May 7, 2023
21 mins read

″ሰው ፓርቲ ″ እናቋቁምና የዘር ፖለቲካን እንቀበረው – ሲና ዘ ሙሴ

sew 1 1
#image_title

በብልፅግና  ሥም  በአምባገነንነት ጥቂቶችን በማበልፀግ ፣ በመላው ኢትዮጵያ  ድህነትን  እያስፋፋ  ያለውን  ገዢውን  ፓርቲ ፣ በጠብ መንጃ ሳይሆን፣ በምርጫ ፣  ለማሶገድ ፣  ፖለቲካ ሣይንስ መሆኑን በቅጡ የሚያውቅ  አዲስ  አሥተሳሰብ  ያለው ፓርቲ ወይም ህሊና ያላቸው ሰዎች የሚመሩት የሰው ስብስብ ፓርቲ   ያሥፈልገናል  ″

 ሲና    ሙሴ

″ ሰው ፓርቲ ″ ( human party ) የተሰኘ የአገሬን ዜጋ ሁሉ ያለ ልዩነት የሚያሳትፍ ፓርቲ ለመመስረት እፈልጋለሁ ። ልብ በሉ ፍላጎቴን እየተናገርኩ ነው ። አንዳችም እንቅሥቃሤ አላደረኩም ። ላድርግም ብል አልችልም ። አቅም የለኝም ። ሆኖም ሃሳብ አለኝ ። እጅግ ጠቃሚ ሃሳብ ።

ይኽንን ጠቃሚ ሃሳቤን ዛሬ ለአገሬ ካላቀረብኩ እና ከጥፋት እንድትድን የራሴን አስተዋፆ ካላደረኩላት ልጇ ነኝ ማለት እንዴት እችላለሁ ?  ዛሬ እኮ ፣ አገሬ እየሞተች ነው ። መሪዎቿ ለውጪ አገር ሀብታሞች  መዝናኛ እና ሲወጡ ሲገቡ ለሚያዩት አርቴፊሻል ውበት እንጂ ለሰው ውበት  ደንታ ቢስ ሆነዋል ። በመሆኑም ብዙ ውብ ወጣቶች በከንቱ እየረገፉ ነው ። በጅል ፣ በጅለአንፎ ና በቂል ፊትአውራሪነት  በሚመራ የወንድማማች ጦርነት ።

በሚያናድድና በሚያስቆጭ ሁኔታ  እቺ አገር ለሥልጣናቸው ዘላለማዊነት እንጂ ፣ ለወንድማማቾች ደንታ በሌላቸው ፤     ህሊናቸው በሱስ በደነዘዘ ጥቂት ማስተዋል ባልፈጠረባቸው  ሰዎች በኃይል ተገፍታ ገደል አፋፍ ደርሳለች ። ትቂት ፣ ሆዳሙና ህሊና ቢሱ የብልፅግና ቁንጮ አመራሮች እንደቀድሞው ኢህአዴግ 60 ዓመት በነበረ ያረጀ ና ያፈጀ የጨቋኝ ተጨቋኝ ትርክት እያሳበቡ ፣  በቋንቋ ፖለቲካ ካልገዛው ሞቼ እገኛለሁ በማለት ጥቂት ዘራፊዎችን በማፍራት ላይ ተጠምደዋል ። አገሪቱን በጎሳና በመንደር እንድትከፋፈል መንገድ እየጠረጉ ነው ። በተግባር ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊያንን እየገደሉ ነው ።

ከዚህ ሰውን በረሳ እና ከቀደመው ኢህአዴግ ባህሪ ያልተሻለ ″ ስመ ብልጽግና ″  እና በሠለጠኑት መንግሥታት ዘንድ ″  እንደ ተነጂ ″  ከሚቆጠር አገዛዝ አገሬን ነፃ የሚያወጣት አንድ ሁሉን አቀፍ “ሰው ” የተሰኘ ፓርቲ መመሥረት ያሥፈልጋል ።እናም በሰው ና ለሰው የተፈጠረ   ታላቅ የፓለቲካ ተቋም በአገሬ ለመገንባት የኢትዮጵያ ሰዎች በህብረት ትነሱ ዘንድ ጥሪዬን አቀርባለሁ ።

ይኽንን ታላቅ እና ከዘመናት በፊት ለእኛ የተሰጠ ሰው የተሰኘ ታላቅ ሥምን ፓርቲ አድርጎ በመላው ኢትዮጵያ ለመንቀሳቀስ ደግሞ  የአገሬ ምሁራን እና ባለሀብቶች በንቃት ለማገዝ ቁርጠኛ ሁኑ ። አሁን ያሉትም ፓርቲዎች ወደፊት “ የኢትዮጵያ  ሰው ዴሞክራሲ ና ህብረተሰባዊ ፓርቲ “ በሚባለው ፣ ፓርቲ ሥር  እንዲደራጁ ማድረግም ሌላው የቤት ሥራ ሊሆን ይገባል ።

አሁን እና ዛሬ የቋንቋ ፓለቲካን አለቅም ብሎ ፣ ቋንቋን እንደዘር መገለጫ በማድረግ በቋንቋ ከፋፍሎ አገርን ለጥቂት ፓለቲከኞች በወርቅ ሰሐን በመሥጠት በገዛ ላብና ደማቸው ጥረው ግረው እስከጊዜው የሚኖሩትን ዜጎች የሚያባላውን ና ጥቂቶችን   እያበለጸገ ያለውን የአንድሰው አበገነንነት የሚፀባረቅበትን  መንግሥት ከኢትዮጵያዊው ሰው ጫንቃ በህጋዊ ምርጫ አሽቀንጥሮ ለመጣልም ይኽ ፓርቲ በአሥቸኳይ መቋቋም አለበት ።

ይኽ ወደፊት ሊቋቋም የሚችለው  ” ሰው ፓርቲ ወይም Human party “  ሁሉን ዜጋ አቃፊ በመሆኑ ከዝንት ዓለም ንትርክ ዜጎችን ይገላግላቸዋል ። ሰው መሆናቸውን በማሳወቅ ። ሁሉም ኢትዮጵዊ ሰው መሆኑንን አውቆ ፣   ለፓርቲው ደጋፍ ያደርግለታል ።  ይኽንን በሰዎች እና ለሰዎች የሚቋቋም ፓርቲን እውን ለማድረግም አያሌ ምሁራን እና የፖለቲካ ሊቃውንት በቅንነት  ይሳተፋሉ ብቻ ሳይሆን ከልባቸው እንደሚጥሩ  አምናለሁ ይኽ ሰው  የተሰኘ  ፓርቲ ፣ የራሱ ፕሮግራም ፣ የተለያዩ ዕቅዶቹና አገርን በተመለከተ የሚያወጣቸው ፖሊሲዎች ይኖሩታል ። እነሱም  ወደፊት በአባላቱ ተሳትፎ  የሚዘጋጁና ለህዝብ ይፋ የሚሆኑ ይሆናሉ ።

በታላላቅ የፖለቲካ ሊቃውንት እና የተለያዩ ምሁራን ታግዞ ፤   በጥልቅ ጥናት እና ምርምር ላይ ተመሥርቶ ፤ የሚዘጋጀው  ለአገር የሚበጅ ሰነድም ከአሜሪካ ህገመንግሥት እኩል የኢትዮጵያ ዜጎች የሚኮሩበት እና የሚመኩበት የፖለቲካ ሀሁ ሰነድ ይሆናል ። የዚህ ፓርቲ ርዕዮትም   በመላው ዓለም  ቅቡልነት  ካላው ርዕዮት ጋር አንድ አይነት የሆነ ፣ የጠራና አንዳችም ብዥታ የማይፈጥር ህኖ ይዘጋጃል ። በአጭር ጊዜ በዓለም ላይ እጅግ ቅቡልነት ያለው በመሆንም ለጠቅላላው አፍሪካ ሁሉ እንደምሣሌ የሚቆጠር በመሆኑ ፤  ዜጎችን በማንቃት “ሀ” ብለው ህይወትን እንዲያጣጥሙ ሥለ ኑሮ እንዲረዱ ያደርጋቸዋል ።

ይኽ ፓርቲ ኢትዮጵያዊያን ፓለቲካዊ ሥልጣንን ለመጨበጥ የግድ ዘረኛ  ወይም ቋንቋኛ መሆን እንደማያስፈልጋቸው በዕውቀት ላይ የተመሠረተ ትምህርት ይሰጣል ። የፓርቲው ዓባላት ህዝብን ወክለው   ሥልጣንን ለመጨበጥ  የሚፈልጉትም ለአጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ” ለሰው ” ሠላም፣ ፍትህ፣ነፃነት፣እኩልነት ፣ዴሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብት መከበር እንጂ ለግል ጥቅማቸው እንዳልሆነ በተግባር ያሳያሉ ። በኢትዮጵያ እየተዛባ ያለው የሀብት ክፍፍል   ፍትሃዊ እንዲሆን እንጂ መደመር እያሉ እየቀነሱ ለራሳቸው እና ለዘመዶቻቸው ሀብት ለማካበት የሚሯሯጡ ሰዎች በሰው ፓርቲ ውሥጥ  ቦታ እንደማይኖራቸውም በተግባር ያሳያል ። አምልኮተ ሰው እንዲፈጠር በፍፁም አያደርግም ።

” ሰው ፓርቲ ” የተለያዩ የማንቂያና የማስተማሪያ መንገዶችን ተደራሽ በሆነ መልኩ አዘጋጅቶ በማቅረብ ” ለካ እንዲህ ነን ። ” ብሎ ሰው እንዲያስብ በማድረግ ዛሬ ካለንበት ኢ ምክንያታዊ መገዳደል ነፃ ያደርገናል ። የግለሰብ አምልኮትንም ያስቀርልናል ።

የሰው ፓርቲ የሰውን መገዳደል ለማሥቆም የሚያሥችሉ ተከታታይ ትምህርቶች ፣ በተለያዩ የሚዲያ አውታሮች ይሰጣል ። ሥለ ፖለቲካ ሥለ ኃይማኖት፣ሥለቋንቋ ጅማሮ በሰ ውና በጥልቀት  ያሥተምራል ።

የአገሬ ሰው ሥለ ሰው  ፣ ሥለ ቋንቋ፣ሥለ ኃይማኖት አፈጣጠር ከሳይንስና ከእምነት አንፃር በሚገባ ካላወቀ በምክንያታዊነት ህይወትን መኖር አይችልም ። እናም ያሉን ውስን ምሁራን ዕውቀታቸውን ለመላው ህዝብ የሚያካፍሉበትን መድረክ ይፈጥራል ።

ፖለቲካም ሣይንሥ መህኑንን ተገንዝቦ ፣ መንግሥትን የመምረጥና የመሻር መብት ህዝብ እንዳለው በመገንዘብ የሚያገለግለውን ይመርጥ ዘንድ የማንቃት ሥራዎችን ህዝቡ ውሥጥ ገብቶ ይሰራል ።

ይኽ ብቻ አይደለም የዳርዊንን ቲዎሪ በአንድ ወገን  ኃይማኖታዊ ታሪክን  በሌላ ወገን በንፅፅር አሥቀምጦ በጨዋነት በማከራከር ለኢትዮጵያ ሰው   ዕውቀትን በምክንያታዊነት እንዲገነዘብ  ያላሰለሰ ጥረት ያደርጋል  ።

ይኽንን እና ሌሎች ጥበቦችን ለመዝራት እና የሰው ህሊና እንዲበለፅግ የሚተጋውን “ ሰው ፓርቲ “ እውን እንዲሆን የአገሬ ሰው ዛሬውኑ ተንቀሳቀስ ። ዛሬ ለዚህ ፓርቲ እውን መሆን ካልተቀሳቀስክ ነገ አገር አልባ ትሆናለህ ።

” ብልፅግና ፓርቲ ማለት በተግባር የድህነት ፓርቲ መሆኑንን አይተሃል ።  ሰውን አውድሞ እንዴት መበልፀግ እንደሚቻል ሊያሳይህ ሲባዝንም ታያለህ ።  ከኢህአዴግ ወደ ብልፅግና ከተቀየረ ማግሥት አንሥቶ የንፁሐን ደም አእምሮ በሌላቸው ፣ ሰውነታቸውን በካዱ ሰዎች  በከንቱ ሲፈስ ፤ ሲሰቃዩ፣ ሲጨፈጨፉ ፣ ሲቃጠሉ፣ ተ ቅዝቀው ሲሰቀሉ እያየ ገዳዮችን ለፍርድ ያላቀረበ ፤ የባስ ግድያው ክልላዊ እንዲሆን ያደረገ ። በትግራይ ወንድማማቾችን ያፋጀ ። ይኽንን በማድረጉ መፀፀቱን ሳይገልፅ ፤ የጦርነቱ ዋና አክተር ሆኖ ከአክተሮቹ ጋር ታርቀናል ያለ ።  ” ጦርነቱ ቲያትር ነበር ። “ ያለን  በትወራ ብቻ  ህዝብ መበልፀግ ይችላል ፤ ብሎ የሚያምን መሪ ያለው  የኢማጂኔሽን እና “ የባዛር “መንግሥት ነው ። “ ብልፅግና ! ( ፕሬዝዳንት ኢሣያሥ አፈወርቂ እንዳሉት ።)

