February 18, 2014
13 mins read

እየተዋረዱ መገዛት እስከመቼ!?

በቅዱስ ዬሃንስ
አለምነው መኮነን የተባለ የብአዴን ወኪልና የባንዳ አስፈፃሚ የአለቆቹን የዘወትር አባባል በማስረገጥ እመራዋለሁ የሚለውን የአማራ ህዝብ <<ሰንፋጭ የሆነ ትምክህተኝነት የተጠናወተው፤ ትምክህተኝነቱን ያልተው፤ በባዶ እግሩ እየሄደ መርዝ ንግግር የሚናገር ወዘተ>> ካለ በኋላ <<የትምክህት ልጋጉን ማራገፍ አለበት>> በማለት እንደሌሎች ብሄረሰቦች ሁሉ ደከመኝ፡ ሰለቸኝ ሳይል ዋጋ የከፈለውን የአማራ ህዝብ ዋጋ በማሳጣት የሌሎቹ ጠላት አድርጐ በማቅረብ፡ የዘረኞች ተባባሪነቱን አስመስክሯል።
የአማራው ህዝብ የወያኔ ዘረኞች ዋነኛ ዒላማ ሆኖ የአገዛዙን የግፍ ፅዋ ያለማቋረጥ መጋት ከጀመረ ድፍን 23 አመታት ተቆጠሩ። ፋሽስቱ ወያኔ የኢትዮጵያን ህዝብ ብሔራዊ ስሜት በማምከን ፣ የዘመናት ተገዥነቱን ለማረጋገጥ በቅድሚያ የአማራን ሕዝብ ማንነት ማጥፋት ፣ የአማራን ሕዝብ ስነ ልቦናዊ ጥንካሬ መስለብ እና አንገቱን ማስደፋት አስፈላጊ መሆኑን በጽናት ያምናል። ይህ በመሆኑም ፣ በአማራ ህዝብ ላይ በወያኔ የሚፈፀመው ግፍ እና በደል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ስር እየሰደደና እየከፋ በግልፅም በስውርም በተቀነባበረ መንገድ ቀጥሏል።
ይህ የህወሀት የጸረ አማራ ፕሮፓጋንዳ ማሽን የሚመራው በዋና ዋናዎቹ የወያኔ ሹሞች ቢሆንም ወያኔ የአማራን ህዝብ የሚገድለዉ፤ የሚያዋርደዉና የሚያሳደድዉ አማራ ነን በሚሉ ነገር ግን የአማራን ህዝብ በጅምላ በሚሰድቡና አማራዉ ሲገደል፤ ሲታሰርና ሲፈናቀል ይበልህ በሚሉ በእነ አለምነው መኮንን አይነት ወፍ ዘራሽ ካድሬዎች ነው። አንበሳ ሲያረጅ የዝንብ መጫወቻ ይሆናል እንዲሉ፡ የአማራው ህዝብ ዛሬ ቀን ጣለውና፣ በጠላቶቹ እጅ ወደቀ፣ የድፍን ስድና መረን ያደገ ዋልጌ ሁሉ የስድብና የዘለፋ አፍ ማሟሻ የመሆን ዕጣ ደረሰው። አለምነው መኮነን የተባለ የብአዴን ወኪልና የባንዳ አስፈፃሚ የአለቆቹን የዘወትር አባባል በማስረገጥ እመራዋለሁ የሚለውን የአማራ ህዝብ <<ሰንፋጭ የሆነ ትምክህተኝነት የተጠናወተው፤ ትምክህተኝነቱን ያልተው፤ በባዶ እግሩ እየሄደ መርዝ ንግግር የሚናገር ወዘተ>> ካለ በኋላ <<የትምክህት ልጋጉን ማራገፍ አለበት>> በማለት እንደሌሎች ብሄረሰቦች ሁሉ ደከመኝ፡ ሰለቸኝ ሳይል ዋጋ የከፈለውን የአማራ ህዝብ ዋጋ በማሳጣት የሌሎቹ ጠላት አድርጐ በማቅረብ፡ የዘረኞች ተባባሪነቱን አስመስክሯል።
