢትዮጵያን ሲያጠፋ እንዳልነበር፣ ወያኔ ሊወድቅ ሲንገዳገድ በድንገት ተነስቶ ኢትዮጵያ ሱሴ ያለውም ኢትዮጵያ ሱሱ ሁናበት ሳይሆን በኢትዮጵያ ፍቅር የወደቀውን አማራን ለማነሁለል ሲል ብቻ ነበር፡፡

ያዲሳባ የዲሞግራፊ ቅይራ ንግግሩ ይፋ ከወጣበት በኋላ ግን ለማ መገርሳ አማራን ማታለል ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደረሰ፡፡  የነ ዲባቶ (ዶክተር) አምባቸው የባሕርዳር ጭፍጨፋ ሲካሄድ፣ ጭፍጨፋውን ያካሄደውን መከላከያን ይመራ የነበረው እሱ መሆኑ ደግሞ የለማ መገርሳን ማንነት ይበልጥ ይፋ አደረገው፡፡  ስለዚህም አማራን እያዳከመለት የኦሮሙማን ፕሮጀክት ለመፈጸም እስካስቻለው ድረስ፣ ጭራቅ አሕመድን ከፊት አድርጎ ከኋላ ሁኖ ከመምራት ውጭ ምርጫ አጣ፡፡

አሁን ላይ ግን ጭራቅ አሕመድ አማራን የሚያታልልባቸውን ትሪኮቹን (tricks) ተጠቅሞ ጨርሷል፡፡  ካሁን በኋላ ጭራቅ አሕመድ በኃይል ካልሆነ በስተቀር አማራን በማታለል ሊፈጽም የሚችለው አንዳችም ነገር የለም፡፡  ባማራ ሕዝብ ላይ ይፋ ጦርነት የከፈተውም በዚሁ ምክኒያት ነው፡፡  ጭራቅ አሕመድ አማራን ማታለል ካልቻለ ደግሞ ለለማ መገርሳ የኦሮሙማ ፕሮጀክት ምንም ጥቅም የለውም፡፡  እንዲያውም ጉዳቱ ያመዝናል፡፡  ስለዚህም ባስቸኳይ ያስወግደዋል፡፡

ጭራቅ አሕመድ ስለነጻነት ምንነት ምንም ባማያውቅበት ዕድሜው፣ ኦሮሞን ካማራ ነጻ ለማውጣት ጫካ የገባ የኦነግ የሕፃን ወታደር (child soldier) ነበር፡፡  የኦነግ የሕፃን ወታደር የነበረ በመሆኑ ደግሞ በኦነግ አለቅጥ የተነወረ (ነውር የተፈጸመበት abused) የነውር በሽተኛ (abused child) ነው፡፡  የኦነግ የሕፃን ወታደር የነበረ ከመሆኑ በላይ አናቱ አማራ ናቸው መባሉ፣ ያባቱ ማንነት ደግሞ በውል አለመታውቁ በኦነግ የተፈጸመበትን ነውር ይበልጥ የከፋ አድርጎታል፡፡  የተማረ ነው ይባል የነበርው ሃይሌ ፊዳ፣ አባቱ የመናዊ በመሆናቸው ምክኒያት በማንነቱ ያን ያህል ተሰቃይቶ ኦሮሞነቱ ጥርጣሬ ውስጥ እንዳይገባ ሲል ብቻ ከኦሮሞ በላይ ኦሮሞ ልሁን ካለ፣ አናቱ አማራ ናቸው የሚባሉት ምንም ትምህርት የሌለው ጭራቅ አሕመድ ደግሞ አሮሞነቱ እንዳይጠርጠር ሲል ብቻ አማራን ከምድረግጽ ሊያጠፋ ቢነሳ ምንም አያስገርምም፡፡

እንደ ጭራቅ አሕመድ ያለ፣ ከሕፃንነቱ ጀምሮ አለቅጥ የተነወረ የነውር በሽተኛ/ነዋሪወቹን/ (ነውር የፈጸሙበትን) ለማስደሰት ሲል ምንም ከማድርግ አይመለስም፡፡  መዱስ (መጽሐፍ ቅዱስ) እንደሚያስተምረን አብርሃም ለጌታው /ያለውን/ ታማኝነት ለማስመስከር ልጁን ይስሐቅን ለእርድ እንዳቀረበ፣ ጭራቅ አሕመድ ደግሞ ‹‹ቀድሞ የይፋ አሁን የሕቡዕ አለቃየ››  ለሚለው ለጌታው ለለማ መገርሳ ያለውን ታማኝነት ለማስመስከር አማራን ማረድ ሳይሆን ልጆችህን እረድ ቢለው በደስታ ያርዳል፡፡

ያንድ ብሔር አባል አለመሆኑ የሚጠረጠር ግለሰብ ወዶም ሆነ በነውር ተገዶ የዚያ ብሔር ብሔርተኛ ከሆነ፣  ጥርጣሬውን ለማስወገድ ሲል ብቻ ማናቸውንም አረመኔያዊ ድርጊት ለመፈጸም ቅንጣት አያቅማማም፡፡  ሂትለር ይሁዳወችን ያለ ርኅራኄ የጨፈጨፈበት አንዱ ምክኒያት፣ የይሁዳ ደም አለበት የሚባለውን ጭምጭምታ ለማስተባበል ነበር፡፡  ምሥራቅ አውሮጳውያን (ቸኮች፣ ፖሊሾች፣ ዩክሬኖች፣ ክሮአቶች…) ካንግሎ ሳክሶኖች በከፋ ሁኔታ ዘረኛ መስለው ለመታየት የሚጥሩት፣  ከነጭ አይቆጥሩንም ለሚሏቸው ለምዕራብ አውሮጳውያን ነጮች መሆናቸውን ለማስመስክር ሲሉ ነው፡፡  ያሜሪቃ ጥቁር ፖሊስ ከነጭ ፖሊስ የበለጠ በጥቁር ላይ የሚጨክነው፣ ታማኝነቱን ለነጭ አለቆቹ ለማሳየት ነው፡፡  ባባቱ አማራ ነው የሚባለው ጌታቸው አሰፋ ያማራ ሳጥናኤል የሆነው፣ ትግሬነቱን ለማስመስከር ነበር፡፡

ጭራቅ አሕመድ ደግሞ በናቱ አማራ ነው ከመባሉ በላይ የተጋባው ጎንደሬ ናት ከምትባል ሴት ጋር ነው፡፡  ስለዚህም በጎጠኝነት የሰከሩት የኦሮሞ ጽንፈኞች ጭራቅ አሕመድን ከአሮሞ አይቆጥሩትም፡፡  እንደማይቆጥሩት ደግሞ እሱ ራሱ በደንብ ማወቅ ብቻ ሳይሆን አልቅጥ ያስጭንቀዋል፡፡  ኦሮሞነቴን ማንም አይሰጠኝም፣ ማንም አይነፍገኝም፣ እናቴ አማርኛ አትችልም እያለ ሳይጠይቁት የባጥ የቆጡን የሚቅባጥረው ይሄን ጭንቅቱን ለማለዘብ ነው፡፡

ጭራቅ አሕመድ በኦሮሞነቱ ስለማይታመን ባይነ ቁራኛ እንደሚጠበቅና እያንዳንዷ ድርጊቱ ባጉሊ መነጽር እንደምትመረመር አሳምሮ ያውቃል፡፡  ትንሽ ቢሳሳ ግዙፍ ውለታው መና ቀርቶ ከሃዲ እንደሚባ ነጋሪ አያስፈልገውም፡፡  እስከጣፈ ድረስ ተላም የሚተፉ አገዳ መሆኑን በደንብ ያውቃል፡፡  ስለዚህም ጥፍጥናውን ላለማጣት ሲል ብቻ ማናቸውንም ፀራማራ ድርጊት ለመፈጸም ቅንጣት አያቅማማም፡፡  የሱ ጽኑ ፍላጎት ደሞ ኦነጋውያን ትናንት ከሚያምኑት የበለጠ ዛሬ እንዲያምኑት ስለሆነ፣ ትናንት ከጣፈጠው የበለጥ ዛሬ መጣፈጥ ነው፡፡  ስለዚህም ጥፍጥናውን ለመጨመር ሲል፣ ትናንት ቶሌ ላይ ያማራን ሕጻናት ግዳይ እንደ ጣለ፣ ነገ ጉለሌ ላይ፣ ከነገ ወዲያ ደግሞ ቦሌ ላይ ግዳይ ለመጣል ሙሉ ዝግጁ ነው፡፡

በለማ መገርሳ እይታ ግን፣ የጭራቅ አሕመድ ጥፍጥና አማራን ማታልለና ማዘናጋት መቻሉ ሲሆን፣ ይህን ጥፍጥናውን ደግሞ ሙሉ በሙሉ በማጣት ታኝኮ የተጨረሰ አገዳ ሁኗል፡፡  ስለዚህም ለማ መገርሳ በቅርቡ ይተፋዋል፡፡  ጭራቅ አሕመድን ተፈቶ ሲጠለው ደግሞ፣ ቱሲወች (Tutsi) የሁቱወችን (Hutu) መሪ ሃብያሪማናን (Habyarimana) እንደገደሉት አማሮች የኦሮሞወችን መሪ ዐብይ አሕመድን ገደሉት በማለት እልፍ አእላፍ አማሮችን ባንድ ጀምበር በመጨፍጨፍ የኦሮሙማ ፕሮጀክቱን ከግብ ለማድረስ ይጠቅምበታል፡፡  ጭራቅ አሕመድ በለማ መገርሳ ቀጭን ትዕዛዝ ግርማ የሺጥላ ላይ የፈጸመውን፣ ለማ መገርሳ ደግሞ በራሱ በጭራቅ አሕመድ ላይ ይፈጽምበታል፡፡  የጭራቅ አሕመድ መፃኢ ዕጣ ይሄውና ይሄው ብቻ ነው፡፡

ስለዚህም ያማራ ሕዝብ ሆይ፣ ጭራቅ አሕመድ ግርማ የሺጠላን አስወግዶ ይፋ ጦርነት እንደጀመረብህ፣ ለማ መገርሳም ጭራቅ አሕመድን አስወገዶ ይፋ ጭፍጨፋ ሊጀምርብህ መሆኑን አውቅህ፣ ራስህን ከጭፍጨፋ ለማዳን ማድረግ ያለብህን ሁሉ ከወዲሁ አድርግ፡፡

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

4 Comments

  1. መስፍን፤
    አብይ አህመድ በለማ መገርሳ ነው የሚዘወረው የሚለው ትንተናህ ውሃ አይቋጥርም። ከአራት አመት በፊት የተጻፈ እስኪመስል ድለስ አናሳ አመለካከት ሆኖ አግኝቸዋለሁ። ለማ መገርሳ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ያለ ሰው አይደለም/ ብዙ ተወርቶበት ነበር። ታንዛንያ ኦነግን ወክሎ ተደራዳሪም ተደርጎ ተራግቧል። እውነትና ንጋት እያደር ዪጠራል እንዲሉ አልነበረም። የኢትዮጵያ ችግር መሰረቱ አብይ አህመድ ነው። እውነቱን ለመናገር ጀዋርም፤ ሽመልስም፤ አዳነችም ወይም ሌላ ኦሮሞ አይደለም። ሁሉም የአብይ ጉዳይ አስፈጻሚዎች ናቸው። የችግሩ ሁሉ ጠንሳሽ አብይ አህመድ ነው። ማፍናቀል፣ መግደል፣ ቤት ማፍረስ እና ሁሉም አይነት እኩይ ሃሳብ የሚፈልቀው ከአብይ አህመድ ነው። ይህን የሚያደርገው እናቱ አማራ ስለሆነች ኦሮሞ አይደለህም እንዳይባል ነው ያልከውም ውሃ አይቋጥርም። አቢይ በናቱ የቡራዩ ኦሮሞ በአባቱ የጂማ ኦሮሞ ነው። አራት ነጥብ። እነ አበበ ገላው ናቸው የአማራ ወዳጅ ለማብዛት ብለው በናቱ አማራ ነው ብለው ያስወሩጥ ያ ሃሰት ነው። ሰውየው የአማራ ጥ፣ላቻ ያለውበት የ16ኛው ክፍለዘመን ሙሉ ኦሮሞ ነው።

  2. ይሄ ጠቅላይ መሪ የሱ ሰው ማን ይሆን? ጁዋርም አንገቱን ልትለው ቀን እየጠበቀች ነው መራራ ጉዲናም ኪንግ ሜከር ለመሆን አድፍጦ ይከታተላል ሽመልስም የሱ ሰው መስሎ ዞር ሲል ምላሱን ያወጣበታል ኦሮም ምን ቢያሽቃብጥ አይንህን አልየው ብሎታል ትግሬም አሳቻ ጊዜ እየፈለገ ነው ያማራው ማብራሪያም አያስፈልገውም እንግዲህ ይሄ ሰውዬ በነብይ እስራኤል ዳንሳ፤በእዩ ጩፋ እና መራሄ ነብያት ዮናታን አክሊሉ ጸሎት ካልሆነ ማን አለው ከጎኑ? ብርሃኑ ነጋ አደጋ ሲመጣ ሶስቴ ሳይሆን 12 ጊዜ ይክደዋል እንደፍጥርጥሩ ምን አገባኝ ለካ እነ ዳውድ ኢብሳና የባህል ናጅ ሚኒስትሩ ቀጀላ መርዳሳም አለ መጥኔ አገሪቱ ምን በደለች?

  3. ጽሁፉና መስፍን ያጣቀሰው ምሳሌ ልክ ነው። መኩሪያ ነህ ማነህ ስለ እናቱ አብይ ከዚህ በፊት ተናግሯል ቆይተህ ሚስቱንም የጎንደር ኦሮሞ ነች እንዳትለን። የሆነ ሆኖ ስታሊን ዲያቆን ነበር ኮሚኒስት ከሆነ በኋላ በተራማጆች እንዳይጠረጠር በቤተ ክርስቲያን ላይ ዛሬ በሃገራችን የሚደረገውን አይነት ሰቆቃና ግፍ ፈጽሟላ ሰዎች የግሩፑ አካል ካልሆኑ ትክክለኛ አካል ካልሆኑ መስሎ ለመታየት ብዙ እርቀት ይጓዛሉ። እስቲ ማብረጃውን ያምጣ። ምን ብዬ እንደምጠራቸው ግራ ገባኝ የዶክተር ነገር ሳያበቃላት አልቀረም አንዴ ስለለመደብን አንድ የኦሮምያ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬት ቢሰጠው መልካም ነበር።

  4. ታዲያ አንተ እንዳሰብከው ቢሆን ለማስተላለፍ የተፈለገው ነጥብ ምንድን ኘው።አብይ ቢቀጥል ይሻላል ማለትህ ይሆን። ወይስ እንዲህ አይነት ፅሁፍ አንዱ የትግል ስልት ይሆን? ከስሜታዊነት
    በ መቆጠብ የሰከነ ሃሳብ ማካፈል ሲቻል …

Leave a Reply

Your email address will not be published.

182877
Previous Story

“ሽንት አስጨራሽ ቀልድ እና አሽሙሮች…” | ፍራሽ አዳሽ | ተስፋሁን ከበደ | arts tv

welkeit 1 1
Next Story

የወልቃይት እና ራያ ጉዳይ የእነሱ መቆመሪያ ሆኖ አይቀጥልም | Hiber Radio Special

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop