June 19, 2022 ዜና 3 mins readየአማራ ፋኖ ላይ የጦር ብርጌዱን ያለሃፍረት ያዘመተው ጠቅላይ ሚኒስትር – ግርማ ካሳ “ሱቅ እየገቡ ዕቃ ይሰርቃሉ የሚል የፌዝ ክስ በማቅረብ የጦር ብርጌዱን የአማራ ፋኖ ላይ ያለሃፍረት ያዘመተው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ፣ ዘመነ ካሴን ለመያዝ በምድር አንድ ክፍለጦር ያዘመተ እና በሰማይ የጦር ድሮኖቹን ለሰዓታት በጎጃም ሰማይ ላይ እንዲበሩ ያደረገ ጠቅላይ ሚኒስትር ፣ ሕወሓት ጋር በተደረጉ ውጊያዎች የኢንተርኔት እና የስልክ አገልግሎት ጭምር ሙሉ ለሙሉ እንዲቋረጥ ለማድረግ መወሰን የደፈረ ጠቅላይ ሚኒስትር ፣ በሶማሌ ክልል አብዲ ኢሌ ላይ እና በደቡብ ክልል ወላይታ ላይ ፈጣን እርምጃ ለመውሰድ የወሰን ጠቅላይ ሚኒስትር በየዕለቱ ዘግናኝ የሆኑ ግድያዎች የሚፈፀምበት ኦሮሞ ክልል ላይ መጨከን እና የማያዳግም እርምጃ መውሰድ እንዴት ተሳናቸው ? ኦሮሞ ክልል ሲሆን ለምን ያመነታሉ ?”ብሎ ይጠይቃል፡፡ እርምጃ ለመውሰድ ያመነታ አይመስለኝም፡፡ እርምጃ ለመውሰድ ሞክሯል፡፡ ነገር ግን ፡1ኛ እርሱ መንግስት ውስጥ ፣ ደህንነት መስሪያ ቤት፣ መከላከያ ውስጥ ፣ እንዲሁም የኦሮሞ ክልል ልዩ ኃይል ውስጥ ኦነጎ አሉበት፡፡ እንቅስቃሴ ለማድረግ ሲወሰን፣ ኦነግ አስቀድሞ መረጃ ይደርሰዋል፡፡ ስለዚህ የአብይ መንግስት ራሱን ኦነግ ስለሆነ፣ ራሱን ማሸነፍ አልቻለም፡፡ ጦርነትን የሚወስደው ደግሞ በዋናናነት ወታደራዊ መረጃ ነው፡፡2ኛ የወታደራዊ አመራር ብቃት የለውም፡፡ ማውራት እንጂ የጦር ስትራቴጂ አያውቅም፡፡ አንዴ አቁሙ ይላል። አንዲ ቀጥሎ ይላል፡፡ የርሱ የጦር አዝማችነት ታች ያሉ መኮንኖችም ግራ ያጋባበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡3ኛ የፖለቲካ ውሳኔዎቹ ህዝቡን የሚያቅፍ ሳይሆን የሚገፋ፣ አምባገነናዊ በመሆኑ፣ ወጣቶችን ማሰር፣ ማወክ፣ ማሸበር ስለበዛ ነው፡፡ ኦህዴድ ከሕወሃት የባሰ አፋኝ ስለሆነ፣ ኦነግ አራት እጥፍ ጭራቅ ቢሆንም፣ ብዙ ተከታዮችን ለማግኘት ችሏል፡፡ በወለጋ በተለይም በርካታ የወረዳና የዞን አመራሮች ሁለት ኮፍያ ያላቸው ናቸው፡፡ ቀን ቀን የኦህዴድን ኮፍያ ያደርጋሉ፣ ማታ ማታ የኦነኝ ኮፍያ ያደርጋሉ፡፡ አብይ በፖለቲካው ረገድ የሕወሃት ሶስት እጥፍ አፋኝ መሆኑ ቀርቶ ህዝቡን ቢያከብር ኖሮ፣ ኦነግ የትም አትደርስም ነበር፡፡ Facebook X Pinterest Linkedin Whatsapp Reddit Email 1 Comment ግርማ ካሳ ያልከው እንዳለ ሁኖ በአደባባይ “ኦሮሞ ኦሮሞን አይገድልም” ብሎ እንደ ነገረን ኦሮምያ ክልል ብለው በጠሩት የሚላከው ወደ ሰማይ የሚተኩስ ሳይሆን አይቀርም።ReplyLeave a Reply Cancel replyYour email address will not be published. Δ Previous Storyሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ.ም. በምዕራብ ወለጋ ዞን ግምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ በሲቪል ሰዎች ላይ ስለደረሰው ጥቃት Next Storyለቸኮለ! ሰኞ ሰኔ 13/2014 ዓ.ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች Latest from Blog ደራሲና ገጣሚ፡- አበረ አዳሙ በአማራ ምሁራን መማክርት ጉባኤ ላይ ያቀረቡት ግጥም ደራሲና ገጣሚ፡- አበረ አዳሙ በአማራ ምሁራን መማክርት ጉባኤ ላይ ያቀረቡት ግጥም ጎጃም አቸፈር አገዛዙን በጣም አስደንግጧል | ብ/ጀኔራሉ ባህርዳር ላይ ተሸኘ ብ/ጀኔራሉ ባህርዳር ላይ ተሸኘ የጦር አውሮፕላኖች በሽሬ ሰማይ ህወሃት ሌላ ጦርነት አወጀ ብ/ጀኔራሉ ባህርዳር ላይ ተሸኘ የጦር አውሮፕላኖች በሽሬ ሰማይ ህወሃት ሌላ ጦርነት አወጀ አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን የጀኔራሎች ግምገማ ሾልኮ ወጣ ” ከአቅማችን በላይ ሆኗል” የክልሉ ፕሬዚዳንት ደብዛቸው ጠፋ የጀኔራሎች ግምገማ ሾልኮ ወጣ ” ከአቅማችን በላይ ሆኗል” የክልሉ ፕሬዚዳንት ደብዛቸው ጠፋ
ግርማ ካሳ ያልከው እንዳለ ሁኖ በአደባባይ “ኦሮሞ ኦሮሞን አይገድልም” ብሎ እንደ ነገረን ኦሮምያ ክልል ብለው በጠሩት የሚላከው ወደ ሰማይ የሚተኩስ ሳይሆን አይቀርም።Reply
ደራሲና ገጣሚ፡- አበረ አዳሙ በአማራ ምሁራን መማክርት ጉባኤ ላይ ያቀረቡት ግጥም ደራሲና ገጣሚ፡- አበረ አዳሙ በአማራ ምሁራን መማክርት ጉባኤ ላይ ያቀረቡት ግጥም
ብ/ጀኔራሉ ባህርዳር ላይ ተሸኘ የጦር አውሮፕላኖች በሽሬ ሰማይ ህወሃት ሌላ ጦርነት አወጀ ብ/ጀኔራሉ ባህርዳር ላይ ተሸኘ የጦር አውሮፕላኖች በሽሬ ሰማይ ህወሃት ሌላ ጦርነት አወጀ
አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
የጀኔራሎች ግምገማ ሾልኮ ወጣ ” ከአቅማችን በላይ ሆኗል” የክልሉ ፕሬዚዳንት ደብዛቸው ጠፋ የጀኔራሎች ግምገማ ሾልኮ ወጣ ” ከአቅማችን በላይ ሆኗል” የክልሉ ፕሬዚዳንት ደብዛቸው ጠፋ