July 10, 2022
11 mins read

“ከቋንቋ አበደ“ የፖለቲካ ጡዘት መቼ ነው የምንወጣው? – መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

12334445rrr

12334445rrrመግቢያ

WHO THE CAP FIT
SONG OF BOB MARLY .
Man to man is unjust_
Children ya don’t trust
Your worst enemy
Coud be your friend
And your best friend
Your worse enemy.
Some will eat and drink with you
Then behind them su_sopon you
Only your friend know your secrets
So only he could reveal it.
And who that cap fit
Let them wear it .
Said i throw me corn
Me no call no fowl
I saying “cook _cook _ cook _ cluk _ cluk
Same will hate you ,pretend they love you now
Then behind they try to eliminate you , but who Jan bless
No one curse !
Thank God we have past the worse
Hypocrites and parasites
Will come up and take a bite .
And if your night should turn to day,
A lot of people would run a way
And who the cap fit
Let them wear it .

በኢትዮጵያችን  በልቡ ውሥጥ ያለውን ንፁህ እውነት  በነፃነት  መናገር የሚያሣሠርበት እንዲህ በቀላሉ መድረሳችን በበኩሌ እጅግ ግርም ይለኛል ።

የሰለጠነው ዓለም ኮመዲያን በግልፅ በአደባባይ በመንግሥት ባለሥልጣናት ደርጊት ከበሸቀው  ህዝብ ጋር በመወገን  ፖለቲካዊ የልብ ትርታው አዳምጠው በቀልድ እያዋዙ ባለሥልጣናቶቻቸውን ተው ፣ እረፉ ይኽ ለዚህ ህዝብና አገር አይመጥንም በማለት ይመክራሉ ። ምንም መራራ እና የሚያንገፈግፍ ተረብ ቢደርስባቸው ባለሥልጣናቱ ከሥህተት መንገዳቸው ከማር ባሻገር በቀልድ አሥመሥሎ ሰድቦኛልና ዘብጥያ ይውረድ ብለው ከቶም አያውቁም ። እዚህ አገር አስብቶ ማረድ ፤ ልኩን አሳየው በማለት የራስ ቆዳን በማዋደድ ( ራቁታቸውን እንደተወለዱ ና ራቁታቸውን እንደሚቀበሩ በመካድ ) ዜጎች ተፈጥሮ በሰጣቸው አንደበት ለምን ተናገሩበት ብለው ለእግረ ሙቅ የሚዳርጉ መከሰታቸው እናንተንስ አይገርማችሁም ።

እንዴት በዚች ቅድስት አገር   መልካም አንደበት ላይ የተጣመመ ሃሳብ እንዳለ ወይም ከግለሰቡ ዳቢሎሳዊ ሃሳብ እንደወጣ በቅቤ ምላሱ በማሣበቅ ፣ በሥራው ብቻ ታምኖ ንፁሐን ዘብጥያ ይወርዳሉ ? እንዴት የተፈጥሮ አንደበታችን  ያሶግረናል ?  ( ይላሉ ለእውነት ብለው የታሰሩ ምሁራን ። )

በእርግጥ በኢትዮጵያ ከደርግ የሶሻሊዝም የአብዮተኛ እና የፀረ አብዮተኛ ፍረጃ ጀምሮ ውሸት ነግሷል ። ንፁሐን ያለ  ፍትህ ፣ ፍርድ ቤት ሣይቀርቡ ፣ በግለሰቦች የግል ውሳኔ ፣ በነፃ እርምጃ ይገደሉ ነበር ።ያም እኩይ ድርጊት የፍየል ወጠጤ እየተዜመ በሬዲዮ ሞታቸው ይነገር ነበር ። ከደርግ በኋላ   ደሞ  ፤ መልኩን ቀይሮ ብቅ አለ ። የእነሱ እና የእኛ ቋንቋ ። ሰውን በቋንቋው መከፋፈል ።ሰውን ከፋፍሎ  በየቋንቋው መፈረጅ ።ከአንድ ቋንቋ ቤተሰብ የተወለደ ግለሰብን ድርጊት ብትኮንን መላውን የቋንቋውን ቤተሰብ እንደተዳፈርክ የሚቆጠርበት ።  ( የእገሌን ልጅ ተናገርክ ፤ ሰደብክ ፤ ነገሩን ፣ ድርጊቱነሰ ኮነንክ ፤ …አንተ እንትን ሥለሆንክ ። የሚሉ የነገር ቅደም ተከተሎችና ወጊዎች የበረከቱበት ።)  ማስተዋል የጠፈበት ዘመን ።

አሁንማ ብሶል ። እንደ ኮስ አበደች ሁሉም ቋንቋውን እየጠለዘ ነው ። ኳስ አበደች እንደሚባለው ” ቋንቋ አበደ ” እንበል ?

ከዚህ ” ከቋንቋ አበደ ” የፓለቲካ ጡዘት መቺ ነው የምንወጣው ?  የሠለጠኑትን ፣ በዕውቀት የተራቀቁትን አገራት ሰውኛ መንገድ ከመከተል ይልቅ ፣ ” ድንቁርናችን ወርቅነው ። ” እያልን ጭረሻ የማንደማመጥን መንገድን አጠንክረን እየገነባን እኮ ነው  ።

ተመልከቱ ፣ ፈጣሪ ያሳያችሁ ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ሆነ ፌደሬሽን ምክርቤት በአማርኛ ሥብሰባውን እያካሄደ ፣ እንደ አንድ አገር ዜጋ አንድ  ለመሆን የሚያሥችለንን ፣ በአፍሪካውያን ክብር የሚሰጠውን ፣ የራሳችንን ፊደል አማርኛን ለምን በየክልሉ የሥራ ቋንቀ ለማድረግ እንዳቃተን ይታያችኋልን ?

እኛ ኢትዮጵያዊያን ፣ ዛሬ እና አሁን ያልባነንን መቼ እንደምንባንን ከቶም አይገባኝም ። መንግሥት ህዝብን በሚበጀው ወይም ሁሉንም ተጠቃሚ በሚያደርገው ፣ ዜግነቱን በሚያሶድደው መንገድ ህዝብን መመራት አለበት እንጂ በጠላቶቻችን በሚዘወሩ ኢ _ ሰው እና ፀረ _ፍቅር በሆኑ ባለነፍጥ ፖለቲከኞች ማስፈራርቾ እሥከመቼ ፓለቲካውን  እያስታመመ አገርን በተረጋጋ ሁኔታ ማሥተዳደሩን በወከባ ይቀጥላል ?

የበለፀጉት አገራት ታሪክ የሚነግረን ጠንካራ መንግሥት ለመገንባት በወታደራዊ ህግ ብቻ የሚመራ መከላከያ ሠራዊት እና የአገርን ጠላቶች አሥቀድሞ በማነፍነፍ የሲቪሊና ወታደራዊ ደህንነት አሥቀድሞ መገንባት ያሥፈልጋል ። ( ዛሬም የተጠናከረ የደህንነትና የመከላከያ ተቋም እንዲኖራቸው ለነዚህ ተቋማት የሚያወጡት ወጪ የሠራዊት እንክብካቢያቸው ከፍተኘ ነው ። )  እኛም በአቅማችን ከፍተኛውን በጀት   ለመከላከያ ና ለደህንነት ኃይል በመሥጠት መንግሥትን አጠናክረን ፣ በዜጎች ቅቡልነት ያለው ተከታታይ የሆነ ጠንካራ መንግሥታዊ ተቋማ ሊኖረን ይገባል ። ብዬ አምናለሁ ። በዚህ ረገድ የመንግሥት ጥረት የሚያስመሰግነው ቢሆንም ፣ ከፓለቲካው አንፃር ግን ፈቀቅ ያለ ተጨባጭ ለውጥ በበኩሌ አላየሁም ። መንግስት ዛሬ በከፍተኛ “ የማንን ልመን ? “ ጥርጣሬ ውሥጥ የወደቀም ይመሥለኛል ።

