መንኪ ፖክሥን   የምንጠነቀቅበት ሰዓት  ላይ ደርሰናል – መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

“መንኪ  ፖክሥ “ ምሥራቅ አፍሪካ ደርሷል ። በቦሌ ባይገባ በሞያሌ ፣ በቶጎ ጫሌ ና በአርት ሼክ  ፤  በደሎ መና ፣ ወይም በቦረና ፤ አልያም በሞያሌ ወይም በመተማ ና ሁመራ ፣ በአፋር ፣ በአሶሣ እና   በኦጋዴን ወዘተ ። ሊገባ ይችላል ። እናም በቅርቡ በኢትዮጵያም ቁጥራቸው ጥቂት የማይባሉ ህመምተኞች ሊኖሩን ይችላሉ ። በበኩሌ እንደባለሙያ ትልቅ ሥጋት አለኝ ። ምንም እንኳ ክፉኛ ከታመሙ የቫይረሱ ተጠቂዎች አንዱ ብቻ   እንደሚሞት ፣ በጥናት ቢረጋገጥ ና በሽታው ባይካበድም ከወዲሁ ልዩ “ የመንኪ ፖክሥ “ ግብረሃይል ማቋቋም አሥፈላጊ ይመሥለኛል ።

ይኽ በሽታ አንድ ሁለት ቦታ እንደ ብጉር እብጠት አሣይቶ በማግሥቱ ፊትን እና ሰውነትን የሚወሩ እብጠቶች እንደማፈጥር ና እንደሚያሥደነግጥም ከወዲሁ ህዝብ መረዳት አለበት ። ለ21 ቀንም የታገሠ እና በቂ የምልክቶቹን መከላከያ መድሃኒት ያገኘ ህመምተኛ ሁሉ መዳን እንደሚችልም እወቁ ። እናም ለዚህ ለመንኪ ፖክሥ የግል  ኳራንቲን ሥለሚያሥፈልግ ለመንግሥት ሠራተኞች ( የልማት ድርጅቶችን ጨምሮ )  ልዩ የህመም ወይም “ የቀሣ “ ፈቃድ የያዘ መመሪያ ፣ በሚቋቋመው ግብረሃይል በኩል   እንዲወጣ ቢደረግ መልካም ይመሥለኛል ። አለበለዚያ በሽታው በቀላሉ ሊዛመት ይችላል ።

መንኪ ፖክሥ ፣   በመባል የሚታወቀውን እና በመላ ሰውነት ላይ የተቀቀለ ማሽላ የመሠሉ ሆኖም ከማሽላ ተለቅ የሚሉ እባጮችን የሚፈጥረውን    ቫይረስ  በእንሥሣት ላይ በቸደረገ ምርምር ለሠጀመሪያ ጋዜ የተረጋገጠው በመካከለኛውና በምእራብ አፍሪካ በ1958 ዓ/ም እጎአ ነው ። በሽታው በሰው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የተከሰተው ግን በቀድሞዋ ዛየር በአሁኖ ዲሞክራቲክ ኮንጎ ፤ በ1970 ዓ/ም እጎአ  መሆኑ በዓለም የበሽታ ድርሳን ውሥጥ ተመዝግቧል ። ያውም በቀይ ቀለም ። …

ይኸው በዓለም የበሽታ ድርሳን ውሥጥ በቀይ ቀለም የተመዘገበው ሰበቡ ቫይረሥ የሆነው ህመም እንሆ ዛሬ  ና አሁን ከግንቦት 7 ( እጎአ ) ጀምሮ በኢንግላንድ  ተከስቶ መላ አውሮፓን እና አሜሪካን እያሥፈራራ አፍሪካ ደርሷል ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የተጣበቁት መንትዮች እና አስጨናቂው የ6 ሰዓታት ቀዶ ሕክምና - በመላኩ ብርሃኑ (ከአዲስ ጉዳይ መጽሔት)

ይህ ኩፍኝ መሠል ሆኖም ከኩፍኝ መጠናቸው የጎላ እብጠቶችን በሰውነት በሙሉ ና በብዛት ደግሞ በፊት ገፅ  ላይ የሚፈጥረው እና በትኩሳት ፣ በማንቀጥቀጥ ፣በራሥ ምታት ፣ በጀርባ ህመም ፣ በጡንቻ ህመም ና በጉሮሮ ህመም ፣ ሥሜት የሚታወቀው ወረርሺኝ ይኼን ያህል አሥጊና ለመቆጣጠርም የሚያዳግት መድሃኒት አልባ አይደለም ። ማንም ሰው እውቀትን በእውነት ሊገነዘብ የገባልና ይኽ በወረርሺኝ መልክ የተከሰተው በሽታ ከፈንጣጣ  ጋርም የማይመሣሠል ነው ።  ፈንጣጣ ወይም “ አንትራክስ “ በባክቴሪያ የሚመጣ ገዳይ በሽታ ነው ። ሃያላኑ አገሮች በላብራቶሪ አባዝተው  በባዮሎጂ ጦር መሣሪያነት  አከማችተው እንደያዙትም በውሥጥ አዋቂዎች እና በጠርጣሪዎች ይወራል ።  እናም ይኽ ፀሐፊ የዝንጀሮ ፈንጣጣ የሚባለው ጩኸት በመንኪ ፖክሥ ጩኸት እንዲቀየር ይኽ ፀሐፊ  አበክሮ ይጠይቃል ። ጫማና ኩፍያ የሆነ አደናጋሪ ገለፃ ነውና ! ከእውነት የራቀ ትርጉም ይሆናልና  !

ይኽ መንኪ ፖክሥ ፣  በተጨማሪ ፣ ዛሬ እና አሁን አሜሪካ፣ ሲውዲን እሥፔን ፣ ፖርቹጋል እና ኢጣሊያ መከሰቱ ታውቋል ። ዛሬ ደግሞ በአፍሪካ ። በድንገት  የወረርሽኙ ተጠቂዎች   በመከሰቱ ፣ አገራቱ ህመምተኞቹን በየሆሥፒታሎቻቸው አግለው እያከሟቸው ነው ። በሌሎች  የአውሮፓ አገሮችም ወረርሽኙ እንደገባ ይወራል  ። በአፍሪካችን ግን የቤት ውሥጥ “ ቀሣ “ አሥፈላጋ    ነው ። እንደ በለፀጉት አገራት ኢኮኖሚያችን  አይፈቅድምና !

የህነው ሆኖ ፤ የወረርሽኙ ዛሬ በአውሮፖና በአሜሪካ መግባት በእግዳነት የሚታይና የሚያሥደነግጥም አይደለም ። ከላይ እንደገለፅኩት ይኽ የዝንጀሮ ኩፍኝ ( Monkey pox ) በማለት ሥም የተሠጠው ወረርሽኝ በ2003 በአሜሪካ ተከስቶ እንደንደነበር ይታወቃል  ። በወቅቱ ከ70 የማይበልጡ ሰዎችንም ይኽ መንኪ  ፖክስ ይዞ ነበር ።

እናም ፣  ይኽ በቫይረሥ የሚመጣ ኩፍኝ መሠል በሽታ ፣ በቀላሉ በፀረ ቫይረሥ መድሃኒቶች መታከም የሚችል መሆኑ ጥንትም ይታወቃል ። ( ጥንቃቄ አድርጉ እንጂ ፈንጣጣ በማለት አሥፈራሪ ትርጉም በመሥጠት ማካበዱ አለአሥፈላጊ ነው ። )

በቅጡ ለመገንዘብም የዩቲዩቡን ዜና እና የነቢቢሲን ዘገባ መርምሩ ። ይኽ በቫይረስ የሚመጣ በመላ ሠውነት የሚያሥጠለ የትልልቅ ቡገር አይነት እባጭ   የሚፈጥር እና በ21 ቀን የሚሰናበት ነው  ።በቃ ። በዋነኝነት የሚተላለፈው በአይጥ ፣ በአይጠ መጎጥ ና በፍልፈልና በመሣሠሉት እንጂ  በዝንጀሮ አይደለም ። ዝንጀሮ ዋንኛ አሥተላላፊ አይደለም ። ሆኖም የዝንጀሮ ዘመድ አዝማድ ሁሉ  በበሽታው ይያዛል ። ያኔም እርሱ ነበር በ1958 ዓ/ም ጥናት የተካሄደበት ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ቲማቲምን የመመገብ የጤና ጥቅሞች (በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም)

” በተያዘ ሰው ላይ ጥናት አልተካሄደምን ? ” በማለት ጥያቄ መጠየቅ ተገቢ ነው ። እንካችሁ መልሱን ።

በመንኪ ፖክሥ   የተያዘ ሰው ከ 5 እሥከ 21 ቀናት በበሽታው መያዙ ሊረጋገጥ ይችላል ። ወይም የበሽታዎቹ ሥሜቶች በነዚህ ቀናት ይታዩበታል ። በበሽታው መያዙ ከታወቀ በኋላ ከበሽታው ለመዳን እሥከ አራት ሣምንት ሊፈጅበት ይችላል ።

በመንኪ ፖክስ  የተያዘ ሰው ይኽንን ቫይረሥ በሚያሥነጥስ እና በሚያሥል ጊዜ ሊያሥተላልፍ ይችላል   ከህመምተኛው የተቀቀለ ማሽላ  ከመሠሉ  ችምችም ካሉ እባጮቸ ጋር መነካካትም በሽታውን ያሥተላልፋል    በግብረ  ሥጋ ግንኙነት  ጊዜም በሽታው ወደጤነኛ ሰው ይተላለፋል 

ይኽ እንግሊዝና እሥፔንን ጭምር ያዳረሰው እና ወ አፍሪካ ጎራ ያለው ፣  መንኪ ፖክስ ” አይነተኛው ቫይረስ ”  ምንጩ ፣ በመካከለኛውና በምዕራብ አፍሪካ ነው ።  ቢባልም ፣ በእንግሊዝ በወረርሽኙ ከተያዙት  8ቱ ወደ ካናዳ እንጂ ወደ አፍሪካ ተጉዘው የማያውቁ መሆናቸው ታውቋል ።

እናም ወደፊት  ሣይንቲሥቶቹ ተመራምረው የዚህ ቫይረሥ ምንጭ ፣ የአውሮፖና  የአሜሪካ ምሥጢራዊ ላብራቶሪ ነው ።  ባይሉንም እኛ ሰው ነን እና መጠርጠራችን አይቀርም ።

1 Comment

  1. ፈንጣጣ ሥሞል ፖክሥ በቫይረስ የሚከሰት ፣ በክትባትም መከላከል የተቻለ ከዓለም ላይ እንዲጠፋ ርብርብ የተደረገበት በሽታ ነው ። አንትራክሥ ወይም አባሠንጋ ተብሎ በእኛ አገር የሚታወቀው የበሽታ በገዳይ ባክቴሪዬ የሚመጣ በዚሁ ህመም የታመመ ከብትን ሥጋ በመመገብ የሚከሠት ፣ አጣዳፊ ገዳይ በሽታ ነው ። እንደ እሥሞል ፖክሥ ወይም ፈንጣጣ ጊዜ የሚሰጥ አይደለም ። የዛሬውም የመንኪ ፖክሥ ወረርሽኝ ጊዜ የሚሰጥ ሆኖም ጥንቃቄን እና ቁጥጥርን የሚሻ በሽታ ነው ። ( አንባቢ ሆይ ይህንን በፅሐፌ ከአንትራክሥ ጎን በወሽመጥ አሥገብታችሁ በማንበብ ፅሑፉን በተሟላ ሥዕል እንድትገኘዘቡልኝ በአክብሮት እጠይቃለሁ። )

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share