በርግጥ ወያኔ እንደፈረስ የሚጋልበው ብአዴን በታሪኩ አንድም ለህዝቡ የቆመ መሪ ሲያፈራ አልታየም። የአማራ ህዝብ ብአዴንን የመሰለ አሳፋሪ ድርጅት በታሪኩ ገጥሞት አያውቅም። በባዕድ ወረራ ጊዜ ለጣልያን ያደሩ ባንዶች እንኳን ከዛሬዎቹ ብአዴኖች የተሻለ ክብር ነበራቸው። ከዛሬዎቹም በተሻለ በጌቶቻቸው ጣሊያኖችን ይሰሙ ነበር። ብአዴን ግን ራሱን ከባንዳነትም አውርዶ ባርነት ደረጃ ላይ የጣለ ከመሆንም አልፎ በባርነቱ የሚደሰት ድርጅት ነው። ብአዴን የህወሓት ወያኔ ወኪል እንጅ የአማራው ህዝብ ወኪል አይደለም፡፡ ብአዴን ሁሌም የአማራውን ህዝብ እንደ ሰደበ፣ እንዳዋረደ፤ እንዳስገዛ ነው፡፡ የብአዴን ፍሬ የሆነው አለምነው የተባለው የእናት ጡት ነካሽም በድጋሚ ያረጋገጠልን ይንኑ ነው። አለምነዉ እነዚያን እጅግ አሳፋሪና ከፋፋይ ንግግሮች የተናገረዉ ፀረ አማራና ፀረ-ኢትየዮጵያ ጌቶቹን ያስደሰተ መስሎት ወይም የሥልጣን ቆይታውን ያመቻቸና በሥልጣን መሰላል ሽቅብ የተወነጨፈ መስሎት ሊሆን ይችላል፤
ሆኖም የአማራ ህዝብና ወገኑ የሆነዉ ሌላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ይህንን የአንድን ህዝብ ስብእናና ክብር የሚያጎድፍ ንግግር በምንም መልኩ ችላ ብሎ ሊያልፈዉ አይገባም፡፡
እንደሚታወቀው ዘረኛው ወያኔ የጸረ አማራነት አቋሙ እጅግ የከፋ ፣ ስር የሰደደ እና በድርጅት የታቀፈ ነዉ፤ እኛም በድርጅት ታቅፈን በድርጅት ካልገጠምነዉና ካልደመሰስነዉ በቀር የወያኔ ዘረኝነት መቆሚያና ማለቂያ የለዉም። ለምሳሌ ፋሽስቱ ወያኔ በቅርቡ በቤኒሻንጉልና በቤንች ማጅ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ዉስጥ አማራውን በማፈናቀል አማሮች ከአማራ ክልል ዉጭ መኖር አትችሉም ብሏል። የወያኔ ዘረኞች እነሱ በዘጠኙም ክልል እንዳሻቸዉ እየዞሩና ኃብት እያጋበሱ አማራዉን ግን እንደ ውጭ ዜጋ በማየት በገዛ አገሩ ውስጥ ከቦታ ወደ ቦታ እንዳይንቀሳቀስ በማድረግ አማራዉ ሳይወድ በግዱ የስደት ገፈት ቀማሽ እንዲሆን አድርገዉታል። ኧረ ለመሆኑ ይህ የግፍ ፅዋ ሂትለር በጀርመን በይሁዳዎች ላይ ከፈፀመው በምን ይለያል? እንደምናስታውሰው በሽግግሩ ወቅት ጠቅላይ ሚንስትር በነበረው ታምራት ላይኔና በወቅቱ ፕረዜዳንት በነበረው ሟቹ መለስ ዜናዊ በተፈራ ዋልዋ አቀናባሪነት በተሰጠ ትእዛዝ በወተር፤ አርባ ጉጉና በበደኖ ኦህዴድና ኦነግን በየፊናው አስማርተው የኋላ ድጋፍ እየሰጡ ውድ ወገኖቻችን ህይወታቸው ስታልፍ እንደ እንሰሳ ቆዳቸው መገፈፉ፤ ሳይሞቱ በገደል ሲጣሉና ሕጻን ሽማግሌ ሴት ወንድ ሳይለይ በጅምላ የማለቃቸውን ሃዘን ሳንረሳው ዛሬ ደግሞ ዳግም የጠብ አጫሪነቱን፡ በምን ታደርጉኛላችሁ እብሪት ተወጥሮ በባንዳው አለምነው መኮነን አስፈፃሚነት ለክልሉ ህዝብ ያለውን ከፍተኛ ንቀት ሬት ሬት በሚሉና አጥንትን የሚሰረስሩ ስድቦችን በመጠቀም አንካችሁ አሉ። አለምነው መኮነን የረጨውን መርዝ እስኪ አስቡት ወገን? ማንን ተማምኖ፡ የልብ ልብ ተሰምቶት ይመስላችኋል ይህ የመርገምት ልጅ ይህን ያህል ልሃጩን በጨዋው የአማራ ህዝብ ላይ የሚተፋበት? አረመኔውን የፋሽስት አገዛዝ አደለምን። ኧረ ግን አማራው እስከመቼ በዚህ የፋሽስት ስርአት እየተገደለ፡ እየተሰደደና እየተዋረደ መኖርን መረጠ? ኧረ ዝምታው ምንድነው? ግን እስከመቼስ ይሆን?
ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ!
ፋሽስቱ ወያኔ በአማራ ህዝብ ላይ በተከታታይ በማድረስ ላይ ያለዉ በደል፤ ግፍና ዉርደት የወያኔ ዘረኞች ሊነግሩን አንደሚፈልጉት የአማራዉ ጉዳይ ነዉ ተብሎ የሚታለፍ ጉዳይ አይደለም።ይህ ዛሬ በአማራዉ ላይ እየፈጸመው ያለው ዘርን የማዋረድና የማጥፋት ርካሽ ስራ ነገ በእያንዳንዳችን ላይ የሚደርስ መሆኑን ልንረዳ ይገባል። የወያኔ ወንጀል አሁን የተጠነሰሰ ሳይሆን ወያኔ ገና ደደቢት በረሃ ላይ ሲጠነሰስ አብሮት የተጠነሰሰ ሴራ ነዉ። ወያኔና ዘረኛ ስርአቱ እስካልተወገዱ ድረስ ይህ የተጀመረው አማራን የማዋረድ፡ የመጨፍጨፋ፣ የማፈናቀልና የማሳደድ ዘመቻ፣ ተጠናክሮ መቀጠሉ አይቀርም። ወያኔ አማራዉን ካዳከምኩ ሌላዉ አያቅተኝም በሚል ዘረኛ ስሌቱ ዛሬ አማራዉ ላይ አተኮረ እንጂ በወያኔ የተደበደ ፣ የታሰረ፣ የተሰደደ፤ የተፈናቀለ ፤ እንዲራብ የተደረገ፤ የተዋረደና የተገደለ ኢትዮጵያዊ ስፍር ቁጥር የለዉም። ዛሬ የአማራው ህዝብ ብቻ ሳይሆን ድፍን የኢትዮጵያ ህዝብ በወያኔ ጨካኝ ስርአት አማካኝነት በጨለማ ሂዎት ውስጥ እየማቀቀ ነው። ስለዚህ ችግሩ የአገርና የወገን የህልውና ጉዳይ እንጅ የፖለቲካ ጨዋታ ባለመሆኑ የወጣት፣ አዋቂ፣ ጎልማሳ፣ ሽማግሌ፣ ጾታ ሳይለየን ወያኔን ለማስወገድ በሚደረገው ትግል ምላሽ በመስጠት አለበት ባይ ነኝ። በአማራው ህዝብ ላይ የጠቆረውን ጨለማ በብርሃን መተኪያ ጊዜው አሁን ነው። ይህ ትውልድ የታሪክ ባለእዳ አይሁን። በወያኔ ዙሪያ ተሰብስባችሁ የሥርዓቱ ጠባቂና ተጠቃሚዎች የሆናችሁ በሙሉ ባሳለፋችሁት የግዛት ዘመናችሁ የአማራውን ዘር ብትሰድቡትም፡ ብትገድሉትም፡ ብታስሩትና ብታስርቡትም፤ ብታሰድዱትም፤ ሀብት ንብረቱን ብትዘርፉትም፤ በአገሩ በኢትዮጵያ የመኖር መብቱን ብትገፉትም ሕዝቡ መሃሪ ነውና ዛሬውኑ የሕዝቡን ትግል ብትደግፉና ብትቀላቀሉ ይሻላል። በተለይ አማራ ሆናችሁ ብአዴን የሚባል የፋሽስቱ ወያኔን የጥፋት ክንፍ ስታገለግሉ፡ እስከ ዛሬ በሆዳችሁ ስትገዙ የኖራችሁ እንደ አለምነው መኮንን አይነት የእፉኝት ልጆች ሕዝባችሁን የማዋረድና፤ የማድማት ተልኮዋችሁን አቁማችሁ፤ ወያኔ በወገኖቻችሁ ላይ እየፈጠረ ያለው ችግር ተሰምቷችሁ፤ ህዝባችሁን ይቅርታ ጠይቃችሁ፤ አሁኑኑ ለትግሉ ምላሽ በመስጠት መከታ በመሆን አዝሎ ያሳደጋችሁን ህብረተሰብ ከባርነት ቀንበር ታላቅቁት ዘንድ ወገናዊ ጥሪየን አቀርባለሁ። ለውሳኔው አለማርፈዳችሁን በዚሁ አጋጣሚ ላረጋግጥላችሁ ጭምር እወዳለሁ።
ድል ለጭቁኑ የኢትዮጵያ ህዝብ!
ለአስተያየትዎ፡ kiduszethiopia@gmail.com አድራሻየ ነው።

