የነዳንኤል ክብረትና የኔ – ሁለት አቢይ አህመዶች! – ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

የጠ/ሚ ዶ/ር አቢይ ምስል በኔ አእምሮ ውስጥና በፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንዲሁም በሙሃዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት አእምሮ ውስጥ የሰማይና ምድርን ያህል ልዩነት ማሳየቱ ትልቅ ምሥጢር ሆኖብኛል፡፡

ዶ/ር አቢይ በመጀመሪያ አካባቢ የኢትዮጵያ ሙሤ ሆኖ ይታየኝ ነበር – ይህን አልክድም፡፡ እየቆዬ ግን ተገለበጠና ለኢትዮጵያ ጥፋት ከአጋንንቱ ዓለም የተላከ ያህል ይሰማኝ ጀመር –  ይህም እውነት ነው፡፡ አሁን ዓለምን እያተረማመሷት የሚገኙት የኮረና ቫይረስ አምራች የኢሉሚናቲ ኩባንያዎች ኢትዮጵያን በቁጥጥራቸው ሥር ለማስገባት በቅድሚያ መለስ ዜናዊን ተጠቀሙ፡፡ ሲበቃቸው እርሱን አስወገዱትና ይህን ብላቴና አራት ኪሎ አስገብተው በአዲስ ጉልበት ሀገራችንን ማውደም ተያያዙ፡፡ “አውቆ የተደበቀ ቢጠሩት አይሰማም” እንዲሉ ሆኖ ለነዳንኤልና ብርሃኑ ቢሠወርባቸውም ለብዙዎቻችን ግን ይህ ገሃድ እውነት በጣም ግልጽ ነው፡፡

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በወዲያኛው ሰሞን “የአቢይን ያህል ኢትዮጵያን አልወድም” ዓላማው ግልጽ ባልሆነ ሁኔታ ሲያሞካሸውና በዚህኛው ሰሞን ደግሞ ሙ.ጥ ዳንኤል ትናንትና ማታ በደረጀ ኃይሌ ፕሮግራም እንግዳ ሆኖ ዕንባ እስኪያቀር ድረስ ያንኑ የፕሮፌሰር ብርሃኑን ቃል – ከሞላ ጎደል ቃል በቃል መድገሙን ስታዘብ እነሱ የተረዱትን አቢይ እኔ በነሱ የአረዳድ አቅጣጫና መጠን ባለመረዳቴ ራሴን ታዘብኩት፡፡ ችግሩ የኔ እንደሆነ እስክጠራጠር ድረስ ተጨነቅሁ፡፡ “ይህ ናርሲሲስት ፀረ-አማራ ጠ/ሚኒስትር እኔ ያላየሁለትና እነሱ ተረድተውለት ከነሱም በላይ በኢትዮጵያዊነቱ እንዲገዝፍ ያስደረጋቸው ተዓምር ምን ይሆን?” ብዬም ብዙ አሰብኩ፡፡ ደጋግሜ በሃሳብ ብወጣ ብወርድም አልከሰትልህ አለኝ፤ የገባችሁ እንድታስረዱኝ እለምናችኋለሁ፡፡

ብዙ ነገሮች አንጻራዊ መሆናቸው ይገባኛል፡፡ ሺህ ጊዜ አንጻራዊ ይሁኑ እንጂ ግና ትግራይ ከነወንጀለኞቿ ልክ እንደ አንድ ነፃ ሀገር እንደልቧ እንድትፈነጭ ያደረገ፣ አማራ ግን ሁለት ሽህ ሚሊሺያ እንኳን ሲያሰለጥን ዐይኑ ደም የሚለብስና በሌላ በኩል ደግሞ ኦሮሞ በያንዳንዱ ዙር በአሥር ሽዎች የሚቆጠር ዘመናዊ ጦር ለ30 እና 40 ጊዜ እያሰለጠነ ማስመረቁን ለማስፈራሪያነት ጭምር በሚዲያ ሲያስታውቅ በደስታ ተውጦ ዝም ያለ፣ ንጹሓን የአማራ ተማሪዎች ከአራት ወራት ለበለጠ ጊዜ በአክራሪ ኦሮሞ ሽፍቶች ታግተው ሳለ “ራሳቸውን በራሳቸው ያገቱ ሰዎችን ፈልጎ ማግኘት አይቻልም” ብሎ በዜጎች ያላገጠ፣ የአማራን ምርጥ ምርጥ አመራሮች በልዩ ሥልት ገድሎ ወይም አስገድሎ የአንድን ትልቅ ክልል አመራር በራሱ ሰዎች የተካና አማራን ለማጥፋት ቆርጦ የተነሣ፣ ጃዋራዊ ቄሮን አጠገቡ አስቀምጦ ሀገርን በቋንቋና በጎጥ እየበለተ ሳለ ጎንደር ውስጥ አደብ ገዝቶ የተቀመጠን ፋኖ ሊያውም ኮሮና ቫይረስ ዓለምን የስንግ ይዞ በሚያስጨንቅበት በአሁኑ ሰዓት ካላጠፋሁ ብሎ የፌዴራል ጦር ያዘመተ፣ የፌዴሬል መንግሥት ተብዬውን መሥሪያ ቤቶች ከሞላ ጎደል ሁሉንም የኃላፊነትና ጥቅማ-ጥቅም ቦታዎች በኦሮሞ ነገድ አባላት ካለ(በቂ) ችሎታና ካለውድድር ያቃረጠና እያቃረጠ ያለ እስስትና ይሉኝታቢስ ጠ/ሚኒስትር በዚህ መልክ አጋንኖ መግለጽ መልስ የሌለው ክፍለ-ዘመናዊ ዕንቆቅልሽ ነው፡፡ ሀገር ላይ የደረሰውና እየደረሰ ያለው የዚህ ሰው በደል ተዘርዝሮ እንደማያልቅ አስምሬበት ማለፍ እወዳለሁ – አንዳንድ ትያትራዊ ተግባራቱ ከሚፈጽማቸው መሠረታዊ እንከኖቹ ጋር ሲወዳደሩ ቅቡልነትን ለማግኘትና ሤራውን አጠናክሮ ለመቀጠል ከመርዳት ባለፈ ሚዛን የሚደፉ አይደሉም፡፡ ለምሣሌ እስረኛን ማስፈታትም ሆነ መፍታት ዓላማው ለታይታና ለፕሮፓጋንዳ አለፍ ሲልም ለሌላ እስረኛ ቦታ ማስለቀቅ እስከሆነ ድረስ በደስታ እምቢልታን የሚያስነፋ አይደለም፡፡ ለማንኛውም…. ይህን ሁሉ ወንጀል የሚሠራ ግለሰብ ማፍቀርና በዕንባ እየተራጩ “ዘላለማዊ ክብርና ሞገስ ለጠ/ሚኒስትራችን!” ማለት አልገባህ ብሎኛልና የገባችሁ አስረዱኝ፡፡ ይህ ሁሉና ከዚህም የከፋ ወንጀል በፌዴራል መንግሥት ተብዬው እየተፈጸመ ሳለ የፕሮፌሰር ብርሃኑ ሚዲያዎች በስማም እንደተባለበት ሰይጣን ጭጭ ብለዋል፡፡ ምሣሌ ካስፈለገ ኢካድፎረም የተባለው ድረገጽ የቆመበትን ቀንና ሰዓት ማየት በቂ ነው፡፡ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን የማይገቡን ወቅት ላይ ደርሰናል፡፡ ይህን ዕንቆቅልሽ የሆድ ነገር እንዳልለው እነዚህን ሰዎች በሆድ ማማት ይቸግረኛል፡፡ የሥልጣን ነገር እንዳልለውም በተለይ ዳንኤል ከንግግሩ እንደተረዳሁት ለሥልጣንና ለገንዘብ ጥዩፍ መሆኑን ከራሱ አንደበት ሰምቻለሁ፡፡ ምናልባት አንዴ ስለወደዱት የዚህን ሰውዬ ዕድፍና ጉድፍ ላለማየት በካፈርኩ አይመልሰኝ ተጠርንፈው እንደሆነ ሰጋሁ፡፡ ይህም በሽታ ነው፡፡ እንጂ ብርሃኑ አቢይን ስለወደደና ዳንኤልም ስላመለከው ችግራችን እንደጪስ በንኖ ይጠፋል ማለት እንዳልሆነ እነሱና እኛ ብቻም ሳንሆን ታዛቢም ሳይቀር በተግባር እያየን ነው፡፡ የእውነት አምላክ ግን ፍርዱን ይስጥ፡፡ በውነቱ ይህ ዘመን ብዙ ጉድ እያሳየን ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሰማያዊ ፓርቲ ጥሪ ከወዲሁ ያስመዘገባቸው ድሎች - ግርማ ካሳ

Infatuation እና/ወይም calf love (calf’s love) የሚባሉ የእንግሊዝኛ ፈሊጦች አሉ – እነዚህን አባባሎች ሳልጠቅስ ጅምሬን መቋጨት አልፈልግም፡፡ በኛም በአንድ ፈሊጣዊ አገላለጽ “የወረት ፍቅር” ልንላቸው እንችላለን፡፡ ልክፍት እንጂ ምክንያታዊነት የላቸውም፡፡ አንድ ሰው በቂ ምክንያት ሳይኖረው ወይም እንዲኖረውም ሳይፈልግ እንዲሁ አንድን ሰው የሚያፈቅርበት ወይም የሚወድበት ሁኔታ ከተፈጠረ በዚህ ፈሊጥ ይገልጻል፡፡ በዚህ መልክ ያፈቀርከውን ሰው ወደኅሊናህ ስትመለስና ፍቅርህን ስታጤነው ልክ እንዳልነበርክ ይከሰትልህና ልታፍር ትችላለህ፡፡ … ለማንኛውም የአቢይን ጠንካራ ጎን እኔም እንደነሱው ባወቅሁና ተፀፅቼ ንስሃ በገባሁ፡፡ እነዚህ ሰዎች በዚህ ሰው የተመሰጡበትንና አደባባይ የተሰጣውን የሰውዬውን ገመና አስረስቶ ከኢትዮጵያዊነት አንጻር እንደዚህ ከራሳቸው አሳልፈው ሰማየ ሰማያት የሰቀሉበትን አመክንዮ ባውቅ ደስ ባለኝ፡፡ አሁንም ልድገመው – የገባው ካለ ቢነግረኝ ምሥጋናየ ወደር አይገኝለትም፡፡

የኢትዮጵያ አምላክ ከሰው ሠራሹ የኮሮና ቫይረስ ይጠብቀን፤ከምሥኪኑ የዓለማችን ሕዝብ ራስ ወርዶ በሠሪዎቹ በራሳቸው ላይ ንግሥናውን ያሳይ፡፡ ጦርነቱ በራሳቸው ሜዳ ይለቅ፤ አሜን ነው! አሜን፡፡

19 Comments

  1. Fact is always fact. You can’t hide it for whatever purpose you have in mind. As to me, this writer has expressed undeniable realities about the controversial PM of Ethiopia. Though this time around is a time of frustration and hibernation thereof due to nCOVID19, the points mentioned about the PM are seriously discussable.Our problems as a nation are currently mindboggling the solutions of seem to be beyond the horizons unless God Himself intervenes. God forbid, it is gonna be Doomsday for Ethiopia, for example, if this virus begins its toll in a manner of magnitude it is busy now in so called first world countries such as Italy, Spain, and elsrwhere which are believed to have every earthen weaponry to fight it. … Anyhow, WE HAVE TO PRAY HARD and respect the lessons as well as warnings of medical personnel.

  2. በህይወት ዘመኔ እንደ አብይ አህመድ ቂመኛ፣ ተንኮለኛ ስልጣን ወዳጅ አስመሣይ ሰዉ አይቼ አላቅም፤ እኔም እሱን የሚደግፉት በሆዳዉ የተገዙ እንደሆኑ ባቅም ሰዉየዉ ግን የሚያደርገዉ ነገር ያቅለሸልሻል ባይበላ ቢቀርስ ያስብላል፤ በተለይ አማራዉን ማጥፋት ይፈልጋል፤ አስኪ እንደዉ በምን ሞራሉ ነዉ መቀሌ የተወሸቀን ወንበዴ ሳይዝ አማራ ላይ ጦር የሚያዘምተዉ፤ ብቻ ፈጣሪ ካለ የእጁን ይስጠዉ!!!!!

