የማፊያ ከበርቴዎች!!

ከነብዩ አለማየሁ (ኦስሎ)

በኢትዮጵያ አንድ ግለሰብ ወይም company ቢዝነሱ የሚሳካው ወይ ካጭበረበረ ወይም መንግስት አካባቢ ሰው ካለ ወይም ጉቦ ከሰጠ ነው።ለነገሩ ዋና ዋናው ቢዝነስ የተያዘው በህውሀት ሰዎችና ጀሌዎቻቸው ነው። በሌላው ሀገር ተራውን ህዝብ መንግስት የሚያገለግለው በታላላቅ የንግድ ተቑማት ላይ ጠቀም ያለ ታክስ በመጣል ነው። እኛ ሀገር ግን በርካታ ከገዢውፓርቲ ጋር ግንኙነት ያላቸው በጣም አነስተኛ ታክስ የሚከፍሉና ጭራሽ የማይክፍሉም ሞልትዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ በትክክለኛው መንገድ ታክስ የሚከፍለው የመንግስት ሰራተኛ ብቻ ነው። የኑሮ ጫና ግራ ያጋባው አነስተኛ ገቢ የሚያገኘው በስግብግብ ነጋዴዎች ገንዘብ የሚዘረፈው ሀይ ባይ መንግስት ያጣው ይህው የህብረተሰብ ክፍል ነው። በጣም የሚገርመው መንግስት በተለያዩ ነገሮች መዋጮ ሲፈልግ እፋጦ የሚቀበለው ይህንኑ የህብረተሰብ ክፍል ነው። ይህ የህብረተሰብ ክፍል የበይ ተመልካች ሆኖ ኑሮውን መግፋት የለበትም በቃ ማለት አለበት ።ምክንያቱም ቅኝ መገዛት ከዚ በምን ይለያል።
የወያኔ መንግስት የሀገሪቱን የንግድ ህግ እንዳሻው እየለዋወጠ በሀገሪቱ በሌሎች ግለሰቦችና ድርጅቶች የተያዘውን ቢዝነስ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የራሱ እያረገ ለ23 ዓመት ዘልቋል። ወያኔ እንደመንግስት የማያሰራ የንግድ ፍሰት የሚያሰራ የቢዝነስ ህግ በማውጣትና በመተግበር ፈንታ እንደተራ ማፊያ ሆኖ ነጋዴዎችንና የቢዝንስ ሰዎችን በማዳከም የራሱን ኤፈርት የተባለ የማይጠረቃ ድርጅቱን ያጠናክራል። ለምሳሌ በቅርብ ጊዜ ውዲህ የሃገር ውስጥ አስመጪዎችን ናላ አያዞረ ያልው የውጭ ምንዛሬ እጥረት የሃገሪቱን የንግድ ስርአት አደጋ ውስጥ ሲጥለው የህውሀት አባሎችና ጀሌዎቻቸው ግን ባንኮችን እንደ ግል ካዝናቸው ይጠቀማሉ። በጣም የሚገርመው ደግሞ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ነጋዴዎች አሰልቺ በሆነው የውጭ ምንዛሬ ወረፋ ለወራት ሲጉላሉ የባንኮች ገዥ ተብልው የሚሾሙት የህውሀት አሻንጉሊቶች በቲቪ እየቀረቡ የውጭ ምንዛሬ ሞልቶ ተርፉል ይላሉ።
ከሁሉም በላይ እጅግ በጣም የሚያስገርመው ደግሞ የዚህ የንግድ ጉዳት በሀገር ኢኮኖሚ እድገት ላይ የሚያመጣውን አደጋ ዞር ብለው ማስተዋል አለመቻላቸው ነው ። በቅርብ ጊዜ እንደሰማነው የህውሀት ማፊያ መንግስት ሲያያቸው ያላማሩትንና የወያኔ አባላት ያልሆኑትን በርካታ ድርጅቶች ታክስ አጭበርብራቹሀል ብሎ ሲከሳቸው ሰምተናል ሲጀመር ወያኔ ድርጅቶችን በታክስም ሆነ በአንፃር ህግ በመጣስ የመክሰስ የሞራል ሆነ የህሊና ብቃት የለውም። በርካታ የህውሀትና የጀሌዎቻቸው ድርጅቶች ታክስ በማጭበርበር ና ማሀበረሰቡን የሚጎዱ ምርቶችን ለገበያ እንደሚያቀርቡ እናቃለን። ለአብነት ያሀል ከወራት በፊት እንድ የህውሀት ጀሌ የባሀር ዳሩን ጊዎን ሆቴል በጥቂት ሺ ብሮች ኪራይ የግሉ እንዳረገው ሰምተን አዝነናል።
ህውሀት ወያኔ በየትኛውም መልኩ ቢሆን የሀገር መምራት ብቃት የሌለው የወንበዴዎች ስብስብ ነው የኢትዮጵያ ህዝብ ይህንን የወንበዴዎች ስብስብ የባሰ ችግር ውስጥ ሳይከተው ልጅ አዋቂ ሳይል ሆ ብሎ ተነስቶ ማስወገድ አልበት።
ሞት ለአምባገነኖች ኢትዮጵያችን ለዘላለም በክብር ትኑር!!!!!!!!

ተጨማሪ ያንብቡ:  ‹‹አብይ ማደሪያ የለው፣ ግንድ ይዞ ይዞራል!!!›› አንድ ለእናቱ እስክንድር ነጋ!!! እና የደም ነጋዴዎች!!!  (ክፍል ሁለት)

2 Comments

  1. ባህር ዳር ላይ በርካሽ ኪራይ በምጠላው አነጋገር ትግሬ ወያኔ ግዮን ሆቴልን መከራየቱን በዚህ ፅሁፍ ተረዳሁ:: እውነት እንደሆነም አምናለሁ:: ምክንያቱም ከዚህ የበለጡ ብዙ አይን ያወጡ የዘረኝነት መድሎዎችንና ዘረፋዎችን ሲያካሂዱ ነበረና:: ይህ ነገር ወያኔን ለመሰለ አውሬ ትልቅ ሰይጣናዊ የሞራል እሴት ነው::
    ሌሎቻችን ግን እንዲህ እናስብ:: እንዲህ:_ አንድ ባህርዳሬ መቀሌ/አድዋ ላይ ከአካባቢው ህዝብ ጋር ‘ተጫርቶ’ አንድ የ’መንግስት’ ሆቴል በርካሽ ዋጋ ሲከራይ ይታያችሁ:: ጉዱ በል ጎጃም! ጎጃም ለይቶላት የጉድ አገር ሆነች ማለት ነው? በቀደምለት የሚሰነፍጥ ልጋጋምነታችንን በገዛ ‘አለምነዉ መኮንና’ችን ሰማን:: በ’ፌዴራል ሀገር’ አማራው እንዴት ቢደህይ ነው ከትግራይ ‘የተሰደደ’ ወያኔ ሊያውም በመናኛ ዋጋ ግዮንን ሊከራይ የቻለው? ታሪክ መዝጋቢዎች መዝግቡልኝ:: ሁላችንም ሂሳብ የምናወራርድበት ጊዜ መምጣቱ ስለማይቀር ያኔ እንነጋገራለን:: ለአሁኑ ግን ይህ ነገር በሚዘገንን ሁኔታ ያሳዝናል_ ጤናማነት ለሚሰማው (የአለም) ዜጋም እንደሰው ያሳፍራል:: መጥኔ ለነገ ታሪካቸው!!! መጥኔ ለእንስሳዊ ተፈጥሮኣቸው መጨረሻ!!!እኛስ የመከራና ስቃይ አቀበቱን እያገባደድነው ነነ…

  2. ባህር ዳር ላይ በርካሽ ኪራይ በምጠላው አነጋገር ትግሬ ወያኔ ግዮን ሆቴልን መከራየቱን በዚህ ፅሁፍ ተረዳሁ:: እውነት እንደሆነም አምናለሁ:: ምክንያቱም ከዚህ የበለጡ ብዙ አይን ያወጡ የዘረኝነት መድሎዎችንና ዘረፋዎችን ሲያካሂዱ ነበረና:: ይህ ነገር ወያኔን ለመሰለ አውሬ ትልቅ ሰይጣናዊ የሞራል እሴት ነው::
    ሌሎቻችን ግን እንዲህ እናስብ:: እንዲህ:_ አንድ ባህርዳሬ መቀሌ/አድዋ ላይ ከአካባቢው ህዝብ ጋር ‘ተጫርቶ’ አንድ የ’መንግስት’ ሆቴል በርካሽ ዋጋ ሲከራይ ይታያችሁ:: ዘይቤ ለውጠን ‘ጉድ በል ጎጃም!’ ብንልስ? ጎጃም ለይቶላት የጉድ አገር ሆነች ማለት ነው? ይገርማል:: በቀደምለት የሚሰነፍጥ ልጋጋምነታችንን በገዛ ‘አለምነዉ መኮንና’ችን ሰማን:: በ’ፌዴራል ሀገር’ አማራው እንዴት ቢደህይ ነው ከትግራይ ‘የተሰደደ’ ወያኔ ሊያውም በመናኛ ዋጋ ግዮንን ሊከራይ የቻለው? ታሪክ መዝጋቢዎች መዝግቡልኝ:: ሁላችንም ሂሳብ የምናወራርድበት ጊዜ መምጣቱ ስለማይቀር ያኔ እንነጋገራለን:: ለአሁኑ ግን ይህ ነገር በሚዘገንን ሁኔታ ያሳዝናል_ ጤናማነት ለሚሰማው (የአለም) ዜጋም እንደሰው ያሳፍራል:: መጥኔ ለነገ ታሪካቸው!!! መጥኔ ለእንስሳዊ ተፈጥሮኣቸው መጨረሻ!!!እኛስ የመከራና ስቃይ አቀበቱን እያገባደድነው ነነ…
    By the way I am not against the seizure of the hotel by a tigrian person; I oppose the ontention and the skewed procedure applied solely to favor the tigrian. Otherwise, both are mine! no problem in that.

Comments are closed.

Share