የሚኒሶታውን የደብረሠላም መድሃኔዓለምን ከይሁዳዎች መጠበቅ የሁላችን ኃላፊነትም ግዴታም ነው

ግርማ ብሩ (ከቤተክርስቲያኑ መሥራቾች መካከል አንዱ)

ሚኒሶታ ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ

ደብረሰላም መድሃኔዓለም ከተመሠረተ ጊዜ ጀምሮ በብዙ ውስብስብ ችግሮች ያለፈ ሲሆን ከዓመታት በፊት በማን ሥር መሆን አለበት ተብሎ 3 ምርጫ ቀርቦ ነበር። ይኸውም ሃገር ቤት በወያኔ ሥር በሚገኘው ሲኖዶስ፣ ኒውዮርክ በነበሩት አቡነ ይስሃቅ እና 3ኛው ገለልተኛ እንዲሆን ሲሆን በጊዜው በስብሰባው ቦታ በነበርነው አባላት በውጭ የሚገኘው ሲኖዶስም በደንብ ባለመጠናክሩ ገለልተኛ ሆኖ እንዲቆይ ተስማምተን ቤተክርስቲያኑ ለተወሰኑ ዓመታት ገለልተኛ ሆኖ ቆይቷል። ሆኖም ለቤተከርስቲያኑ ምስረታና ዕድገት በጊዜው ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረጉት አባ ፍቅረማርያም የአሁኑ (አቡነ ዳንኤል) ወደ ሃገር ቤት ተመልሰው ጳጳስ ከሆኑ በኋላ የደብረ ሠላም መድሃኔዓለም ገለልተኛ ሆኖ መቀጠል አጠያያቂ ሆኗል።

አቡነ ዳንኤልን ከመጀመሪያው ከአሪዞና ያገኋቸውና ያስመጣኋቸው እኔ ነበርኩ። ከልቤ እወዳቸዋለሁ። አከብራቸዋለሁም። ወደ ሃገር ቤት ሲመለሱና ሲሰናበቱም ያለምንም ቅሬታ ተሰናብቻቸዋለሁ። ወሳኔያቸውንም አክብሬያለሁ። ለምን ከዚህ በጊዜው ቤተክርስቲያኑን ለመመስረት ብዙ ስለተቸገሩ የአሜሪካ ኑሮም ከዕድሜያቸው አንጻር ከባድ ስለሆነ ምናልባት ሃገር ቤት የተሻለ ሊኖሩ ይችላሉ በሚል አልተቃወምኳቸውም።

ሆኖም ሃገር ቤት የጵጵስና ማዕረግ ካገኙ በኋላ መድሃኔዓለምን በአቡነ ጳውሎስ ሲኖዶስ ሥር ለማድረግ ብዙ ሙከራ አድርገዋል። ሚኒሶታ ድረስ በመምጣትም የቅስናና የድንቁና ሹመት ሰጥተዋል። በአቡነ ጳውሎስ ስምም ቀድሰዋል። አስቀድሰዋል።

እርግጥ በጊዜው የነበሩ የሥራ አስፈጻሚ አባላት አስቸኳይ ስብሰባ አድርገው ድርጊቱን እንዳወገዙና ለካህናቱ እንዳስጠነቀቋቸው አውቃለሁ።

ከዛ በኋላም ቢሆን ከመዘምራንም ይሁን ከአመራር አባላት መድሃኔዓለምን በአቡነ ጳውሎስ ሥር አድርገው ልዩ ጉርሻ ለማግኘት እላይና እታች የሚሉ አሉ። ይህ የሚያሳየን ለአባላት የሚሰጡትን ዝቅተኛ ክብር ነው። ይኸን ቤተክርስቲያን ለመመሥረት ምን ያህል ከወያኔና ከሻዕቢያ ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ እንደተናነቅን በየጊዜው የነበራችሁ ምዕመናን ምስክሮች ናችሁ። ታዲያ ይኽ ብዙ መስዋዕት የተከፈለበትን ቤተክርስቲያን ያለ ምእመናኑ ፈቃድ ለጥቅማቸው የሚሯሯጡ አይሁዳዎች ለወያኔ አሳልፈው ለመስጠት እንቅልፍ አጥተዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሰላም ዋጋው በእውነት ስንት ነው?  - ሙናች ከአባይ ማዶ ፊላው ስር  ገሳ ለብሶ እየቆዘመ 

ዛሬ ወያኔ እንኳን ራሱ የሚሾማቸውን ጳጳሳት ቀርቶ በየገዳማቱ እየገባ የራሱን ተወካይ ለማስቀመጥ መነኮሳትን በመደብደብና በማሰቃየት ላይ ይገኛል። የሚመረጠው ፓትሪያርክ የግድ ከትግራይ መሆን አለበት በሚል ግትር አቋሙ ሃገር ቤት የሚገኙትን ካህናት እንዳሰቃዩ ከህዝብ የተደበቀ አይደለም።

ታዲያ ይኸን ድርጊት እንኳን ለመንጋው የቆመ ካህን ይቅርና ማንም አማኝ ቢሆን ሊቀበለው የማይችል ድርጊት ነው። ዛሬ ከካህናትም ይሁን ከም እመናን ለጥቅማቸው የሚስገበገቡና ለሕዝቡ ርህራሄ የሌላቸው አውሬዎች አይጠፉም። በየቤተክርስቲያኑ ምእመናን እንዳይገናኙ በዕምነት እያሳበቡ አጥሮችን ይጋርዳሉ። ምእመናኑም እውነታውን ተገንዝቦና አንድ ሆኖ ሃገር ቤት ያለውን ሁኔታ እንዳያስተካክል አንዳንድ ወያኔ የሚነዛውን የውሸት ፕሮፓጋንዳ ተቀብለው ያራግባሉ።

ወያኔ ሕጋዊውን ፓትሪያርክ በህመም ምክንያት በገዛ ፈቃዳቸው ለቀዋል የሚለውን የፈጠራ ወሬ እውነት አለመሆኑን እያወቁ ምዕመናኑን ወደ ፈለጉት መንገድ ለማሽከርከር አንዳንድ ካህናት ይጠቀሙበት ነበር። ነገር ግን ያ ውሸት እንዳይቀጥል የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስተር የነበሩት አቶ ታምራት ላይኔ ግልጽ አድርገውታል።

አቡነ መርቆሪዎስ በህመም ሳይሆን ከሳቸው ምክንያት እንደወረዱ ከደብዳቤያቸው ተረድተናል። በየጊዜው ለፈጸሙት ስህተትም ይቅርታ ጠይቀዋል። አሁን በስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዚዳንት ግርማም አቡነ መርቆሪዎስ በታምራት ላይኔ ምክንያት እንደረዱና ወደ ስልጣናቸው እንዲመለሱ ተናግረው ነበር። ሆኖም የወያኔ አመራር አባላት ምኞት ባለመሆኑ የሚሾመው ሰው የግድ በትውልድ ትግሬ መሆን ስላለበት ይሄ ልሆን አልቻለም። ታዲያ ይኽንን ሁሉ አግባብ ያልሆኑ ምክንያቶች እያሉና ሁኔታው ሳይስተካከል ቤተክርስቲያንም ሆነ  ምዕመናኑን ወያኔ ባስቀመጠው ፓትርያርክ ስር ለማስገባት የሚደረገው ሩጫ እውነት ም እመናን ለመጥቀም ነው? ወይስ ለሰሩት ውለታ ለመሾም ለመሸለም? ይህን ችግር ለመፍታት ወሳኙ ምዕመናኑ ነው። አይመለከተኝም፤ አያገባም የሚለውን ሃሳብ ወደ ኋላ ትተን ገንዘባችንና ጉልበታችንን እንዲሁም ሰዓታችንን ያጠፋንበት ስለሆነ በአንድነት ተነስተን መብታችንን ማስከበር የእያንዳንዳችን ኃላፊነት ሲሆን በዚህ በተሳሳተ መንገድ የሚሄዱትም የማያዳግም  ትምህርት ያገኛሉ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የዐብይ አሕመድ ተውኔት፣ ገቢር አምስት - መስፍን አረጋ

እግዚአብሔር ቤተክርስቲያናችንን እና ሕዝባችንን ይጠብቅ።

ግርማ ብሩ

ከሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ መሥራቾች መካክል አንዱ

16 Comments

  1. አቶ ግርማ ብሩ ማን ቢስምሽ ታሞጠሙጫለሽ ነው እንጂ ብዙ እሎት ነበር።ነገር ግንከመድሃኒአለም ቤ/ክ አኩርፈው ሲወጡ ያኢግዚያብሔር ክብር ተደፈረ ብለው ሳይሆን ሰው ተነካ ብለው እንደሆነ የመርሳት ችግር ከሌለብዎ በቀር ላእርሶ ግልፅ ነው።በተረፈው ግን ላያገባት ግብታ ላያወዛት ተቀብታ እንዳይሆን እፈራለሁ።እባኮዎ መልካምነትዎን ባግባቡ ይጠቀሙበት። ብዙ ጥሩ ነገሮች እንዳልዎ እናቃለን።አኩራፊ እንጂ አሰታራቂና ታራቂ መሆን የሚችሉ አይመስለኝም። ቸር ይሰንብቱ

  2. My fellow brothers and sisters from Minnisota, please hear me out! Time and again members have been betraid by classical opportunist to hand over our church to the Woyanes. Look Aba Girma of St. Mary Church in London. You have to listen to Girma Biru and other concerned members. The danger is real
    and act up before it is too late. Bless You all!

  3. ይድረስ ለተከበሩ አቶ ግርማ

    የርስዎ ጉዳይ “ለማያውቁሽ ታጠኝ” ነው። ቤተክርስትያንን በተመለከተ እንኳን ባገር ደረጃ ካንድ አውራጃ ውጭ ማሰብ የማይችሉ በመሆንዎ ነው ከደብረሰላም አኩርፈው ከያሌ አመታት በፊት የተለዩት። ዘመኑ ማንም ብእር ጨባጭ እየቦጫጨረ የሚያናፋበት በመሆኑ መልእክትዎ ለሳቅ ለፈገግታ እንጂ ለቁም ነገር አይበቃም። ሆኖም ጀንበር ስትጨልም መንፈራገጥ አይቀርምና የህልምዎ ግብአ ከመሬት በቅርብ እስኪጠናቀቅ ስቃዩ እነዲቀልዎ መድሃኔአለም ይርዳዎ።

    • To my friend Tazabi, be direct to forward your Idea. If you are not comfortable with the idea someone gives, please comment only on the idea one by one and suggest your own with out throwing some thorny words. If you are a beliver in Medihanialem Kiristos and kidist Mariam , You have to use polite words to comment others.

  4. nano and all,

    It is not ato Girma’s personal behavior important here. It is the whole idea of the direction and the decision made by the church authority.What is at stake is the deceiving move made to be “neutral”. This move is surely a move made to clear the way to weyane camp but surely is lswlessness. It is not Orthodox Christians cannon. In this time and age all information is available to sort out the truth but the church’s authorities claiming to be neutral has a moral superiority is lough- able. It is pure ignorance or a wolf under a sheep skin. It is about time we Orthodox have to be united for our church is at a cross road. We need to come to light and accept the truth and the legal way that is to be under the holy synod in refugee.

  5. nano and all,

    It is not ato Girma’s personal behavior important here. It is the whole idea of the direction and the decision made by the church authority.What is at stake is the deceiving move made to be “neutral”. This move is surely a move made to clear the way to weyane camp but surely is lawlessness. It is not Orthodox Christians cannon. In this time and age all information is available to sort out the truth but the church’s authorities claiming to be neutral has a moral superiority is lough- able. It is pure ignorance or a wolf under a sheep skin. It is about time we Orthodox have to be united for our church is at a cross road. We need to come to light and accept the truth and the legal way that is to be under the holy synod in refugee.

    • አቶ ወይ ጉድ

      ሰንበትን እሁድ ነው ካላሉህ አይገባህም ወይ ? ቤተክርስትያን አትሰደድም፤ አንድነቷም የጸና መንበሯም በቅድስት አገር ኢትዮጵያ ነው። ደብረሰላም መድሃኔአለም በዚህ አቋሙ ጸንቶ የኖረ ወደፊትም ጸንቶ የሚኖር ነው። ይህ ሀቅ ለአንተም ሆነ ላቶ ግርማ እንዴት አዲስ እንደሆነባችሁ ለመረዳት ያስቸግራል።

  6. I Strongly agree with Meseret that our priests are selling us for alms, we must fight and stop them before they accomplish their Wayane given target. I strongly say this most current priests are “Hodames” who Live to eat not eat to live.

    Thanks

  7. ተሰደን ያሰደደንን አገዛዝ ለመቀበል መጣራችን በእውነቱ ትልቅ የሞራል ውድቀት፥ የመነፈስ ድክመት ነው። እረ ምን ነካን ወገኖቸ ? ለመሆኑ ስድተኞች ነን ወይስ ዲፕሎማቶች ? ስደተኞች ከሆን በማንና በምን ሁኔታ ነው በስደት ከምንወዳት እናት አገራችንና ከወገኖቻችን ተለይተን በባዕዳን አገር ለመኖር የተገደድነው ? ኢትዮጵያ ውስጥ ከወያኔ ቁጥጥር ነፃ የሆነ ተቋም እንደሌለ እያወቅን ፤ ታዲያ ለምንድነው በነፃነት እንድንኖር ያስጥጉን አገሮች የሠጡንን ነፃነት አሽቀንጥረን ጥለን፥ ነፃነታችን ገፎ ላሰደደን ሥርአት ለመገዛት ባርነትን የምንመርጠው ? ለቤተ ክርስቲያን ቀኖና ሳይሆን ለዘረኛው ወያኔ አገዛዝ መሳሪያ ሁኖ የሚያገለግለውን የካድሬዎች ስብስብ አዲስ አበባ ወስጥ ስላለ ብቻ ”ቅዱስ ሲኖዶስ” ብለን አመራሩን በስደት ሁነን እንድንቀበለው የሚያስገድድ የቀኖናም ሆነ የዶግማ ሥርአት እንዳለ የሚያስረዳን ሊቅ የት አገር ይኖር ይሆን? ገዳማት እየፈረሱ ፥ መናንያን መነኮሳት መካነ በአታቸውን እየለቀቁ ባለበት ሁኒታ ከአገዛዙ ጋር ቁሞ ጭሆታቸውን ጀሮ ዳባ ልበስ ያለውን ”ሲኖዶስ ነኝ” ባይ የመንግሥት አካል እኮ ነው አገዛዙን በስደት ሁነን እንቀበለው የሚሉን እነዚህ ስደተኛ ወገኖቻችን። አወ ያለራስ (ያለ ቅዱስ ሲኖኖስ የበላይ ጠባቂነት) የሚመሰረት ቤተ ክርስቲያን ግን ሊኖር እንደማይችል የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ያወግዛል። በወያኔ በግፍ የተሰደደ ሕጋዊ ፓትርያርክ የሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ ደግሞ ከእኛ ጋር አለ። ታድያ ለምን እኛ ስደተኞች አብሮን ከተሰደደነው ቅዱስ አባት ጋር አብሮ መኖር አቃተን ? ዲፕሎማቶች ሳንሆን ስደተኞች ሁነን ለምን የስደተኛውን ቅዱስ ሲኖዶስ አመራር መቀበል አቃተን ? አንቀበልም የሚሉት ሌላ ቀኖናዊም ሆነ ዶግማዊ መረጃ ማቅረብ የሚችሉ ሁነው ሳይሆን ከስደተኛ አባቶች የሚገኝ ሥጋዊ ጥቅም ስለማያገኙ መሆኑን ሁላችንም ልናውቀው ይገባል። ስለዚህ አቶ ግርማ የቆሙበት መሠረት ሊነቃነቅ የሚገባው እውነተኛ አቅዋም ስለሆነ አብረናቸው ልንቆም ይገባል። የካድሬዎችን ጫጫታ የምናዳምጥበት ጀሮ ሊኖረን አይገባም። አገዛዛቸው የድሀወችን ጭሆት የሚሰማበት ጀሮ የሌለው ጨካኝና ዘረኛ ስለሆነ !

  8. Our church is the home of every christian who realy strongly belives in Jusus Christ and His mother Kidist Mariam. I am the member of Minnesota Medihanialem Church. If we have some issues or concern we can discuss with respect and civility. This is America, where the right to express our idea is respected under the law and garanteed by the constitution.
    All the church members ( the general assembly) are the primary body who decide how the church should be ruled and managed, by selecting christians dedicated and loyal to Medahanilem Christos and Kidist Mariam and who respect the people who elect them. What I want to say is that the adminstrative activity shoud be run by the church members through their elected admistrative members.
    I also strongly belive that our Spiritual Fathers(the clergy) shoud get the proper respect and appreciation for their teaching and church sevrices. Without them our spiritual life is empty. However, I don’t belive that they shoud involve in the day to day adminstraive works of the church. Their main job should be to dissiminate the Gosple to human beings all over in the world. They have to preach peace and truth among the members of the church.

  9. Abba Fikre told us in church that your woman tried to poison him in your home. I am sure you remember that situation. Let me remind you Ato Girma, when we caught Abba Tesfa in pornography red-handed, you founded St. urael Church for him in Minnesota. You condemned us and left Debre Selam Medhane Alem to start another ‘Zeregna’ church with Abba Abba Tesfa as its head. Abba Zena Markos came from Seattle and tried to impress upon us that it is ok for monks to fornicate. Girma you remember what story that ‘Abun’ told us: “The ‘Abemnet’ covered his concubine with a ‘dibinyit ‘ until the searchers left and then he enjoyed her for the rest of the the night. I am sure you remember that story because you were there with us. Now you guys made Abba Tesfa a bishop residing in Color. and worship A. Zena as a saint. Medhane Alem is the church you did your utmost to destroy. Do you think we need your adevice? Girma, I know how badly you have failed, keep your dirty hands and monks from our church and stay with your own ‘Atbia’ and Abba Tesfa. Go figght for Waldiba!!!!! I assure you we will beat the devils at Medhane Alem without your dirty hands. Afrashu Siamata

  10. Yes, Medihanialem needs to let us know which side they are on. They just can’t ignore what is going on and run a church at the same time. If they don’t, we all are going to fight and close up the church. look what happened at the St. Mary Church. How come they don’t see that? Woyane is trying to control every thing. I stop going there long time ago and I’m not planing to go back unless they decided which side they are on. now is the time. Wake-up and open your eyes and ears.

  11. ምነው ዘሐበሻ ይህን ቆሻሻ ነገር በድረ ገጹ ላይ ያወጣል? ”Afrashu syamtata” የሚባለው የወያኔ ሰላይ የአባቶችን ስም የሚያረክስ አስተያየት ሲጽፍ ብዙ ሰው ከሚመለከተው ድረ-ግጽ ላይ ማውጣቱ ? አዬ ከዚህ ላይስ ተሳስታችኋል።

    • አቶ ከበደ

      እውነት መራራ በመሆኗ አልዋጥ ብላዎታለች አንጂ አቶ አፍራሹ ሲያምታታ ሀቁን በማያዳግም ቋንቋ አስቀምጦልዎታል።

  12. እነሆ ውድ ወንድሜ ቃኤል የገደለኝ ኣቤል ነኝ። ዛሬም ደሜ በወንድሜ እጅ ላይ አልደርቅ አለ፤ ምነው ቢሉ ዛሬም መስዋዐትን አልቀበል ያለውን እግዚኣብሔርን እንደመለመን በላቤ በወዜ ፍሬ ኣምላኬን የማከብርበትን መሰዊያዬን በቅናት ኣይናቸው የመለከቱብኝ ገባ። እንሆ በደላቸው በዛ ወዴት እንዳለሁም ቢጠየቁ ኣላየሁትም ያሉት የኔ የኣቤል ደም በእጃቸው አለ። እግዜአብሔር በደልን፤ ክፋትን፤ ተንኮልንና ምቀኝነትን ጠልቶኡልና። በፍረዱ በምደርም ሆነ በሰማይ ይሆናልና ጊዜው እስኪደርስ እጠብቃለሁ።
    ከሎንደን ደብረጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያን ኣባል
    የእናንተ ችግር በእኛም አለና በርቱ ለማለት ነው ወገኖቼ።
    የእግዚአብሔር ሰላም ከናንተ ጋር ይሁን።

Comments are closed.

Share