አሸባሪው የሕወሓት ቡድን የትግራይ ሴቶች እና ሕጻናትን ያለምንም ወታደራዊ ስልጠና ለጦርነት እየማገደ መሆኑን በአፋር በኩል በመከላከያ ሠራዊት የተማረኩ የቡድኑ ታጣቂዎች ተናገሩ

 የሽብር ቡድኑ እድሜአቸው ለውትድርና አገልግሎት ያልደረሱ ሕጻናት እና ሴቶችን ከቀዬአቸው በተሳሳተ የሐሰት ፕሮፖጋንዳ በማስገደድ ለእንግልት እና ለጦርነት እየማገደ መሆኑን የተማረኩ የቡድኑ ታጣቂዎች ገልጸዋል።

231806577 1608361036005551 2437698464498981436 n

ያለምንም ወታደራዊ ስልጠና ወደ አፋር ክልል ሰርገው በመግባት በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥፋት ሊያደርሱ ሲሉ በመከላከያ ሠራዊት በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ተናግረዋል።

235433709 1608361159338872 2686330640098433697 n

ሽብርተኛ ቡድኑ አስገድዶ ላሰማራቸው ታጣቂዎቹ ስለ ኢትዮጵያ እና ስለ መከላከያ ሠራዊት የጥላቻ እና የተዛባ ትርክት እንደነገራቸው የገለፁት ምርኮኞቹ ስለሚዋጉበት ዓላማም ኾነ ሌላ ጉዳይ ጥያቄ ማንሳት የማይቻል መሆኑንም ጠቁመዋል።
መከላከያ ሠራዊት በመንግሥት ውሳኔ መሰረት ከትግራይ መውጣቱን ተከትሎ አሸባሪው ትህነግ ወደ ክልሉ በመግባት ሠራዊቱን እንደደመሰሰ በማስመሰል በተሳሳተ መንገድ ለቅስቀሳ መጠቀሙን ገልጸዋል።
231474038 1608361102672211 6726188371473732286 n
231474038 1608361102672211 6726188371473732286 n
ሽብርተኛው ሕወሓት በአሀኑ ወቅት አስገድዶ ላሰማራቸው ታጣቂዎች አንድ መሳሪያ ለስድስት ሰው እያስታጠቀ መሆኑን የተናገሩት ምርኮኞቹ ምንም አይነት የሎጅስቲክ ድጋፍ ማቅረብ የማይችል በመሆኑ ታጣቂዎቹ በርሃብና በእንግልት ምክንያት ምንም አይነት የመዋጋት አቅም እንደሌላቸው እንደገለጹ ከመከላከያ ሠራዊት የተገኘ መረጃ ያመላክታል።
አሚኮ
ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) አራተኛ ጉባዔውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀቀ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share