ዛሬ እና አሁን  መንግሥት እንደግለሰብ ማንን ማመን ማንንስ ያለማመን ጥርጣሬ ውሥጥ ሊወድቅ የቻለው ፣ካለፈው የደርግ አዙሪት ያልወጣ የፓርቲ አባላትን ይዞ ሥለሚጓዝ ነው ። እርግጥ ነው በሥም ፓርቲው ተለውጧል ። በግብር ግን የተለወጠ አንዳች ነገር የለም ። መንግሥት በአንክሮ ከተመለከተ ዘሬም የሚጓዝበት አደረጃጀት ደርግ ከመሠረተው ቀበሌ ና ገበሬ ማህበር የሚነሳ ነው ። ዛሬም የማዘጋጃ  ተቋማዊ ሥርዓት የለም ።  ዛሬም ፓርቲና መንግሥት አልተለየም ። በመሆኑም በፓርቲ ሥም  ከቀበሌ ጀምሮ በሰው ነፍሥ የሚወሥኑ እግዜሮች ቢኖሩ አይገርምም ። ከደርግ ጀምሮ ነበሩና !!!!!!!!

በበኩሌ መንግሥት ወይም ገዢው ፓርቲ  ለ21 ኛው ክ/ዘ የሚመጥን የመንግሥት ሥርዓት ለማዋለድ አንድ ብርቱ ዘዴ ካልቀየሰ በታሪክ ተወቃሽ ሊሆን የሚችልበት መሥቀለኛ መንገድ ላይ እንዳለ ይታየኛል ።

በተለይም በትግራይ  ያለው ፣ ሰው መሆንን የካደ የሊሂቅ ሥብሥብ አጥፍቶ መጥፋት አላማው ነውና አሁንም የኢትዮጵያ ህዝብ በሆነው መሬት በእኔነው ባይነት በብርቱ ይከራከራል ። ይኽንን ህዝብን ከህዝብ የማጋጨት እኩይ መንገድ እንዳቋረጥ ፣ በኢትዮጵያ ህዝብ ቅቡል የሆነ ልዩ ዘዴ እና ዘላቂ መፍትሄ የሚያመጣ አዲስ የዜጎች እኩልነት መንገድን  መንግሥት ሣይዘገይ መቀየሥ ይኖርበታል ብዬ አምናለሁ ። ያ ዘዴም የትግራይ ህዝብ ሰውነትን በካደው ፣ የትግራይ ሊሂቅ ላይ የሚነሳበት እና እሥከወዲያኛው የሚጠራርገው መሆን ይኖርበታል ። ልብ በሉ የትግራይ ህዝብ እንደ ኢትዮጵያዊነቱ የኢትዮጵያ ግዛት ሁሉ አገሩ መሆኑንን በተጨባጭ ከተረጋገጠለት እጅግ የሚያስደንቅ ኢትዮጵያዊነቱን የወያኔንን ግብአተ መሬት በመፈፀም ያረጋግጣል ።

እያንዳንዱ ሰው ፣የራሱ አእምሮ እንዳለውም ተገንዘቡ ። ዛሬ ባለማወቅ ያደረሰው ጥፋት ነገ ወደ ህሊናው ሲመለስ ና ከድንቁርና    ሲፋታ ይገባዋል ።

በመጨረሻም ህዝብ ይነቃ ዘንድ እንደ ቦብ ማርሊ ህዝብን በኪነት የሚያነቁ ከያኒያንን እና የጥበብ ሰዎችን ፈጣሪ ያብዛልን ። ከወዳጅ ጠላታችን እንድን ዘንድ በማለት ፅሑፌን እቋጫለሁ ።

………………………

Leave a Reply

Your email address will not be published.

OLF
Previous Story

በኦሮሚያ ክልል ዘር ማጥራት ጭፍጨፋው በአብይ አህመድና በኦሮሚያ ክልል መንግስት የተቀነባበረ ነው ሲል ጃልመሮ ገለፀ

174552
Next Story

የጫካውን ኦነግ ሸኔ ማጥፋት ቀላል ነው። ያስቸገረን የቢሮው ኦነግ ሸኔ ነው።

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop