የቀድሞው የደርግ ወታደርና በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ የኢሕአዴግ ደጋፊነቱ የሚታወቀው አርቲስትና የማስታወቂያ ሠራተኛ ሠራዊት ፍቅሬ አንዲትን ሴት የቲቪ ማስታወቂያ አሠራሻለሁ በሚል ለመሳሳምና ለማሻሸት ሞክሯል በሚል በአስገድዶ መድፈር ሙከራ ክስ እንደቀረበበት አዲስ አድማስ ጋዜጣ ከአዲስ አበባ ሲዘግብ፤ አርቲስቱ ይህን ጉዳይ እንደማያውቅ ማስተባበሉንም ጋዜጣው ጨምሮ ዘገቧል።
በበማስታወቂያና በፊልም ስራ የሚታወቀው አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬ፤ በመድፈር ሙከራ አቤቱታ እንደቀረበበት መወራቱን በተመለከተ ተጠይቆ “በሬ ወለደ ወሬ ነው” ሲል ማስተባበሉን የዘገበው አዲስ አድማስ ጋዜጣ የሠራዊት መልቲ ሚዲያ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ ሠራዊት ፍቅሬ ላይ አንዲት የዩኒቨርስቲ ተማሪ ለፖሊስ አቤቱታ ማቅረቧን የሚናገሩ ምንጮች፣ ባለፈው ቅዳሜ “ለማስታወቂያ ስራ እፈልግሻለሁ” ብሎ ፒያሳ አካባቢ በሚገኝ ሆቴል ውስጥ ለመሳምና ለማሻሸት ሲሞክር አመለጥኩ” የሚል ነው ብሏል ጋዜጣው በዘገባው።
የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ምንጮቹ እንደሚሉት፤ የአቤቱታው ሂደት ተቋርጦ፣ ጉዳዩን በሽምግልና እንዲያልቅ መደረጉን ይናገራሉ፡፡ ከፖሊስ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ሳይሳካ የቀረ ሲሆን፤ ሠራዊት በበኩሉ “ወሬው የበሬ ወለደ አሉባልታ ነው፤ ምንም የማውቀው ነገር የለም” ብሏል፡፡ “ካሁን በፊት ከወገቤ በላይ ብዙ ተብያለሁ፤ አሁን ደግሞ ከወገቤ በታች መጡ” በማለት ቀልድ አዘል አስተያየቱን ሠጥቷል ሲል ጋዜጣው ዘገባውን አጠናቋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ በርከት ያሉ የማስታወቂያ ሠራተኞች እና ፊልም እና ድራማ የሚያሰሩ አርቲስቶች ለትወና የሚመርጧቸውን ሴቶች ቅድሚያ ወሲብን እንጅ መንሻ እንደሚጠይቁ፤ ይህን የማያሟሉ ሴቶች ግን ብቃቱ እያላቸውም ቢሆን ለፕሮጀክቱ ብቁ እንደማይሆኑ በተደጋጋሚ መነገሩ አይዘነጋም።
የእንግዳ ልኡክ ጽሁፎችን የአርትዖት አምዶችን ወይም አስተያየቶችን እና ትንታኔዎች መጣጥፎችን እንቀበላለን:: ሀሳበወትን እና እውቀትዎን ለአንባቢዎቻችን እንዲያካፍሉ እንጋብዛችኋለን። ጽሑፋችሁ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አንባቢዎችን ይደርሳል፣ ያለቀ ጽሁፍ በ admin@zehabesha.com በኩል ያቅርቡ! የሚሰነዘሩ አስተያየቶች ደራሲውን ብቻ የሚያንፀባርቁ እንጂ የዘ-ሐበሻ ዶት ኮም ኦፊሴላዊ ፖሊሲ ወይም አቋም የሚያንፀባርቁ አይሆኑም!!
4 Comments
Comments are closed.
Wey ye derg wetader kkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkkk
who crowned this buffon banda as an artist? it is an effront for genuine artists to be lumped with such gourme who sold out his conscience for a dime . please Mr editor dont ever call such crumb pickers “artist”. he is more of a mercenery CADRE of the woyane.No more and no less.
dear editor
sorry . this girl need only publicity…just publicity
A new method of earning money under the cover of law