March 16, 2023
4 mins read

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ከጀርመን መንግሥት የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ ጋር በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጉ ተገለጸ

335719504 128714383484009 4329517205669378197 n 1 1
335719504 128714383484009 4329517205669378197 n 1 1

አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ

መጋቢት 5 ቀን 2015 ዓ/ም

አዲስ አበባ ሸዋ

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዚዳንት አቶ ማሙሸት አማረ እና ተቀዳሚ ፕሬዚዳንት እና የውጭ ጉዳይ ኃላፊ አቶ አብርሃም ጌጡ ከጀርመን መንግሥት የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ ከሆኑት ከቫንሳ ፕሪንዝ ጋር በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸው ተገልጧል።

ውይይቱ የተደረገው መጋቢት 5/2015 ዓ/ም ሲሆን በውይይቱም በርካታ ጉዳዮች የተነሱ መሆኑ ታውቋል።

ከተነሱ ጉዳዮች መካከልም:_

1) በአዲስ አበባ ዙሪያ ባለው ህገ ወጥ ቤት ፈረሳ፣

2) ወደ አዲስ አበባ የምግብ አቅርቦት አለመግባት፣

3) በሰላም ጉዳይ፣

4) በሀገሪቱ ወቅታዊ አጠቃላይ ጉዳይ፣

5) በሀገሪቱ ስለተከሰተው ጦርነት እና ውጤቱ፣

6) ሥለተፈፀመው እና እየተፈፀመ ሥላለው የሰብአዊ መብት ጥሰት ዙሪያ፣

7) ስለተፈናቀለው ዜጋ እና በማንነታቸው ላይ ያነጣጠረ ቤት ፈረሳን በተመለከተ፣

ግድያ፣ እስራት እና ንብረት ዘረፋ እንዲሁም አፍኖ መሠወርን በተመለከተ፣

9) በሀገሪቱ ውስጥ የደረሰው ድርቅ እና ረሀብ_በሰዎችና በእንሰሳት ላይ እያደረሰ ያለው ሞትና ሰደት፣

10) በአዲስ አበባ እየደረሰ ያለው የኑሮ ውድነት፣

11) ዜጎች በማንነታቸው እየተለዩ ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ መከልከላቸው በተለይም በአማራው ህዝብ ላይ ተጠናክሮ በቀጠለው ሰብአዊ የመብት ጥሠት ግልፅ በመሆነ መልኩ እየተፈፀመ በሚገኘው የዘር ፍጅት (genocide)

12) በሲዳማ እና ኦሮሞ ብሄረሠቦች እያንዣበበ ያለው ግጭት፣

13) በሶማሌ እና አፋር ያለውን የግጭት ሁኔታን በተመለከተ፣

14) በኦሮሚያ እና በሶማሌ ያንዣበበው ግጭት፣

15) ህገ መንግሥቱን ተከቶሎ በተነሣ የክልልነት ጥያቄ የደቡብ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ግድያ ፣ እስራትና ማዋከብ በተለይም በጉራጌና ወላይታ ላይ የሚደርሰውን እሥራት እና ግድያ፣

16) በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጉዳይ፣

17) በፍትህና የህግ የበላይነት ጉዳይ፣

18) በግፍ በታሰሩት የመኢአድ ከፍተኛ አመራር – በሆኑት የእንጦጦ አንባ ሁለተኛ ደረጃ መምህር ዘመነ ጌጤ ቦጋለ እና

የአዲስ አበባ የመኢአድ ም/ቤት አባል እና የቀድሞው የአዲስ አበባ የመኢአድ ሰብሣቢ አቶ ቴዎድሮስ ማሞ እንዲሁም

የፓርቲው አባል የሆኑት አቶ አካሉ ተምትሜ በግፍ የታሰሩ መሆናቸውን፣

19) 17 በሚሆኑ የደንቢ ዶሎ ዩኒቨርስቲ የአማራ ሴት ተማሪዎችን ደብዛ ጠፍቶ መቅረትን በተመለከተ፣

20) በአዲስ በተካለለው የኦሮሚያ የአስተዳደር – ከተሞች ጉዳይ እየደረሰ ያለው ተቃውሞ፣

21) በጉጅ ፣ በነገሌ ቦረና ኦሮሞዎች ላይ የሚደርሰውን እስራትና ድብደባ በተመለከተ

ከ3 ሰዓት በላይ የወሰደ ውይይት እና ጥልቅ ውይይት አድርገዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

180754
Previous Story

ኢትዮጵያዊው ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ባለሙያ ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዎርጊስ በሜልበርን አውስትራሊያ |

331621403 108251625549821 9045876669942140677 n 1 1
Next Story

አሳዛኝ ዜና ልብወለድ የሚመስል ግን “መራር እውነታ”

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop