ከአዲስ አበባ ወደ ባህርዳር የሚወስደው መንገድ በመሬት መንሸራተት በመዘጋቱ የትራንስፖርት መስተጓጎል አጋጠመ

ከአዲስ አበባ ወደ ባህርዳር የሚወስደው መንገድ በመሬት መንሸራተት ዓባይ በረሃ በመባል በሚታወቀው አካባቢ ልዩ ስሙ ፍልቅልቅ በሚባለው ስፍራ ላይ በመዘጋቱ የትራንስፖርት መስተጓጎል ማጋጠሙን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ትላንት ሐሙስ ምሽት ሌሊቱን ባጋጠመ የድንጋይ መንሸራተት ናዳ የትራንስፖርት አገልግሎት መስተጓጓል እንዳጋጠመ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ነው ያስታወቀው።
234416044 4689765547721951 1742305381397716395 n
234416044 4689765547721951 1742305381397716395 n
ችግሩን በቶሎ ለመቅረፍም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በስፍራው አሰቸኳይ ጥገና የሚያደርግ ግብረ ሃይል በመላክ በስፍራው ከሚገኘው አሰቸኳይ ጥገና ቡድን ጋር በጋራ እየሰሩ እንደሆነ እና ስራው ተጠናቆ መንገዱ ክፍት ሲደረግ የሚያሳውቅ መሆኑን አስታውቋል።

EBC

 

232207810 4689742637724242 8592243141446612012 n

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከባህር ዳር አሁን የደረሰን ቪዲዮ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share