ከአዲስ አበባ ወደ ባህርዳር የሚወስደው መንገድ በመሬት መንሸራተት ዓባይ በረሃ በመባል በሚታወቀው አካባቢ ልዩ ስሙ ፍልቅልቅ በሚባለው ስፍራ ላይ በመዘጋቱ የትራንስፖርት መስተጓጎል ማጋጠሙን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ትላንት ሐሙስ ምሽት ሌሊቱን ባጋጠመ የድንጋይ መንሸራተት ናዳ የትራንስፖርት አገልግሎት መስተጓጓል እንዳጋጠመ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ነው ያስታወቀው።
ችግሩን በቶሎ ለመቅረፍም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በስፍራው አሰቸኳይ ጥገና የሚያደርግ ግብረ ሃይል በመላክ በስፍራው ከሚገኘው አሰቸኳይ ጥገና ቡድን ጋር በጋራ እየሰሩ እንደሆነ እና ስራው ተጠናቆ መንገዱ ክፍት ሲደረግ የሚያሳውቅ መሆኑን አስታውቋል።
EBC