“ሰው ነው የሚናፍቀኝ” ጋዜጠኛ ታዲዎስ ታንቱ

Meaza Mohammed-Lets be #voice for the #voiceless in thr international women's day
Meaza Mohammed – Lets be #voice for the #voiceless in thr international women’s day

መስከርም አበራ

ባለፈው እሁድ ጋሽ ታዲዎስን ልንጠይቅ ወደ ቂሊንጦ ጎራ ብለን ነበረ። ፍተሻውን አልፈን ከገባን በኋላ ረዘም ያለ ጉዞ የሚጠይቀውን የታሰሩበትን ዞን ሶስት ስንቃረብ ጭርታው አንዳች ደስ የማይል ነገር ይናገራል። “ማንን ልጥራላችሁ?” አለን ከውጭ የቆመው ጠባቂ፣ ነገርነው፣ ገባብሎ ተጣራና ተመለሰ።

ጋሽ ታዲዮስ ብቅ አሉ። ፀጉራቸው ከማደጉ በቀር ደህና አካላዊ ሁኔታ ላይ ናቸው። በንቁ አይኖቻቸው ቃኜት ሲያደርጉ እጄን አነሳሁላቸው። ወዲያው ቀልጠፍ ብለው መጡ። እኔን ሰላም ብለውኝ አብሮኝ ያለውን እንግዳ ግራ በመጋባት ማየት ጀመሩ። እሳቸው እንደማያውቁት እሱ ግን የከፈሉለት ዋጋ ግድ ብሎት ሊጠይቃቸው እንደመጣ ነገራቸው “አመሰግናለሁ የኔ ጌታ” አሉ በትህትና። “ኧረ! እንኳን እርስዎን ቤተሰብም መጠየቅ ነበረብን” አላቸው። “ምን ቤተሰብ ጋ ብትሄዱ ሻይ ቡና ተፈልቶላችሁ ትመጣላችሁ ይሆናል እንጅ እነሱ ምን ጥየቃ ይፈልጋሉ ብለህ ነው አሉት”

ወዲያው ወደ እኔ ዞረው ስሜን ጠርተው “እንዴት ነሽ!መቼ ተፈታሽ?” አሉኝ። “ቆየሁ እኮ! እርስዎ እንዴት ነዎት?” አልኩኝ ። “አካል ይደክም ይሆናል እንጅ በመንፈስ ጠንካራ ነኝ፣ ስለጠየቃችሁኝ አመሰግናለሁ፣እዚህ ስንሆን ሰው ይናፍቀናል ፣እንዲህ ስትመጡና ስትጠይቁን ደስ ይላል” አሉኝ ጠያቂ በናፈቀ ቅላፄ። እዳ ተሰማኝ ፣ሃፍረት ነገርም ሽው አለኝ።

ቀጠሉ “እኔ ሰው ነው የሚናፍቀኝ፣ ፍትህማ ቢናፈቅስ ከየት ይገኛል? አሁን አሁን የሚያደርጉኝን ዝም ብዬ ማየት ጀምሬያለሁ” አሉኝ። አብሮኝ የመጣው ሰው በሃዘን አንገቱን ሲደፋ አየሁት ። ስለፍርድ ቤት ጉዳይ ጠየቅኳቸው። “አንዷ ተከላካይ ምስክር ነሽ፣ ክሱን ወስደሽ አንብቢና መጥሪያ ሲደርሰሽ መገኘት ነው፣ታለማ አልነገረሽም? ” አሉኝ ፈርጠም ብለው ። ታለማ ጠበቃቸው ናቸው። “ነግረውኛል፣ እሽ እገኛለሁ” አልኩኝ ። አይበገሬነታቸው፣ንቁነታቸው ገረመኝ!!! “በሉ ሂዱ ይበቃል ፣ሲመቻችሁ ብቅ በሉ መቼም በቶሎ የሚለቀኝስ አልመሰለኝም” አሉ እንደመሳቅ ብለው። ሰው እንደናፈቃቸው አስተዋልኩ፣ልቤ አዘነ! “ፍትህ ከፈጣሪ ነው ይፈታሉ ፣እኔ መጥቼ እጠይቅዎታለሁ” ብዬ ተሰናብተን ወጣን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አሳዛኝ ዜና ልብወለድ የሚመስል ግን "መራር እውነታ"

ጠንካራው ሰው በእጅጉ ሰው ይናፍቃቸዋል፣ ለምን እንደታሰሩ የሚገባው፣ውለታ የሚከብደው ሁሉ ሊጠይቃቸው ይገባል። ማስፈታት በሰው እጅ ነው፣መጠየቅ ግን በእጃችን ነው!

