“ከቋንቋ አበደ“ የፖለቲካ ጡዘት መቼ ነው የምንወጣው? – መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

መግቢያ

WHO THE CAP FIT
SONG OF BOB MARLY .
Man to man is unjust_
Children ya don’t trust
Your worst enemy
Coud be your friend
And your best friend
Your worse enemy.
Some will eat and drink with you
Then behind them su_sopon you
Only your friend know your secrets
So only he could reveal it.
And who that cap fit
Let them wear it .
Said i throw me corn
Me no call no fowl
I saying “cook _cook _ cook _ cluk _ cluk
Same will hate you ,pretend they love you now
Then behind they try to eliminate you , but who Jan bless
No one curse !
Thank God we have past the worse
Hypocrites and parasites
Will come up and take a bite .
And if your night should turn to day,
A lot of people would run a way
And who the cap fit
Let them wear it .

በኢትዮጵያችን  በልቡ ውሥጥ ያለውን ንፁህ እውነት  በነፃነት  መናገር የሚያሣሠርበት እንዲህ በቀላሉ መድረሳችን በበኩሌ እጅግ ግርም ይለኛል ።

የሰለጠነው ዓለም ኮመዲያን በግልፅ በአደባባይ በመንግሥት ባለሥልጣናት ደርጊት ከበሸቀው  ህዝብ ጋር በመወገን  ፖለቲካዊ የልብ ትርታው አዳምጠው በቀልድ እያዋዙ ባለሥልጣናቶቻቸውን ተው ፣ እረፉ ይኽ ለዚህ ህዝብና አገር አይመጥንም በማለት ይመክራሉ ። ምንም መራራ እና የሚያንገፈግፍ ተረብ ቢደርስባቸው ባለሥልጣናቱ ከሥህተት መንገዳቸው ከማር ባሻገር በቀልድ አሥመሥሎ ሰድቦኛልና ዘብጥያ ይውረድ ብለው ከቶም አያውቁም ። እዚህ አገር አስብቶ ማረድ ፤ ልኩን አሳየው በማለት የራስ ቆዳን በማዋደድ ( ራቁታቸውን እንደተወለዱ ና ራቁታቸውን እንደሚቀበሩ በመካድ ) ዜጎች ተፈጥሮ በሰጣቸው አንደበት ለምን ተናገሩበት ብለው ለእግረ ሙቅ የሚዳርጉ መከሰታቸው እናንተንስ አይገርማችሁም ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በህገመንግስቱም ቢሆን ወልቃይት ጠገዴና ራያ የአማራ እንጅ የትግራይ ሊሆኑ አይችሉም!!!

እንዴት በዚች ቅድስት አገር   መልካም አንደበት ላይ የተጣመመ ሃሳብ እንዳለ ወይም ከግለሰቡ ዳቢሎሳዊ ሃሳብ እንደወጣ በቅቤ ምላሱ በማሣበቅ ፣ በሥራው ብቻ ታምኖ ንፁሐን ዘብጥያ ይወርዳሉ ? እንዴት የተፈጥሮ አንደበታችን  ያሶግረናል ?  ( ይላሉ ለእውነት ብለው የታሰሩ ምሁራን ። )

በእርግጥ በኢትዮጵያ ከደርግ የሶሻሊዝም የአብዮተኛ እና የፀረ አብዮተኛ ፍረጃ ጀምሮ ውሸት ነግሷል ። ንፁሐን ያለ  ፍትህ ፣ ፍርድ ቤት ሣይቀርቡ ፣ በግለሰቦች የግል ውሳኔ ፣ በነፃ እርምጃ ይገደሉ ነበር ።ያም እኩይ ድርጊት የፍየል ወጠጤ እየተዜመ በሬዲዮ ሞታቸው ይነገር ነበር ። ከደርግ በኋላ   ደሞ  ፤ መልኩን ቀይሮ ብቅ አለ ። የእነሱ እና የእኛ ቋንቋ ። ሰውን በቋንቋው መከፋፈል ።ሰውን ከፋፍሎ  በየቋንቋው መፈረጅ ።ከአንድ ቋንቋ ቤተሰብ የተወለደ ግለሰብን ድርጊት ብትኮንን መላውን የቋንቋውን ቤተሰብ እንደተዳፈርክ የሚቆጠርበት ።  ( የእገሌን ልጅ ተናገርክ ፤ ሰደብክ ፤ ነገሩን ፣ ድርጊቱነሰ ኮነንክ ፤ …አንተ እንትን ሥለሆንክ ። የሚሉ የነገር ቅደም ተከተሎችና ወጊዎች የበረከቱበት ።)  ማስተዋል የጠፈበት ዘመን ።

