July 3, 2021
2 mins read

ሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በሶስት አገራት ላይ የጉዞ እገዳ ጣለች

ዴልታ የተሰኘው አዲሱ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ በ85 አገራት ተሰራጭቷል
244 185806

ሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በሶስት አገራት ተጓዦች ላይ የጉዞ እገዳ ጣለች።

244 185806ሳውዲ አዳዲስ የኮሮና ቫይረስ ዝርያዎች መብዛታቸውን ተከትሎ ከኢትዮጵያ ቬትናም እና ከተባበሩት አረብ ኢምሬት የሚነሱ መንገደኞች ወደ አገሯ እንዳይገቡ መወሰኗን ገልጻለች።

አገሪቱ ከዚህ በተጨማሪም ዜጎቿ ወደ ሶስቱ አገራት እንዳይበሩም የከለከለች ሲሆን እገዳው ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በሚል መተላለፉ ተገልጿል።

የበረራ እገዳው ከነገ ጀምሮ የሚተገበር ሲሆን የሳውዲ ዜግነት ያላቸው ዜጎች እገዳው ከተላለፈባቸው አገራት የሚመጡ መንገደኞች ግን ለ14 ቀን በለይቶ ማቆያ ከቆዩ በኋላ እና ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው ከተረጋገጠ በኋላ ወደ መኖሪያ ቤታቸው መግባት ይችላሉ ተብሏል።

ለመጀመሪያ ጊዜ ዴልታ የተሰኘው የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ከታየ በኋላ አሁን ላይ በ85 አገራት መሰራጨቱን የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያስረዳል።

በተያያዘ ዜና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች (ዩኤኢ) ከአዳዲስ የኮሮና ቫይረስ ዝርያዎች ጋር በተያያዘ ዜጎቿ ወደ 14 የአፍሪካ ሃገራት እና የደቡብ እስያ ሃገራት እንዳይጓዙ ከልክላለች፡፡

ዩኤኢ ዜጎቿ ወደ ሃገራቱ መጓዝ ብቻም ሳይሆን ከሃገራቱ እንዳይገቡም ነው የከለከለችው፡፡

በእገዳው ከታካተቱ ሃገራት ስምንቱ አፍሪካዊ ናቸው፡፡

ደቡብ አፍሪካ፣ ናሚቢያ፣ ኡጋንዳ፣ ዲ.አር ኮንጎ፣ዛምቢያ፣ ሴራሊዮን፣ ላይቤሪያ እና ናይጄሪያ ይገኙበታል፡፡

ህንድ፣ ፓኪስታን፣ ባንግላዴሽ፣ ኔፓል፣ ስሪ ላንካ እና ቬትናም ደግሞ እገዳው ከተጣለባቸው የደቡብ እስያ ሃገራት ናቸው፡፡

እገዳው በህንድ፣ ፓኪስታን፣ ባንግላዴሽ እና ስሪ ላንካ እንደ ጎርጎሮሳውያኑ ሃምሌ 21 ድረስ እንደሚቆይ ዘ ናሽናል ዘግቧል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Security Council meeting 2
Previous Story

ከብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት በወቅታዊ ሀገራዊና ቀጠናዊ፣ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ የተሰጠ መግለጫ

Next Story

በተመድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ከም/ቤቱ ስለትግራይ በተነሱ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop