February 1, 2023
7 mins read

የታከለ አስደንጋጭ ዝርፊያ ሲጋለጥ! – እናኑ ጥላሁን

takeleለማመን_የሚከብድ ለምስኪን ኢትዮጵያዊ የማይገባ ኔክስት ሌቭል ዘረፋ የሰማሁት ከኤርሚያስ አመልጋ ቀጥሎ በታኬ እኮ ነው እህእ የመጀመሪያ ታኬ እንደመጣ ያደረገው የሼኩን መሬት መቀማት ነው። 11 መሬቶች ወደ መሬት ባንክ አስመለስኩ ብሎ ጀግና ጀግና ሲጫወት ሰዉም የአብይ ፍቅር ትኩስ የነበረበት ስለነበር አብሮ ተንጫጫ (የዚ ውጤት በኋላ እመለሳለሁ) ሁለተኛው ዙር ቅርጠፋ የተማሪዎች ምገባ ና ዩኒፎርም ተባለ። በዚህም ለአራት ድርጅቶች ዩኒፎርም አድቫንስ ሲከፈል አንዱ ድርጅት አድቫንሱን 75 ሚል ሙሉ በሙሉ ተከፋፍለው እጄ ላይ የቀረው 16 ሚል ነውና መስሪያ ስለሌለኝ ዩኒፎርሙን ማስረከብ አልችልም የምታስገድዱኝ ከሆነ የወሰዳችሁበትን አወጣለሁ ብሎ ሽምግልና ተልኮ እንደነበር ስንቶቻችሁ ታስታውሳላችሁ

ወዲያው የኮተቤ መንገድን መጨረስ ተብሎ የኮተቤ መንገድ ፀሀይ ከጠለቀበት ተክለብርሀን ላይ ተወስዶ ለድሪባ ደፈርሻ (ግማሹን ጀምሮ ስለነበር ያለጨረታ) ጀባ ቢባልም በአገር ልጅነት ተቀባበለ ግን እንዳሰበው ብሩ አልሆነምከዛ የሀገር ቤት ኮንትራክተር በዶላር ለአሁኑ የአሜሪካ ጉዞ እንደማያዋጣ የገባው ታኬ የመስቀል አደባባይን ፕሮጀክት ለቻይኖቹ በ2.5 ቢል እና የቄራን መንገድ በኪሜ 400 ሚል ለ4 ኪሜ 1.6 ቢል ያለጨረታ ከፍሎ አስጀመረ (በኢትዮ ታሪክ ውዱ መንገድ የቦሌ መንገድ ሲሆን እሱም በኪሜ 60 ሚል ነበር የወጣበት) ይህም ከጫማና ከቺክ ያልዘለለ ብር መልሶ ወደ አንደኛው ደንበኛው ወደ ሚድሮክ ፊቱን መልሶ መሬቶቹን በድርድር ግማሹን በአብነት ግማሹን በሚድሮክ ስም በአብዛኛው እንዲመለስ ሆነ። (የአሁኑ የሼኩና የአብነት ክስ ወሎ ሰፈር ጋር ያለውን ማየት ነው) ይህ በዶላር ጉቦ መቀበል ያስጀመረው የመጀመሪያው የመሬት ኬዝ ሙሉ በታኬ ጊዜ የተሰጡ ትልልቅ ካሬዎች ኒዮርክ ብር የገባባቸው ናቸው። (የሸገር ታይምስን ዶክመንተሪ እዩአቸው)

በዚህ የጀመረው የታኬና የአብነት እከክልኝ የወርቁን መሬት እኮ ማስመለስ እችላለሁ በሚል ሚድሮክ ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ሹም ሽር አስነስቶ አረጋን ወደ ዩኒቲ ታከለን ወደ ማእድን አብነትን ወደ ሸራተን የወሰደ ጉዞ ነበር። (ስለ ሚድሮል ካቢኔ ሹም ሽር የአብነት በሼኩ ንብረቶች ላይ ጠቅላይ መሄድና የጀማል ተሽሎክልኮ አለቃውን ማስወጋት ልብወለድ መፅሀፍ የሚወጣው ከአገር መፈንቅለ መንግስት የማያንስ ጨዋታ ለሌላ ጊዜ ይቀመጥልን)

ከዛማ በአመት 600 ሚል ዶላር የሚልከውን የሚድሮክ ጎልድ ንብረት ከጃዋርና ከድንቁ (የጃዌ ባንክ ሮለር በገንዘቡ ጃዌ በአክቲቪስትነቱ ያንን ማእድን ማዘጋቱ ይታወሳል) አፍ ላይ ታኬ ወደ ሼኩ፣ ሼኩም በዱባይ ወደ ታኬ የመጀመሪያው ትራንሳክሽን ተጀመረ። እንደው ሰው ከከንቲባነት ወደ ማእድን ሲመደብ እንዴት እንዳንል (በሲቪል ተመርቆ የመጀመሪያ ስራ ያገኘ የሚል ሚም አስታውሳለሁ) ያኔ በጊዜው አበቤ ከንቲባ ካልሆንኩ ብላ አብይን አስቸገረች ተብሎ አይኑ ከታኬ ላይ ተነሳለት።

ይህን የለመደው ታኬም ከዚ በኋላ 38 የማእድን ፈቃዶችን ልክ እንደ መሬቱ በመሰረዝ መልሶ መውሰድ የፈለገ ደጅ እንዲጠና በማረግ ያቺኑ ስልቱን ተጠቅሞ ስራውን ጀመረ። አሁን በቅርብ እንኳን የእንግሊዙን ከፊ ሚኒራል ጨምሮ 55 ፍቃዶችን ሰርዞ ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት ድራማ ሲሰራ ነበር። በወሩ የተመለሰላቸው አየን እንጂ ከዛማ ታኬ ደስ ሲለው ቢሮዬ እየታደሰ ነው በሚል ቢሮውን ሸራተን፣ ደስ ሲለው መንግስት ቢሮ ውስጥ ማማስ ኪችንን በማስገባት የጀመረው ላግዠሪ ታኬ የአራዳ ልጅ የሚል ማእረግ አሰጥቶታል(በ30 ብር ሰብሲዳይዝድ ምግብ የሚበላ የማእድን ሚኒስቴር ሰራተኛን እና ኮንዶ የወሰደ የእግር ኳስ ደጋፊ አባቴ ቢለው አይደንቅም)። በመጨረሻም ሚሊኒየም አዘጋጅቶ የነበረው የማእድን ኤግዚቢሽን ላይ ለሱና ለጓደኞቹ ፋሽን ሾ በፖዲየሙ ላይ በቫዮሊን ታጅበው እያዩ ውጪ 15 ኩንታል ሲሚንቶ በቸርነቱ እያደለ ነጫጮቹ ድንኳኖች ለሊት በተሰለፉ ሰዎች ሞልቶ ያየሁ ግዜ ግን ለመጀመሪያ በባለስልጣን ያዘንኩበት አጋጣሚ ነበር።
_
አፍሪካ ኢዝ ኤ ዱምድ ኮንቲኔንት። የተለየ የሚያረግ የሚሆን የለም። ታኬም አጦዘው እንጂ ከሽመልስ ወይም ከራሱ ከአብይ የተለየ አስተሳሰብ የለውም። አልፈርድበትም ግን በሌብነቱ እኮንነዋለሁ። ደሞም ለዚ ህዝብ ይገባዋል። ብርሀኑ ለምን ተማሪ ጣለ ብሎ የሚኮንን፣ የሚሰራለት እና የሚሰራበት ያልገባው ህዝብ እንደ ታኬ አይነት አክተር ባለስልጣን በጣም ዲዘርቭ ያደርጋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

Go toTop