አሁንማ ብሶል ። እንደ ኮስ አበደች ሁሉም ቋንቋውን እየጠለዘ ነው ። ኳስ አበደች እንደሚባለው ” ቋንቋ አበደ ” እንበል ?

ከዚህ ” ከቋንቋ አበደ ” የፓለቲካ ጡዘት መቺ ነው የምንወጣው ?  የሠለጠኑትን ፣ በዕውቀት የተራቀቁትን አገራት ሰውኛ መንገድ ከመከተል ይልቅ ፣ ” ድንቁርናችን ወርቅነው ። ” እያልን ጭረሻ የማንደማመጥን መንገድን አጠንክረን እየገነባን እኮ ነው  ።

ተመልከቱ ፣ ፈጣሪ ያሳያችሁ ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ሆነ ፌደሬሽን ምክርቤት በአማርኛ ሥብሰባውን እያካሄደ ፣ እንደ አንድ አገር ዜጋ አንድ  ለመሆን የሚያሥችለንን ፣ በአፍሪካውያን ክብር የሚሰጠውን ፣ የራሳችንን ፊደል አማርኛን ለምን በየክልሉ የሥራ ቋንቀ ለማድረግ እንዳቃተን ይታያችኋልን ?

ተጨማሪ ያንብቡ:  "ድንቅ " ሌክቸር!

እኛ ኢትዮጵያዊያን ፣ ዛሬ እና አሁን ያልባነንን መቼ እንደምንባንን ከቶም አይገባኝም ። መንግሥት ህዝብን በሚበጀው ወይም ሁሉንም ተጠቃሚ በሚያደርገው ፣ ዜግነቱን በሚያሶድደው መንገድ ህዝብን መመራት አለበት እንጂ በጠላቶቻችን በሚዘወሩ ኢ _ ሰው እና ፀረ _ፍቅር በሆኑ ባለነፍጥ ፖለቲከኞች ማስፈራርቾ እሥከመቼ ፓለቲካውን  እያስታመመ አገርን በተረጋጋ ሁኔታ ማሥተዳደሩን በወከባ ይቀጥላል ?

የበለፀጉት አገራት ታሪክ የሚነግረን ጠንካራ መንግሥት ለመገንባት በወታደራዊ ህግ ብቻ የሚመራ መከላከያ ሠራዊት እና የአገርን ጠላቶች አሥቀድሞ በማነፍነፍ የሲቪሊና ወታደራዊ ደህንነት አሥቀድሞ መገንባት ያሥፈልጋል ። ( ዛሬም የተጠናከረ የደህንነትና የመከላከያ ተቋም እንዲኖራቸው ለነዚህ ተቋማት የሚያወጡት ወጪ የሠራዊት እንክብካቢያቸው ከፍተኘ ነው ። )  እኛም በአቅማችን ከፍተኛውን በጀት   ለመከላከያ ና ለደህንነት ኃይል በመሥጠት መንግሥትን አጠናክረን ፣ በዜጎች ቅቡልነት ያለው ተከታታይ የሆነ ጠንካራ መንግሥታዊ ተቋማ ሊኖረን ይገባል ። ብዬ አምናለሁ ። በዚህ ረገድ የመንግሥት ጥረት የሚያስመሰግነው ቢሆንም ፣ ከፓለቲካው አንፃር ግን ፈቀቅ ያለ ተጨባጭ ለውጥ በበኩሌ አላየሁም ። መንግስት ዛሬ በከፍተኛ “ የማንን ልመን ? “ ጥርጣሬ ውሥጥ የወደቀም ይመሥለኛል ።

ዛሬ እና አሁን  መንግሥት እንደግለሰብ ማንን ማመን ማንንስ ያለማመን ጥርጣሬ ውሥጥ ሊወድቅ የቻለው ፣ካለፈው የደርግ አዙሪት ያልወጣ የፓርቲ አባላትን ይዞ ሥለሚጓዝ ነው ። እርግጥ ነው በሥም ፓርቲው ተለውጧል ። በግብር ግን የተለወጠ አንዳች ነገር የለም ። መንግሥት በአንክሮ ከተመለከተ ዘሬም የሚጓዝበት አደረጃጀት ደርግ ከመሠረተው ቀበሌ ና ገበሬ ማህበር የሚነሳ ነው ። ዛሬም የማዘጋጃ  ተቋማዊ ሥርዓት የለም ።  ዛሬም ፓርቲና መንግሥት አልተለየም ። በመሆኑም በፓርቲ ሥም  ከቀበሌ ጀምሮ በሰው ነፍሥ የሚወሥኑ እግዜሮች ቢኖሩ አይገርምም ። ከደርግ ጀምሮ ነበሩና !!!!!!!!

ተጨማሪ ያንብቡ:  የጎሕ መንፈስ (በየነ ሞገስ)

በበኩሌ መንግሥት ወይም ገዢው ፓርቲ  ለ21 ኛው ክ/ዘ የሚመጥን የመንግሥት ሥርዓት ለማዋለድ አንድ ብርቱ ዘዴ ካልቀየሰ በታሪክ ተወቃሽ ሊሆን የሚችልበት መሥቀለኛ መንገድ ላይ እንዳለ ይታየኛል ።

በተለይም በትግራይ  ያለው ፣ ሰው መሆንን የካደ የሊሂቅ ሥብሥብ አጥፍቶ መጥፋት አላማው ነውና አሁንም የኢትዮጵያ ህዝብ በሆነው መሬት በእኔነው ባይነት በብርቱ ይከራከራል ። ይኽንን ህዝብን ከህዝብ የማጋጨት እኩይ መንገድ እንዳቋረጥ ፣ በኢትዮጵያ ህዝብ ቅቡል የሆነ ልዩ ዘዴ እና ዘላቂ መፍትሄ የሚያመጣ አዲስ የዜጎች እኩልነት መንገድን  መንግሥት ሣይዘገይ መቀየሥ ይኖርበታል ብዬ አምናለሁ ። ያ ዘዴም የትግራይ ህዝብ ሰውነትን በካደው ፣ የትግራይ ሊሂቅ ላይ የሚነሳበት እና እሥከወዲያኛው የሚጠራርገው መሆን ይኖርበታል ። ልብ በሉ የትግራይ ህዝብ እንደ ኢትዮጵያዊነቱ የኢትዮጵያ ግዛት ሁሉ አገሩ መሆኑንን በተጨባጭ ከተረጋገጠለት እጅግ የሚያስደንቅ ኢትዮጵያዊነቱን የወያኔንን ግብአተ መሬት በመፈፀም ያረጋግጣል ።

እያንዳንዱ ሰው ፣የራሱ አእምሮ እንዳለውም ተገንዘቡ ። ዛሬ ባለማወቅ ያደረሰው ጥፋት ነገ ወደ ህሊናው ሲመለስ ና ከድንቁርና    ሲፋታ ይገባዋል ።

በመጨረሻም ህዝብ ይነቃ ዘንድ እንደ ቦብ ማርሊ ህዝብን በኪነት የሚያነቁ ከያኒያንን እና የጥበብ ሰዎችን ፈጣሪ ያብዛልን ። ከወዳጅ ጠላታችን እንድን ዘንድ በማለት ፅሑፌን እቋጫለሁ ።

………………………

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share