1 Comment

  1. I see some progresses.Some people including the geography professor Mesifn woldemarim were saying there is no Amhara identiy. But now there is a shift from that .The good thing is that the Amhara elites now realized that Amhara is one of the nationas and nationalities of Ethiopia. This is really a good lesson for them .In addition they will understand how painful is when one’s identity is attacked.They have to sense the feelings of the other people when their nation’s identity is attached. These Amhara elites expressly (not under the cover of Ethiopianism as they were doing before for so many years) now started raising their voices fighting “injustices” done against their ethnic group ,amhara people, and called all amharas including those working for the government to join this struggle for the right of Amhara people to be respected. This is their right .It is not racism or tribalism.They can demand the right of Amhara people to be protected and their identity right to be respected.This right of the people is recognized in international human right instruments and Ethiopian constitution.They can organize them selves on the basis of the their nation’s identity and express anger through different peaceful mechanism including calling all the Amhara’s to join them.
    Having said that they have the right to call the demonstration, that doesn’t mean that I agree with the substance of their specific request .As i understood the opinion of the vice president of Amhara region was Amharas are not superior to any nations and nationalities.He stressed on equality of the Ethiopian nations and nationalities.He recommended that the Amahars when living with other nations and nationalities that they should live in peace, harmony , love and respecting the identity and culture of other nations and nationalities. he also said there are some bad attitudes and chauvinistic tendencies among some amhara people undermining other nations and nationalities.He stressed these people being they themselves very poor and leading extremely destitute life ,undermine other hard working people leading better standard of life .by the way I am not undermining the Amhara people .I am personally connected to the Amhara people in one way or another .I have a great respect for the Amhara people.but we can’t deny some facts and realities.A beggar from Amhara ethnic groups ,when begging ,usually says’ a stranger and a guy from noble class is waiting outside ‘. do we deny this fact? do we really deny the existence of these back ward tendencies and attitudes among some amhara people as expressed by the vice president of Amhara regional state.Denying these facts by itself constitutes as accepting these chuvinistic backward tendencies of the Amhara superiority as a governing principle .Guys take your time ,cool down and think big !!please please be civilized and understand the century you are living in !!

Comments are closed.

Previous Story

የማለዳ ወግ …ሳውዲ ጉዳይ – ዛሬም ድጋፍ በምድረ አሜሪካ – ዋሽንግተን ዲሲ !

oslo
Next Story

የማፊያ ከበርቴዎች!!

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop