አዲስ አበባ ሌላዋ የዘመናችን የኢትዮጵያ ወልቃይት! – ፊልጶስ

የአዲስ አበባ ወጣቶች እየታደኑ እየታሰሩ ነው። የአድዋን 126 የድል ቀን   በሚኒሊክ አደባባይ መከበርና የብልጽግናን ሌብነት በአደባባይ መነገር፤  ለኢሳቷ  (ESAT) የዘመናችን ጣይቱ ብጡልና ለመሰሎቿ የሚዋጥላቸው አልሆነም።  የካራ ማር 44ኛ የድል ቀንም ጠ/ሚ  አብይ አህመድ ለወጉ ”እንኳን አደረሳችሁ”  ባይሉም፤   የድሉን ቀን ለማክበር የወጡ ኢትዮጵያዊያኖችና  የባልደራስ ለእውነትኛ ዲሞክራሲ አባላት ታፍሰው ወደ እስር ቤት ተወረወሩ።  አሁንም  ”ኢትዮጵያዊ   ነው”  ያሉትንና በኢትዮጵዮጵያ ሰንደ ዓላማ   አረንጓዲ፣  ቢጫ፣ ቀይ፤ የማይደረደርውን  ሁሉ በየቤቱ እያደኑ በማሰር ላይ ናቸው።  ታዲህ ይህ   በኑጹሃን ላይ የሚደረግ ግፍና በደል  ወልቃይትን ያስታውሰናል። ወልቃይት   የወያኔ  መቃብር እንደሆነች ሁሉ፤ አዲስ አበባም ለኦሮሙማ-ብልጽግና መቀበሪያ እንደምትሆን የጎሰኝነትንና የተረኝነትን የአገዛዝ አወዳደቅ ያስተምረናል።

ከዘመናት የወያኔ ግፍና ስቆቃ በኋላ ወልቃይት አሁንም አደጋው እንደተደቀነ ቢሆንም  “ነፃ “ ወጥታለች። ወልቃይት ለዚህ ለመብቃት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ታስረዋል፣   ተገለዋል፣  ተሳደዋል፣ አካለ ስንኩል ሆነዋል፣ በጅምላ ተቀብረዋል፣ በአጠቃላይ ወያኔ በኢትዮጵያ ላይ የፈፀመው ግፍ ሁሉ በደቦ ተፈፅሞባታል። ታዲያ ወልቃይት ከወያኔ ነፃ ስትወጣ ፣ አዲስ አበባም በተመሳሳይ ሁኔታ በተረኞቹ ኦሮሙማ-ብልጽግናዎች   በዜጎቿ ላይ   ግፍ እየተፈጸመ ነው።

እንደ ወልቃይት አዲስ አበባም ተመሳሳይ ታሪክና ትርክት እያስተናገደች ነው።

ልቃይት፤  ወያኔ ትግል እንደጀመረ 1966 እስከ 1967 ድረስ ወደ ሱዳን የሚያደርገው ማንኛውም ደርሶ መልስ ጀብሃ በሚቆጣጠረው በኤርትራ ክፍለ ሃገር አድርጎ ነበር። በ1967 መጀመሪያ አካባቢ ወያኔ ከ’ርዳታ ድርጅት የዘረፈውን ቁሳቁስና የጭነት መኪናዎች ይዘው ወደ ሱዳን ለመሻገር ሲሞክሩ ጀብሃ። “ከዘረፋችሁት ሃብት ግማሹን አካፍሉኝ” አለ። ወያኔ ስግብግብ ‘’ዘራፍ!’’ አለ። ብሎም አልቀረ፥፥ የዘረፈውን ሃብት ከነመኪናዎቹ አቃጠላቼው። እናም ተከዜን ተሻግሮ ወደ ወልቃይት ፊቱን አዞረ። ቀስበቀስም አካባቢውን ተቆጣጥሮ ከሱዳን ጋር ለሚያደርግ ግንኙነት ብሎም ወያኔ ለህልውናው የደም ስር ወልቃይት ሆነች።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አሁንሞ የሐገርን ኢኮኖሚ እየገደለ ያለው አዲሱ የብሄራዊ ባንክ ነው

አዲስ አበባ ወያኔ ”አዲስ አበባን የኔ የግሌ ነች” ለማለት ምክንያት ስላልነበረው ከተማዋን አራቁቶ በልቶ ተቃውሞው ሲያስፈራው በተለይም 1997 ምርጫ በኋላ  የትላንቱን ኦህዴድ፤ የዛሬውን ኦሮሙማ- ኦነጋዊ-ብልጽግና  ከናዝሪት አውጥቶ ”አዲስ አበባ ያንተ ነች” አለው። ወያኔ የአዲስ አበባን ህዝብ ለመበቀልና አንገት ለማስደፋት  ከሄደበት መንገድ አንዱ ይህ ነበር ። በ”ርግጥ ወያኔ የአዲስ አበባን ህዝብ በተዘዋዋሪም በዘረኞቹ  የመቆጣጠሪያ ስልት መቀየሱ ነው።

ልብ እናድርግ!…፡ ወያኔ ጀበሃ በ’ኔ ግዛት አታልፍም ሲለው የሄደው ወደ ወልቃይት ነበር። የአዲስ አበባ ህዝብ የወያኔን ጸረ ኢትዮጵያዊነት ቀደሞ የተረዳ በመሆኑ፤ የሱን ወንቶ- ፈንቶ  የጎሳ ፓለቲካ “— የነካ እንጨት” ሲያደርግበት ለኦህዴድ አዲስ አበባን በእጅ መንሻ ሰጠው። ወያኔ ፈንጅ ለመቅበሩ ‘ርግጠኛ ነበር፥፥ ለምን እና እንዴት? ብለው የማይጠይቁት የኦህዴዲ ጽንፈኞች ደግሞ እንደ ትልቅ ድል ቆጥረውታል።

ወልቃይት፤ ወያኔዎች የወልቃይትን ማንነት ለማጥፋት ከግድያ ጀምሮ የትግራይ ተወላጆችን በተለያየ መንገድ ‘’ዲሞግራፊውን’’ ቀየሩት።  ከተለያዩ አካባቢዎች ህዝብን በመሰብሰብና በማስፈር   በሱዳን የተሰደዱ ስደተኞችን ከመመለስ ጀምሮ፤ ከጦሩ የተሰናበቱትን በመቶ ሺ የሚቆጠሩ እና ከተለያዮ የትግራይ ወረዳዎችን ይጨምራል። ኢኮኖሚውንም ተቆጣጠሩት። ስራ እየተመረጠ ለወያኔና መሰሎቹ ብቻ ተሰጠ። ዜጋው ከአፓርታይድ በከፋ ከምድር በታች ያለ ኢ-ሰባአዊ ሁሉ ተፈፀመበት።

አዲስ አበባ፤ የትላንቱ ኦህዴዲ የዛሬው ኦሮሙማ – ብልፅግና ‘’አዲስ አበባ የኦሮሚያ ዋና ከተማ ብቻ አይደለችም፤ ኦሮሚያ ልዩ ጥቅም ማግኘት ይገባታል አለ::’’ አደረጋትም ፤ ዜጎች ልፍተውና ደክመው ያስገነቡትን ቤት በማን አለብኝ ለኦሮሙማ ተከታዩች አደሉት።

የአዲስ አበባ ህዝብ በልማት ስም ቤት ንብረቱ እየፈረስ እንደ አሮጌ ቁና የትም ተወረወረ ፤በምትኩ ተረኞቹ የኦነጋዊ- ብልጽግናዎች ከየቦታው እየተጠረሩ ሁሉንም ነገር ተቆጣጠሩት፥: አዲስ አበባ ዜጎች ተወልደው ባደጉበት ባይተዋር ሆኑ። ወጣቶቹ ተምረው ስራ ማግኘትና ኑሮ መመሰረት ህልም ስለሆነባቼው መሰደድና በባዕድ አገር፡ መከራተት እጣ ፈንታቼው ሆኖ፤ ብዙዎቹ በሳአውዲ እስር ቤት የምድርን ስቃይ ሁሉ ይከፍላሉ።

የአዲስ አበባ ህዝብ በግልጽ በኢትዮጵያዊ ማንነቱና ለዘመናት በገነባው ማህበራዊ እሴት ላይ ጦርነት ታወጀበት፥፥ በወልቃይት እንደተደረገው ሁሉ በአዲስ አበባም ከሱማሌ ክልል ተፈናቀሉ የተባሉት ከግማሽ ሚሊዮን ህዝብ በላይ አሰፈሩበት። ይህም አልበቃቼው፤ በአንድ ቤት ውስጥ እስክ 170 የሚደርስ መታወቂያ ከአዲስ አበባ ውጭ ለመጡ የእነሱ ተወልጆች በገፍ አደሉ ”ምርጫ”  አድርገን አሸነፍን አሉ።

ተጨማሪ ያንብቡ:   መታሰቢያነቱ በግፍ ለተገደሉ የዮኒቨርቲ ተማሪወች።

በወልቃይት ወያኔ እንዳደረገው ሁሉ ኦሮሙማ – ብልፅግና የከተማዋን ማንነት ለማጥፋት ከስም መቀየር ጀምሮ እስከ አዲስ ክፍለ ከተማ መፍጠር ድረስ ሄዱ። በከተመዋ የ”ነርሱን ቋንቋ የማይናገር የስራም ሆነ የኢኮኖም ተጠቃሚ መሆን እንዳይችል በመንግሥት ደረጃ መዋቅር ዝርግተው ይሰራሉ። የኦሮሚያ ፍርድ ቤት  በዋና ከተማ ላይ በማቋቋም በፍትህ ላይ ተሳለቁ።  ገዥዎቻችን በድግስና በግብዥ እየተምነሸነሹ፡ አዲሰ አበቤ ግን በችግር ” የበይ -ተመልካች’’ ሆኖ ይሰቃያል።

ወልቃይት፤ ወልቃይቶች በማንነታቸው ወያኔ ሲዘምትባቼው ጮሁ፣ ታሰሩ ፣ ተገደሉ ፣ ታገሉ ፣ በኢትዮጵያም ወያኔን የማስወገድ የትግል ፋና ወጊ ሆኑ ፣ ትግሉን አገር አቀፍ እንዲሆን ሰቆቃቼው በዓለም ዳርቻ እንዲሰማ ከፍ አድርገው ጮሁ ። ያ ትግላቼው ፍሬ አፍርቶ ዛሬ ለነፃነት በቁ።

አዲስ አበባ  አዲስ አበባሜ በማንነቱ ላይ በግልጽ ጦርነት እንደታወጀበት ሲያውቅ መታገል ጀመረ። በህዝቡ ያልተመረጠ ከንቲባ ሲሾምበት አጥብቆ ተቃወመ፥፤ ግን ወያኔዎች እንዳደረጉት ሁሉ የአዲስ አበባ ባለተረኞቹ  ኦሮሙማ – ብልጽግናዎች ሰላማዊ ታጋዮችን ከብዙ ማገላታት በኋላ ወደ ዘብጥያ አወረዷቸው።  ከአንደ አመት ተኩል  እስር በኋላ   የትኛውን  የጦር ዕዝ እንደመቱ ባናውቅም፤  የወያኔ አድራጊ-ፈጣሪና መሰሎቻቸው ሲፈቱ እነሱም ተፈቱ።

ለግዜውም ቢሆን አዲስ አበባን ታጋይ አልባ ያደረጓት መሰላቼው። ወያኔንም ወልቃይቶችን የቻለውን ያህል ገሎና አሳዶ ታጋይ አልባ ያደረጋት መስሎት ነበር። “ግን ታጋይ ይሞታል ፣ ትግል ግን አይሞትምና “ ወልቃይቶች ገና ብዙ ተጋድሎ ቢጠባቅቸውም  በነጻነት ለመኖር በቁ። የአዲስ አበባ የአሁኑ ትግል የህልውና ትግል ነው::  ለአዲስ አበባ ህልውና መከበርና ስለ ፍታዊነት በሰለጠነና በሰላማዊ የጠየቁ ዜጎችን በግፍ አስሮ ሰላም አይኖርም። የአሁኑ የግፍና የአፈሳ እስር ደግሞ ህዝብን ለመታገል የበለጠ ቆራጥ ያደርገዋል እንጅ አያንበረከከውም።

የአዲስ አበባ ህዝብ “መዲናችን የማንም ሳትሆን የሁላችን የኢትዮጵያዊያን ብሎም የአፍሪካ ነችና ‘ራስን በራስ የማስተዳደር የተፈጥሮ መብታችን አትከልክሉን ፤ ለዘመናት ከመላው ያአገሪቱ ክፍል በተውጣጡ ዜጎች የተገነባውን ማንንነት አትንኩብን! አክብሩልን! “ ፤ ከኢትዮጵያዊነይት ማማ አንወርድላችሁም!  በአረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ሰንደቅ ዓላማችን አንደራደርም ! አለ እንጂ፣ የራሱ ያልሆነውን አልጠየቀም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የተምቤን ስብሰባችን ጉድ አደረገን (አብርሃ ደስታ)

ለባለተረኛ ገዥዎቻችን የምናስተላልፈው መልእክት፤  በአሁኑ ግዜ አገራችን ከጦርነቱ ባልተናነሰ የኑሮ ውድነት እየተጠበሰው ነው።  ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ብሎ መከራና ችግሩን ሁሉ ችሎ አገሩን የሚያሰቀድመውን የአዲስ አበባ ህዝብ አትፈታተኑት። ትላንት ጎሰኝነትንና ጸረ-ኢትይጵያዊነትን እንደ ጡጦ አጥብቶ ካሳደጋችሁ ወያኔ ተማሩ።  ምንም ይሁን ምንም ኢትዮጵያዊነት ለሁላችን መደሃኒትና መዳኛችን መሆንኑ አሁንም ከወያኔ ስህተት ተማሩ ! ብለን እንመክራለን።  አዲስ አበባ ለሁላችንም ትበቃለች። አቅፋ ደግፋ ትይዘናለች።  የአዲስ አበባ  ህዝብ አብሮና ተከባብሮ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ መኖርን እንጅ፤ የአንድን ጎሳ የበላይነት የሚሸከምበት ጫንቃ የለውም። ለዚህም ነው ” አዲስ አበባ የኢትዮጵያዊነት ማሰሪያ ውል ናት!” የምንለው። ‘’አዲስ አበባን ማዳን ኢትዮጵያን ማዳን ነው! ’’ የምንለው:: ስለዚህም ህዝብ ለታላቋ ኢትዮጵያ ሲል ቅድሚያ የሚሰጠው  የአገርና የህዝብ አንድነት ስላለ እንጅ በእናንተን የመንደርተኝነትን አገዛዝና ፓለቲካ ሊቀበል ቀርቶ መፈጠራችሁንም ባያውቅ ይመርጥ ነበር።  መገንዘብ ያለባችሁ ህዝብ ከእንናተ ከገዥዎቻችን እጅጉን በበለጠ አገሩን ያስቀድማል። እናም  ነገ-ዛሬ ሳትሉ በህገ-ወጥ መንገድ ያሰራችኋቸውን ወግኖቻችን ፍቱ።   ጨቋኝ ጎሰኛም ሆነ የነጻነት ታጋይ ከወልቃይት ይማር።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኖራለች!!
———-//——-ፊልጶስ

የካቲት-2014

*ይኽ  ነጻ አስተያየት  ከዚህ በፊት የወጣ ቢሆንም፤  ከወቅቱ ጋር እንዲስማማ ማስተካከያ ተደርጎልተል።

 

3 Comments

  1. ብዙ የተበላሹ ነገሮች አሉ፡፤ በፊት በወያኔ አሁን ደግሞ በኦሮሙማው ቁንጮ አብይ አህመድ የሚዘወረው የኢትዮጵያ ጠላቶች አካሄድ አሁን ላይ አዲስና ለየት ያለ አቀራረብን ይዞ ብቅ ብሏል፡፤ የአሁኑ ስልታቸው ህዝባዊ ይዘት የነበራቸውን ሜድያወችና (ምሳሌ ዘሀበሻ) እንደዚሁም የህዝብ አንቂ የነበሩ (ምሳሌ ክንፉ አሰፋ) የመሳሰሉትን በአብይ አህመድ ወጥመድ አስገብቶ ሰፊውን ተከታዮቻቸው የነበሩትን ሁሉ እያወናበዱ ወደኦሮሙማ ደጋፊነት ለመሳብ ከፍተኛ ስራ እየሰሩ ነው፡፡ በተለይ ለዚህ የረቀቀ የእቡዩ የአብይ አህመድ ስታራቴጅ ዋናው ተዋናይ አማራ ጠሉና የፖለቲክ እርሾ አቡኪው ዶ/ር በርሀኑ ነጋ ነው፡፡
    ከዘረፋውና ከጭፍጨፋው በተጨማሪ የእነ አብይ አህመድ ኦሮሙማ ግብ ኢትዮጵያዊነትን አጥፍቶ አገሪቱን ኦሮማዊት ማድረግ ነው፡፤ ለዚህም ግቡ አብይ አሁን ላይ ሁለት ጣምራ ጦሮችን እየወረወረ ነው፡፤ አንዱ ያሰበውን ውጤት እንደምያመጣለት ቢረዳም ሰውየው ጨካኝ ስለሆነ ፋኖን ትጥቅ ማስፈታት በሚል ሴራ አማራን በአማራ ለማጨፋጨፍ ነው፡፡ሌላኛው ደግሞ አዲስ አበባን መሰልቀጥ ነው፡፡ አዲስ አበባን መዋጥ፣ የአድዋ ድልን ማደብዘዝ፣ የካራማራ ድልን አለመዘከር የኢትዮጵያ መሪ ነኝ (መሪ ነው አላልኩም) ከሚል ሰው የሚጠበቅ አልነበረም፡፤ የጅልና የቂል ስራ ነው የሰራው፡፡
    ክንፉ አሰፋ በዘሀበሻ ብቅ ብሎ ስይጠየቅ አዳነች አበቤ ህዝቡ መርጧታል ሲል ማረጋገጫ ሰጥቷል፡፡ዘር ከልጓም እንደሚስብ ሁሉ ሳንቲምም ለጊዜውም ቢሆን እውነትን ያስደፈጥጣል፡፤ ክንፉ ስለአድዋ ድል ሲያወሳ ተሳስቶ አንድ ጊዜ እንኳን ቢሆን የአጼ ምኒሊክን ስም አልጠቀሰም፡፡ የዘሀበሻ ሹክሹክታ ዘጋቢ ሄኖክ ደግሞ በገዱ አንዳርጋቸው ላይ በጊዜና በአውድ የማይገናኙ ንግግሮችን ለቃቅሞ ሰፍቶና ደራርቶ አቅርቦታል፡፤ ገዱ አንዳርጋቸው በኢህአደግ ዘመን በአማራ ህዝብ ትግል ላይ የሰራቸው ጥፋቶች ጠባሳው እንዳለ ቢሆንም አሁን በኦሮሙማ ዘመን ዘግይቶም ቢሆን አቋሙን አስተካክሎ ወደህዝባዊነቱ ተመልሷል፡፤ በተለይ በሁለት ጉዳዮች ላይ በጣም ወሳኝ አቋም ይዞ ማንነቱን በይፋ አስመስክሯል፡፡ ይህም ” ከዚህ እድሜዬ በኋላ” ብሎ ሁለቱንም አገርንና ህዝብን የሚጎዱ ድርጊቶችን አላደርርግም ብሎ ጠንካራ ኢትዮጵያዊነቱን አስመስክሮባቸዋል፡፤እምቢ ካለባቸው ክስተቶች ውስጥ አንዱ የህዳሴው ግድብ የዋሽንግተኑ በአሜሪካኖችና በግብጾች ተርቅቆ ለፊርማ የቀረበውን ስምምነት በልኡክ መሪነቱ “አልፈርምም” ማለቱ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ “ፋኖ ትጥቅ ይፍታ” የሚለው የአብይ አህመድን ሴራ ላይ አልስማማም!! እምቢ !!ብሎ አቋሙን በይፋ አሳውቆ እምቢ ማለቱ ነው፡፤ የሚገርመው በሁለቱም እምቢታወቹ ላይ ልጥቀስ”” ከዚህ እድሜዬ በኋላ” የሚል የማይቀለበስና የማይታጠፍ ቆፍጣና አቋሙን ገልጿል፡፡ ታዲያ ይህንን ሰው ነው ዘሀበሻ በሹክሹክታ ላይ የተንሿከከበት፡፡ ሲገርም?? እድሜ ለዶ/ር በርሀኑ ነጋ!!
    የአዲስ አበባ በኦሮሙማ የመሰለቅጥ ጉዳይ ወያኔ ወልቃይትን ውጦ እንደተፋበት ድራማው ባይከር ደስ ይል ነበር፡፤ ነገሩ ግን ተበለሻሽቷልና ከወልቃይቴዎች በላይ ትግሉ አዲስ አበቤዎችን ብዙ መስዋእትነት ሊጠይቃቸው ይችላል፡፡ በእርግጠኝነት የሚሆነው ግን ኦሮሙማ ከአዲስ አበቤ ዋጋውን አግኝቶና ተዋርዶ የዋጠውንና የሰለቀጠውን እንዲተፋ ይደረጋል፡፡

  2. ማስተዋል ቢኖር የለማ ከተማ ላይ መጥቶ ከመደረት ወይም ግንጥል ጌጥ ፣ከመሆን ኦሮሚያ ካለው ሰፊ ቦታ በተመረጠ ስፍራ የራሱን ከተማ ቢቆረቁር በየቤቱ ተመርቆ ቀጭ ያለው የተማረው ሀይል ሰፊ የስራ እድል ባገኘ ነበር። እባካችሁ ለራሳችሁም ስትሉ፣ ለሌላውም ሰላም ለመስጠት ፣የኦሮሚያን ዋና ከተማ ከአዲስ አበባ አውጡ።የኔ የኔ ማለቱ መጨረሻው ለሁሉም ጥፋት ነው።ከታሪክ ተማሩ፣ አለም አሁን ያለችበትን ሁኔታ ተረዱ!!

  3. The comment by Zega above assumes the claim on Addis Ababa is motivated by a search for wealth etc. It is mainly motivated by a motive do destroy Ethiopia as a state. Else, the wisest thing to do would have been exactly what was pointed out in your comment.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share