5 Comments

  1. ጎበዝ ከግርጌ የምንጽፋትን እያያችሁ አውጡልን ብዙ ሰው እንድታስተናግዱ፡፡ ጸሃፊዋ መስከረም አበራ ተሸላሚዋ መአዛ መሃመድ፤ታሳሪው ክቡር ታዲዮስ ታንቱ፡፡ እንዴት ያለ ግጥምጥሞሽ ነው በዛሬይቷ ኢትዮጵያ ሰው በባትሪ ቢፈለግ ከነዚህና ከእስክንድር ነጋ የተሻለ ዜጋ የለም፡፡ እግዚአብሄር ከናንተ ጋር ይሁን ሆዳም ሆዳሙ እየቀለለ ሲመጣ እናንተ ክብደታችሁ እየጨመረ ይመጣል፡፡ መአዛዬ ስራሽ እውቅና አግኝቷል በኦሮሞ ጨካኞች ስለሚታረዱት ስለታገቱት የትምህርት ቤት ልጆችና ስለ አቶ ታዲዮስ ታንቱ አትሰልችብን ዛሬ ላይ ከአብይ በላይ ክብርና እውቅናን አግኝተሻል፡፡ ጎበዝ ዳንኤል ክብረት በጤናው ነው? አሁንስ ለሱ ማዘን ይዣለሁ ምንም ሳይጎድለው ጠርቶ አረከሰው፡፡ ይኸው ነው እንግዲህ ምኑን የወደደ ማእረጉን ይጠላል የተባለው ብዙ ደክሞ ነበር በቤተ ክርስቲያን አገልግሎቱ ቀስ ብለው ጠርተው ስራውን አቆሸሸበት እኔን እሱን ብሆን 2 አመት እሰወርና ንስሃ ገብቼ የአብይን ካባ ወደዛ ወርውሬ ቤተ ክርስቲያንን አገለግል ነበር፡፡ ይህ እንዳለ ሁኖ ስለ አባ ማትያስ የተናገረው ግን አንዱም ስህተት የለበትም፡፡

    • የኢትዮጵያ ትልቁ ችግር “ችግር” ፈጣሪዎችንና ማህበረሰብን ከማህበረሰብ ጋር ለማጋጨት ሆን ብለው የሚሰሩ ዘረኞቹንና ከአማራ ውጭ ሌላ የማይታያቸውን እስክንድር ነጋን፣ መስከረም አበራንና ይህ ጦርነት የአቢይ አህመድና የህወሓት ነው አማራ አትዋጋ፣ እንዳውም የኛ ጥረት አማራን የማይጎዳ ማዕቀብ ኢትዮጵያ ላይ እንዲጣል ነው ያለችውን መዐዛ መሐመድን እንዲሁም ጧትና ማታ ኦሮሞን መሳደብ ስራው ያደረገውንና የአማራ ዩቲዩበሮች እያመጡ የሚያሰድቡትን ታዲዮስ ታንቱን የጀግንነት ምልክት ማድረጋችን ነው። ምነው እውነትም ኢትዮጵያችን ሰው አጣች እንዴ?

  2. Well done. Thank you so much for visting Great Tadios Tantu in Abiy Ahemde’s gail.
    Free Tadios Tantu, Sentayehu Chechol and so many Prisiners of conscience in Ethiopia.

  3. Well done Meski. Thank you so much for visiting Great Tadios Tantu in Abiy Ahemde’s gail.
    Free Tadios Tantu, Sentayehu Chechol and so many Prisiners of conscience in Ethiopia.

  4. ስብሀት ነጋንና የትግሬ አራጃችን ለቅቆ አቶ ታድዮስ ታንቱን ማሰር ምን የሚሉት ስብእና ነው?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share