ዛሬ በተግባር የብልፅግና ፓርቲ አገር እያፈረሰ ያለውም ከዚህ አሥተሳስብና ባህሪው የተነሳ ነው ። በተለይም ጠቅላዩ  ከዚህ በዛራዊነትና ኢማጅኒስትነት የተነሳ ፣ ሁሉንም ችግር በኢማጂኔሽን በማየትና ከነባራዊው እውነት በማፈንገጥ ፤  ድሮን እና ዙ 23  የኢትዮጵያን ውሥጣዊና ውጫዊ ችግሮች ይፈቱልኛል በሚል  አባዜ ውሥጥ ገብተው በማጥ ውሥጥ እየዳከሩ ነው ። ይኽም ድካሮ የክልል መሪዎቹን ሁሉ በማወናበድ ፣ እራሳቸውን ብቻ ሳይሆን አገሪቱን ወደ ገደል አፋፍ እያስጠጋት ነው ።

ሰውየው ፣ በአሰቃቂ ሁኔታ ጠፍተው አገርን ሊያጠፉ ከቀድሞ ቅኝ ገዢዎች ጋር የተማማሉ እሥኪመሥለን ድረስ የገዛ ወገናቸውን በግድ ለማሥገበር ወንድም ወንድሙን እንዲገድል ትዕዛዝ ሲሰጡ እያየን ነው ።  ይኽንን ሴጣናዊ  ትዕዛዝ ግን የመከላከያ መሪዎች አናሥፈፅምም ብለዋል ። ( የሳን ዙን የጦር ጥበብ በሚገባ የተረዱ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ሥላሉን እድለኞች ነን ። ) ለዚህ አሥተዋይነትና ታላቅነት  የከበረ ምሥጋና ይኽ ፀሐፊ ያቀርብላቸዋል ። ወደፊት የሚቋቋመው ” ሰው ፓርቲ ” የላቀ የሰብዓዊነት  የጀግንነት መዳሊያ ይሸልማቸዋል  ።

ሰው ፓርቲ አማራ ፣ ኦርሞ ፣ ሱማሌ፣ ትግሬ ፣ ሲዳማ ወዘተ ። መባባል አገር በመመራት ደረጃ ይቅር ።  የኢትዮጵያ ሰው የሚኖርበትን አካባቢ እንደ ባህሉ፣ ወጉ ፣ቋንቋው እራሱ በሚመርጣቸው ተወካይቹ ያሥተዳድር ።

የገጠር ቀበሌዎች በነፃ ምርጫ  የራሳቸውን መሪዎች ይምረጡ ። የከተማ ቀበሌዎችም የራሳቸውን ከንቲባ ራሳቸው ይምረጡ ። እኛ እንጂ ህዝብ አያውቅም ይብቃ ። እኛ እንጂ የሚሉን እኮ ትላንት በኢማጂኔሽን መኪና እየነዱ ወደሱቅ የሚሄዱ ከተርታው ህዝብ መሐል የተገኙ ሰው እኮ ናቸው  ¡¡

ይኽንን ሃቅ በማሳወቅ ፣ ወደፊት  በጭፍን የመነዳት ፣ በመንጋ የመወገን ፣ በሥሜት ብቻ የመደገፍን የኋላቀሮች ፓለቲካን   የሰው ፓርቲ በማሥቀረት   ኢትዮጵያውያን አንድ ልብ እንዲኖራቸው እንደሚያስችል አስባለሁ ። ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ፕሬዝዳንታቸውን በግልፅ ውድድር ፣ በምርመራ ጋዜጠኞች ጭመር በታገዘ የእጩ ፕሬዝዳንቶች ሥብዕና ምርመራ በውል አውቀው ለአራት ዓመት ብቻ እንዲያገለግላቸው ይመርጣሉ ። አንዴ የተመረጠ ለሁለተኛ ጊዜ ዕድል የሚያገኘው በአራት ዓመት የሰራው ሥራ ተመዝኖ ሲሆን በምርጫ ፉክክር ካሸነፈ ለተጨማሪ አራት ዓመት ፕሬዝዳንትነቱ ይራዘምለታል ።   ( በነገራችን ላይ ይኽ ፓርቲ ሥልጣን እንደያዘ ከጋዜጠኞች ጋር ተባብሮ የሚሰራ ና የመናገርን ተፈጥሯዊነት የሚያከብር ይሆናል ። አወራችሁ ፣ ተናገራችሁ ፣ ተሳደባችሁ በሚል  ተፈጥሮ አንደበትን ለመዝጋትም አይዳዳም ። አሁን ብልፅግና ተብየው በሁሉም ነገር የደኸየ ፓርቲ የሚፈፅመውን ከቶም አይደግምም ። )

እንግዲህ የዛሬውን  “ የበለው !ፍለጠው  ! ቁረጠውን  አገዛዝ ለማሶገድ , ብቸኛው አማራጭ ሰላማዊ ትግል ቢሆንም ፣ የአንዱን ጠባብ እና አውሬአዊ አሥተሳሰብ በሌላው ተመሳሳይ ጠባብነት እና ትምክህት  ለመተካት እንዳይሆንም የሰው ፓርቲ ይጠነቀቃል ። የሠለጠነ እና ሁሉም ሰዎች በእኩልነት የሚሳተፉበት እና “ የእኔ ነው ። “ የሚሉት  ፓርቲ በመሆንም የሰለጠነውን ዓለም ያስገርማል ።  የኢትዮጵያ ዜጎች ሁሉ ፣ በሰው ፓርቲ ዙሪያ ይሰባሰባሉ  ። የፓለቲካ ንቃታቸው ብቻ ሳይሆን ልባቸውን በተቻለ መጠን የሚመረምር መስፈርት አዘጋጅቶም ዓባላትን ይመለምላል ። ″ በሥነምግባር የኮሰመኑ እና በሆዱ የሚስብ የፓርቲው አባል አይሆኑም ። ″ የሚልና ሌሎች   ጠቃሚ ና ቅቡልነት ያላቸው መሥፈርቶች የአባልነት መመዘኛ ይሆናሉ ።

ይኸንን ″ ሰው የተሰኘ ና ለሰው ክብርና ልልና የሚተገል ፓርቲ ″  በውጪ አገር ያላችሁ በኣባልነት መቀላቀል ትችላላችሁ  ። መስፈርቶቹን ካሟላችሁ ። ይኽ ፀሐፊም መሥፈርቱን ካሞላ ብቻ ነው የሚሆነው ። በአገሬ ኢትዮጵያ ፣ እጅግ ምጡቅ እና ድንቅ  አእምሮ ያላቸው ዜጎች  ከፓለቲካ ጨዋታ ውጪ ናቸውና ወደ ጫወታው እንዲገቡ ና ይኽንን ፓርቲ በማቋቋም ሃሳቡን እውን እንዲያደርጉ በታላቅ አክብሮት እጠይቃለሁ ። ጠንካራ ፓርቲ ሳይኖረን ፣ በአምባገነንነት እና በአንድ ሰው ፈላጭ ቆራጭነት እየተመራ ፣ ድህነትን የሚያስፋፋውን ፣ ″ ግጭትና ጦርነት የሚጠምቀውን ″ ብልፅግና  የተሰኛ ፓርቲን  በምርጫ  ከቶም ልንቀይር  እንደማንችልም ከወዲሁ ብንገነዘብ መልካም ነው ።

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

182315
Previous Story

ፋኖ ማን ነው? ፋኖ አስከብሯል

182334
Next Story

የአብይና የነ ደመቀ ፍጥጫ | “ወደዳችሁም ጠላችሁም በድሮን አፈርሰዋለሁ” ዐብይ | “ያንተ ብልፅግና ይፍረስ ” ደመቀና መላኩ |Ethio 251 ኢትዮ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop