እናቷን አባቷን ባለቤቷን ሶስት ልጆቿን እህቷን ከአራሷ ልጇ ጋር ወንድሟን ከአራት ልጆቹ ጋር በአጠቃላይ ሃያ አንድ ቤተሰቦቿን በግፈኛው አብይ አህመድ በግፍ የተገደሉባት

እህታችን ጠይባ ሁሴን መሐመድ
እህታችን ጠይባ ሁሴን መሐመድ

እናቷን አባቷን ባለቤቷን ሶስት ልጆቿን እህቷን ከአራስ ልጇ ጋር ወንድሟን ከአራት ልጆቹ ጋር በአጠቃላይ ሃያ አንድ ቤተሰቦቿን በግፈኞች የተገደሉባት ምስኪን እህታችን ናት ። ጠይባ ሁሴን መሐመድ ትባላለች ።

ጠይባ ሁሴን መሐመድ በዱባይ ለሰባት ዓመታት ፣ በሳዑዲ አረቢያ ደግሞ ለስምንት ዓመታት ሰርታለች ። በሰው አገር የተንከራተችላቸው ቤተሰቦቿ ወለጋ ጊቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ ውስጥ ምንም ባላወቁት ሁኔታ ተገድለውባታል ።
በ1977 ዓ/ም ከኮምቦልቻ እና ከከሚሴ እናት እና አባቷ ወደ ወለጋ እንደሄዱም ሰምቻለሁ ። ጠይባ የተወለደችው ወለጋ ነው ።
ምን ብለን የትኛውስ ኃይለ ቃል ነው የሚያጽናናት !?

EthioVoice.net

 
ተጨማሪ ያንብቡ:  ሰበር የደስታ ዜና 7ግዜ ጠርምሶnየወጣ ጀግና - እንኳንም አተረፈህ

2 Comments

  1. ኦሮሙማው አህመዲን ጀበል አለህ? በሌለ ነገር ቁራን ሽንት ቤት ተገኘ ቁራን ተቀደደ እያልክ ስታላግጥ የከረምከው ሰብአዊ ፍጡራን የአማራ እስላሞች ከአንድ ቤተሰብ 24 ሰው ሲታረድ ድምጽህን አጥፍተሃል ድሮም የፖለቲካ ሃይማኖት ስለሆነ አላመንህም ነበር ላንተ ኦሮሞ ያደረገው ወንጀል ሁሉ ቅድስና ነው ጀነት ያስገባል ለነዚህ ንጹሃን ሞት ጓደኛህ ጁዋር መሃመድ፤አንተ፤አቡምናምን የምትባሉ ባለጊዜዎች ተጠያቂ የምትሆኑበት ጊዜ መምጣቱ አይቀርም። ሴትዮዋ ታለቅሳለች እናንተ ትስቃላችሁ።

  2. የኦሮሞ የነጻነት ትግል ፍሬው ይህ ነው። የመደመሩ ሂሳብ ውጤት ሰውን በዘሩና በቋንቋው እየመረጡና እየቀነሱ ማስላት ነው። በአሃዝ የበዙት በኦሮሞ ህዝብ ስም ያሰፈሰፉት የውጭና የውስጥ ብሄርተኞች እንዲህ ስለመሰለው ግፍ ምን መልስ ይኖራቸው ይሆን? ያኔ ወያኔ ወደ መቀሌ ኦሮሞ ወደ ሚኒሊክ ቤ/መንግስት ሲገባ ሰው በፈንጠዝያ ሲዘል ለአንድ የቅርብ ጓደኛዬ እንዲህ ብዬው ነበር። “ስማ ለውጥ በምድሪቱ ይመጣል ብለህ አታስብ። አሁን የምታየው የጫጉላ ቤት ጊዜ ነው። ኦሮሞዎች ከወያኔ የከፉ ይሆናሉ” ስለው ስልኩን ጀሮዬ ላይ እንደዘጋው ትውስ ይለኛል። ስሜታዊነት ምንም ጊዜ ሚዛናዊ ሆኖ አያውቅም። የትግራይ ልጆች ክፋት የረቀቀና ሁለት መልክ ያለው ነበር። በውጭ ሃገር ክንፍ ቀጥለው መልዓክ ነን ሲሉ በሃገር ውስጥ ደግሞ ዝንቅ ባህሪ ነበራቸው። አመራራቸውም የተጠላው የትግራይ ልጆች በመሆናቸው ሳይሆን በሚፈጽሙት የማያባራ ግፍ ነበር። ዛሬ ቀኑ መሽቶ ወያኔን የሚያስመሰግን ሆነ። ግራም ነፈሰ ቀኝ ማንም ቢሆን ከደርግ መከራ በህዋላ ከደርግ የከፋ ከፋፋይና ሃገር ሺያጭ እንደ ወያኔ ያለ ይመጣል ብሎ እንዳላሰበው ሁሉ አሁን ደግሞ ጭራሽ አንድ አፍራሽ በከፋ አፍራሽ ተተክቶ ምድሪቱን ያምሳታል።
    አምናለሁ ዛሬም በጠ/ሚሩ አመራር ተስፋ ያልቆረጣችሁ ደጋፊዎች እንዳላችሁ። እሱ የእናንተ ምርጫ ነው። ግን መሬት ላይ እየታዬ ያለው ጭብጥ ነገር የሚያሳየን ሰቆቃና መከራን ብቻ ነው። ኢኮኖሚው ያለ ልክ ከማሽቆልቆሉ የተነሳ ሰው በከተማና በገጠር በረሃብ የሚናጥበት ጊዜ ላይ ቆመናል። የወያኔ መሪዎች በተለይም የአቶ ጌታቸው ረዳ ወፍሮ መታየት የትግራይን ህዝብ በልቶ ማደር አይናገርም። በአንጻሩ የጊዜው አለቆቻችን የኦሮሞ የብሄር ሰካራሞች በዚህም በዚያም አምሮባቸው መታየት ሰፊውን የኦሮሞ ህዝብ እፎይታ አያሳይም። የሰው ፍጥረት ሆነው በጭፍን ጥላቻ አማራን ከምድረገጽ ለማጥፋት ዘመቻ የከፈቱት የኦሮሞ ታጣቂዎች ሊመከቱ የሚችሉት ገዳዪችን በመግደል ብቻ ነው። ይህን ሊያደርግ የሚገባው መንግስት ተብየው ሆኖ እያለ የሰላም ድርድር በማለት የጀመረው ጉዳይ ለኦሮሞ ፓለቲከኞች ጊዜ መግዣ እንጂ ሌላ ትርጉም አይኖረውም። ከኤርትራ ወደ ሃገር ሲገቡ ከወያኔ ጋር በመቀሌ የመከሩትና ከፍተኛ ቀባበል የተደረገላቸው ኦነጎች ወለጋ ሂደው የመሸጉት መቀሌ ላይ በመከሩት ሴራ ነው። አሁን ከመሸ በህዋላ የወያኔ መሪዎችና የእነ ሽመልስ መተቃቀፍና ለትግራይ ህዝብ እርዳታ በሚል ሰበብ መተቃቀፉ የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው ከሚል የፓለቲካ ሸር እንጂ ከስብዕና የመነጨ አይደለም።
    ዛሬ የኦሮሞ ጀማሪ የስለላ መረብ ሰራተኞች ሰውን እያፈኑ፤ እየገደሉ፤ እየሰወሩ ያሉት ልክ እንዳለፈው ለመኖር ራስን ደም መቀባትና መቀባት ብልሃት በመሆኑ ነው። ሴትንና ካህንን በጥፊ መትቶ ጀግና ነኝ የሚል ደንቆሮ ታጣቂ፤ ወንድሙን አፍኖ ጫካ በመውሰድ አስሮ መግረፍና ዳግም እንዳይተነፍሱ ማድረግ ለኦሮሞ ጠባብ ብሄርተኞች እንደ ዲሞክራሲ የሚቆጠር ነው። አልፎ ተርፎም ባህር ማዶ ተሻግረው ሰውን ለማስፈራራት፤ ብሎም ስልክና ሌሎች ነገሮችን ለመጥለፍ የሚያደርጉት ሙከራ ሁሉ ገና ዳዴ የሚሉ ግራና ቀኛቸውን የማያውቁ መሆናቸውን አስረግጦ ያሳያል። የዚህች እህታችን መላ ቤተሰቧን ማጣት የኦሮሞ የዘር ፓለቲካ ያመነጨው የመከራ ዶፍ ነው። አንድ “The World Aflame” የተሰኘ መጽሃፍ በዓለም ላይ ያሉ ግጭቶች ሁሉ ይፋዊ መንሴአቸው ልዪ ልዪ ይሁን እንጂ በአንድ ቃል ሊጠቃለሉ ይችላሉ ይለናል። ያም ቃል ” የበታችነት ስሜት” ነው። ሌላው ሁሉ የነገር ማጣጫ እንጂ ፍሬ ቢስ ነው። ሰው በግፍ ገድሎ እንጀራ ከሚቆርስ ሰው ይልቅ በጫካ ውስጥ ያሉ አናብስት ይሻላሉ። ግን መቼ ነው መገዳደል የምናቆመው? መቼ ነው አንተ እዚህ አንቺ እዛ እያለን ድንጋይ መወራወራችን የሚያከትመው? መቼ ነው ከሰሜን ደቡብ ከምስራቅ ምዕራብ በግፈኞች የሚያነቡ አይኖች ማንባት የሚያቆሙት? ዋ በህዋላ ምንም አትራፊ በሌለበት ሁሉም በከሰረበት ምድር ላይ ብቻችን እንቆምና ወዬው እንዳንል እፈራለሁ።፡ በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share