ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም  በተለያዩ ጊዜያት ስለሰጧቸው ሁለት የሚቃረኑ ቃለ መጠይቆች (እውነቱ)

mengesha syum
mengesha syum

1 ) ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም እኤአ መስከረም 7 ቀን 2017 ዓም  ወልቃይት በትግራይ ስር አልነበረም ሲሉ የሰጡት ቃለ መጠይቅ  

2 ) ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም እኤአ ታህሳስ 5 ቀን 2018ዓም  ወልቃይት በትግራይ ስር ነበረ ሲሉ የሰጡት ቃለ መጠይቅ

 

ማሳሰቢያ፦  

እነዚህን ሁለት የሚቃረኑ ቃለ መጠይቆችን አዳምጦና ለምን ብሎ መርምሮ መንስኤውን ማንም በቀላሉ ሊረዳ ይችላል፡፡

ቃለ መጠይቅ ቁጥር 1 

ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም እኤአ መስከረም 7 ቀን 2017 ዓም የሰጡት የመጀመሪያው ቃለ መጠይቅ

Online ምንጭ ፦ https://www.youtube.com/watch?v=N4jPUj_3FYI&t=1489s

በዚህ ቪኦኤ ባቀረበው ቃለ መጠይቅ ውስጥ  በ23ኛው ደቂቃ ላይ ራስ መንገሻ ስዩም “”እኔ ልጅ ሆኜ  ሳድግም ሆነ በኋላ ትግራይን  ሳስተዳድር ወልቃይት  በትግራይ ስር አልነበረም’’ ብለ  እኤአ መስከረም 7 ቀን 2017 ዓም  የሰጡት ቃለ መጠይቅ  ነው፡፡

ቃለ መጠይቅ ቁጥር 2 

ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም እኤአ ታህሳስ 5 ቀን 2018 ዓም የሰጡት ሁለተኛው ቃለ መጠይቅ

Online ምንጭ ፦ https://www.youtube.com/watch?v=Ueh8YnWvFF4

እኔ ልጅ ሆኜ  ሳድግም ሆነ በኋላ ትግራይን  ሳስተዳድር ወልቃይት  በትግራይ ስር አልነበረም ብለው  እኤአ መስከረም 7 ቀን 2017 ዓም  የሰጡትን ቃለ መጠይቅ  ከላይ በተራ ቁጥር አንድ ላይ መስማት ይቻላል፡፡

ወያኔ ቃላቸውን አጥፈው አዲስ ቃለ መጠይቅ እንዲሰጡ ባሳደረባቸው ተጽእኖ ይመስላል በነጻ ህሊናቸው በፊት የሰጡትን ቃል ሸምጥጠው ወልቃይት በትግራይ ስር ነበረ ያሉበትን ይህንን  የ2018ቱን ቃለ መጠይቅ ሰጡ፡፡ ይህ የ4 ደቂቃ አጭር የቃለ መጠይቅ ዘገባ በድምጸ ወያኔ ቴሌቪዥን ጋር ካድረጉት ቆይታ ተቀነባብሮ የቀረበ መሆኑን  ከቪድዮው ማወቅ ይቻላል፡፡

 

ማስታወሻ፦ ሁለቱም ቪድዮወች  በእጃችን ይገኛሉ ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ቅጥረኛ የአብይ አህመድ ጄነራሎች ለሚያፈሱት የአማራና የሌሎች ኢትዮጵያውያን ደም የክፍያቸው መጠን ጨምሯል፣ - አንዳርጋቸው ጽጌ

1 Comment

  1. እውነቱ ሆይ፦
    ይህ መረጃ በእውነትም በእጅህ ካለ የሚሊዮን ዶላር መረጃ ስለሆነ በጥንቃቄ መያዝ አለበት፡፡ ወያኔወች በደም ስካር ተውጠው ከኢትዮጵያ ለ27 አመታት የዘረፉትን ቢሊዮኖች ዶላሮች እየረጩ የመጨረሻቸውን መፈራገጥ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ስለሆነም ይህንንም ቪድዮ እንደምንም ብለው ሊያስጠፉት ይችላሉና ጥንቃቄ ይደረግ፡፤
    የምእራቡ አለም ኢትዮጵያን ለመጉዳት ከድሀው የኢትዮጵያ ህዝብ ተዘርፎ በሚከፈላቸው አያሌ ገንዘብ ጭምር የወያኔ ጭፍራወችን ለማዳን የማያደርጉት ነገር የለም፡፤ (ለምን ኢትዮጵያን ለመጉዳት የሚለው ምክንያታቸው ብዙ ስለሆነ ለአሁኑ አናነሳውም ) ፡፡ ወያኔወች በዚሁ ሳምንት ውስጥ ሂሳብ እንናወራርዳለን ብለው ለከፈቱት ጦርነት (በእኛ በኩል ሻጥር ወይንም ታክቲክ ወይንም ስህተት በሉት ) አላማጣ፣ ኮረምና ማይጸብሪ ተለቆላቸው ሲገቡ ጥጋባቸው ሰማይን በወንጭፍ እንደመቱ ያህል ምድር አልበቃቸው ብሎ ታይተዋል፡፡ ወዲያዉኑ ነገሮች እርምት ተደርጎባቸው ልዩ ሀይሉና መከላከያው ማጥቃት ጀምሮ ከተሞቹን ሲቆጣጠር ለቅሷቸውን ጀመሩት፡፡ ቀጥሎም ወደሱዳን የመውጭያና የመግቢያ በሩ ወልቃይት ለወያኔ የሞት ሽረት ጉዳይ ስለሆነ ይህ ህልማቸው ሲጨልምባቸው “ወልቃይት እኮ በታሪክ የትግራይ ነበር” የሚለውን ተስፋቢስ ተረት ተረት እንደገና አንስተው ማላዘን ጀመሩ፡፡
    እኔም ለሁለት ቀናት July 15 & 16 የተመለከትኩት ቢቢሲ በየሙሉ ሰአታቱ በሚያቀርበው ዜና ላይ ስለትግራይ ሰፋፊ የፕሮፓጋንዳ ስራወችን ሲዘግብ መዋሉ እጅግ አስተዛዛቢ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ (ለብዙ አመታት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባስደር የነበሩት ሚስተር ቲቦር ናሽ ግን የምእራቡ ዓለም ሁሉንም አድርጎና ሁሉንም ነገር ሆኖ ቢሞክርም ወሳኙና ለነገሩ መፍትሄ የሚሆነው በኢትዮጵያ ህዝብ በኩል የሚደረገው ነው በሚል የተናገሩት መድምደሚያ እውነተኛነቱ አርክቶኛል)
    በዚህ ስሌት ወያኔ ታሞ ሀክም ቤት የገባ በሽተኛን ብንመስለው በምእራቡ አለምና በወያኔ መሀከል ግንኙነቱ የምንም ይሁን የምን ያለው ቁርኝት ግን በሽተኛው ወያኔ ተሰክቶለት የሚተነፍሰውን አየር የመንቀል ወይንም ያለመንቀል ያህል ወሳኝነት ያለው መሆኑንና መጨረሻ ላይም ወያኔን ያለጥርጥር ሊያድነው እንደማይችል መገመት ይቻላል፡፡ ወያኔ ተንፈራግጦ ወይንም ሳይንፈራገጥ እንዲሁ ይሞታታል እንጅ ተመልሶ ሀይል ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥም ሆነ በትግራይ ክልል ውስጥ እርባና ያለው ነገር ለማድረግ በማይችልበት ቁመና ላይ ይገኛል፡፡ ለዚህ እውነታ ላይ ለመገኘቱም ለቀሪ የወያኔ ርዝራዦች ቀነኒሳ እንዳለው “አይዞሽ ገለቴ”….. “ምን ታደርጊዋለሽ” የሚለውን አባባል ፈገግ እያሉ ይጽናኑ ዘንድ ጋብዘናቸዋል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share