  3. ወንድሞቼ አብይን በቅጡ ሳላውቀው እንዳሁኑ በጣም የምመካበት መሪ ነው ብዬ እርሱን ለመቀበል እዚህ አሜሪካ ቤቱስቤን ይዤ 14 ስአት በመንዳት በተዘጋጀውም አዳራሽ ለመግባት ለ7ሰዓታት ሳንስለች ተስልፈን በሳቅና በድስታ ነበር;: በዛ ስፍራ ዳንኤል ክብረት ዋናው አጋፋሪ ታማኝ በየነ እሽርጋጅ እግር ሳማ ነበር:: ግና ወራትም ሳይቆጠር አኔ ብዙ ወንድሞች በሚሰራችው በሚናገራቸው ያለውን ክፍትትና አስመሳይነት ግዜ ወስደን ቁጭ ብለን መነጋገር ስንጀምር ድክማችን ከንቱሆኖ የተባለትን ሳይሆን እጅግ ክፉ አስመሳይ አጭበርባሪ አፈ ቅቤ አቅርቦ የሚገድል በጣም ቂመኛ የተዋጣለት ሴረኛ የተካነበትም ስው ነው;:
    አስቡ ይህ ሰው በወጣነቱ ኦሮሞ በአማራ ተጨቁኖ ብሎ ወደ ህውሀት በበጎ ፈቃደኝት የገባ ነው ለህዋት ሎሌነት ላበረከተው አስተዋፅኦ ከስብል ሰርቪስ ኮሌጅ እስከ ፒኤችድ አሽክመውታል;;
    ይህ መልካም ግን አሁን ድረስ በወጣትነቱ ጀምሮ በተፈበረከው የአማራ ጥላቻና ፍራቻ አሁን ድረስ ግልፅ የሆነ አዲስ አበባ ላይ በእስክንድር ላይ በጥላቻና በዛቻ የተናገረውና ያስከለክለው የነብረው ማሳድድ ይህ ነው ዩየማይባል ነበር::አሁን ድረስ ለማንም ያልተስወረ አማራ ላይ ጂሀርን በእንክንካቤ አስቀምጦ የሚፈፅመው ግድያ ና ማዳከም ቀላል አይባልም::
    መንድማችን ጉዱ ካሳ ትክክል ብለሃል እውንትም ነው!አብይ እያስመሱለ የማገድል ነው!አንድ እናት አብይ ከኤድስ የከፋ በሽታ ነው

  4. “አሜን ነው! አሜን” የምትለዋ መዝጊያ ፈገግ አድርጋኛለች። ምክንያቱም ይች የነእሥራኤል ዳንሣ መፎገሪያ እንደሃሌ ሉያ የሚጠቀሙባት መሆንዋን ሥለማውቅ ጠሀፊውም ለፉገራ ብሎ (ጴንጤወቹን ማለቴ ነው)እንደጠቀሳት ሥለገባኝ ከልቤ አሣቀኝ፣ እንዲህ እያዋዙ ቁም ነገርን ማሥተላለፍ በውነቱ ግሩም ነው። በተረፈ የቀረበው ሃሣብ ለህሊና ሥውራንና ለከርሣሞች ካልሆነ በሥተቀር ምንም ህሠት የሌለበት ያዳባባይ እውነት ነው፣ ፈጣሪ ህገራችንን ክዚህ እይነቱ እስሥት ይገላግለን። በጣም አሥመሣይና ስልጣንና ዝና አፍቃሪነቱ ደግሞ ወደር የማይገኝለት እቡይ ነው።

  5. እኔን ደግሞ የገረመኝ የአቢይ አህመድ ነገር አይደለም! ኢትዮጵያን ማፍረስ የሚፈልጉ የኦሮሞ ዘረኞችም እኔም አንድ ላይ አቢይን ልንጠላማ አንችልም! የዚህ ጸሃፊ ደንቆሮነት የታየኝ እዚህ ላይ ነው- ጀዋርና ስራውን ጠልተን እንደገና ጀዋር አላማውን ማሳካት እንዲችል አቢይ እንዲጠፋለት ፈልጎ እኔም አቢይ እንዲጠፋልኝ ፈልጌ እንደተፈለገውም አቢይ ብጠፋ ማነው አሸናፊው እኔ ነኝ ጀዋር? እንተ ዝም ብለህ በነፋስ እየተነዳህ ዳንኤል አቢይ ብርሃኑ እያልክ የምትክለፈልፈ ክልፍልፍ እባክህ ረጋ ብለህ አስብ! ዝም ብለህ ማታ ያየኸውን ቀን መጫሩን ተውና ምንድነው አማራጬ ማነው ስትራቴጂክ ዘመዴ ብለህ እራስህን ጠይቅ- ዱሮ ጥሩ ትጽፍ ነበር አሁን ግን አንተም ገለባ ሆነህ ቀረህሳ ምነው?

    • ወንድሜ አባተ በለው ለአሥተያየትህ እጅግ አመሠግናለሁ። በግል ደረጃ ግን መሰዳደቡ ጥቅም የለውም፤ አያሥተምርምም። ስማኝማ – መጽሐፉ “ወንድሙን ‘ጨርቃም’ ብሎ የሚሣደብ የሸንጎ ፍርድ ይገባዋል” ይላል። ስለዚህ ለኔ የወረወርካቸው “ደንቆሮ፣ገለባ” የሚሉ ስድቦች ተገቢነታቸው ብዙም አልታየኝም። ስህተቴን በጨዋ ቋንቋ ብትነግረኝ ወይ ብታስረዳኝ ግን ታስተምረኝ ነበር። ስድብ የመካን አእምሮ ውጤትና የድውይ አስተሣሰብ መደገፊያ ምርኩዝ እንጂ እንዳንተ ካለ የተማረና ራሱን በወቅታዊ የዓለም ዕውቀትና ግንዛቤ ካዘመነ ዜጋ በፍጹም አይጠበቅም። ስድብ ስድብን ይወልዳልና ከባድ ቢሆንም በአእምሮ እንደማደግ ያለ ጠቃሚ ነገር የለም።
      ስለበፊቱ ሥራየ ለሰጠኸኝ ምሥጋና አመሰግናለሁ። ከነልዩነታችን እወድሃለሁ፤ ቸር ሰንብትልኝ ወንድሜ።

      • ጉዱ ካሳ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ- አቢይን ልያጠፉት ቀርበው ያልተሳካላቸው አሁንም ቀንና ማታ የሚሞክሩ ሃይሎች እንዳሉ ላንተ መናገር የሚያስፈልግ አይመስለኝም! ለምን ሊያጠፉት እንደሚፈልጉ ደግሞ እኔም አንተም የምናውቅ ይመስለኛል። እነዚህ አቢይን ማጥፋት የሚፈልጉ ሃይሎች ደግሞ ኢትዮጵያ እንደ ቅርጫ ስጋ ብትከፋፈል ደንታ የላቸውም እኔና አንተ ደግሞ እሱን አንፈልግም- እስኪ ንገረኝ የት ነው የኔና ያንተ አሰላለፍ መሆን ያለበት የምናየው ትልቁን ስዕል ከሆነ? ለዚህ ነው ዝም ብለህ ነው የምትጋልበው ያልኩህ! አንተ ብቻ አይደለህም ብዙዎች ናቸው እንደሱ የሚያስቡ- ዳንኤል ክብረት ጋር በብዙ ነገር አልስማማም ግን ስለአቢይ የተነገረው ያየውን ነው ደግሞም እዉነቱን ነው- እርግጠኛ ነኝ ይህ ሰው አቢይን ክኔም ካንተም በላይ ያውቀዋል- አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው የሃይል አሰላለፍ ምንድነው ያነተ አማራጭ- እኔ አቢይን ከቆሻሻው እደግፈዋለሁ! ምክንያቱም ኢትዮጵያ ሳትከፋፈል እንደአገር መቀጠል አለባት በሚለው ሃሳብ ላይ አንለያይም- ዳንኤልን ዝም ብለህ ቦጨከው እንጂ እሱም ይህንኑ ነው ያለዉኮ1 ኢትዮጵያን ሊዉጧት የቀረቡ የአገር ውስጥ ሃይሎች በበረቱበት ግዜ ኢትዮጵያን ከሚዉጧትና ሊያጠፏት ከሚፈልገው ጎራ ዉስጥ ኢትዮጵያን የሚያድን ወይም በኢትዮጵያ ወደፊት ላይ እንዴኔም እንዳንተም የሚያስብን ሰዉ እኔም አንተም የማንፈልጋቸዉ ሰዎች ትልቅ ዛቻና ሞት ሲደገስለት አንተም ከእነዚህ ገዳዮች ጋር ማበርህ የሚያሳየኝ አንድ ነገር ቢኖር የሩቅ ሳይሆን የቅርብ አሳቢ መሆንህን ወይም እንደ እስክንድር ጭንብል ያላወለክ ዘረኛ ነህ- ውትወታዉንና የቄስ መሰል ምክሩን ትተህ የቆምክበትን ጎራ ወይ ያለህን አማራጭ ንገረኝ

        • አብቶ አሁን መጠነኛ ለውጥ ማሣየት ጀምረሃልና ደሥ ብሎኛል፤ ሮም ባንዴ አልፈረሰችም/አልተገነባችምምና ጅምር ዕድገትህን ውድጄልሃለሁ።
          ቢሆንም “የምትጋልበው፣… እንደ’ሥክንድር ጭምብል ያላወለቅህ ዘረኛ ነህ፣ ውትወታውንና የቄስ መሰል ምክሩን ትተህ…” በሚል ያስቀመጥካቸው አገላለፆችህ “ዕድገት”ህን አጠየሙብህና ትግሥት አልባነትህን አሣበቁብህ። አሁንም ተሥፋ አልቆርጥም። ሥትፈልግ አቻምየለህም በለኝ አሣምነው … ቄስም በለኝ ሊቀ ጳጳስ የሚጠቅምህን እነግርሃለሁ፤ ሣትቆጣ አንብብ። ኮሮና ከሰጠኝ ያመት ዕረፍት ጊዜየን ሰውቼ ነው እማወጋህ።
          ከሰው ጋር ተነጋግሮ ለመግባባት ታጋሽና ትኁት መሆን እጅግ ጠቃሚ ነው -ሲጀመር። እንዳንተ ቡፍ ቡፍ በማለትና በሥድብና ዘለፋ በልጦ በመገኘት የማንንም ልብና አእምሮ በሃሣብ ልዕልና ማሸነፍ አይቻልም። ትዕቢትና እንደልቡ መሆን ሰውን ያርቃል፤ አፍ እንዳመጣ መናገር ለጠብ እንጂ ለዕርቅ አይገፋፋም። ንግግርና ውይይት ጥበብ ነው፤ ንግግርና ውይይት የታሰበባቸውና የታሹ ዲፕሎማቲክ ቃላትን ይፈልጋል። አለዚያ በቀደመው አስተያየቴ እንዳልኩህ ሥድብ ሥድብን ይወልዳልና መውረድ ለሚፈልግ ሥድብ ካለድካምና ወጪ በቀላሉ እንደመገኘቱ ለማንም ከባድ አይደለም። እሥካሁን ምንም እንዳላልኩ አውቃለሁና ታገሠኝ።
          …አንተ በምታስበው መንገድ ምንም ጎራ የለኝም። ጎራ ካልነው ጎራየ ኢትዮጵያዊነት ነው። የፖለቲካ ፓርቲ አባል አይደለሁም። ግለሰቦች ምንም ይሥሩ ምን አላመልክም፤ አልሰግድም። ግን በሚወደዱበት ማመሥገንን፣ በሚወቀሱበት መውቀሥን የሚከለክለኝ ሊኖር እንደማይገባ አምናለሁ። ሰውን መውደድ ችግሩን እንዳታይ ካሣወረህ ሌላ ችግር ነው።
          የሀገሬ ችግር መፍትሔው – በጉጉት የምትጠብቀው ይመሥለኛል እሥከዚህ አብረኸኝ ከተጓዝክ – የአስመሣይነትን ካባ አውልቆ እውነተኛ የሕዝብ ሰው መሆን ነው። ከዘረኝነት አረንቋ መውጣት ነው። ወያኔ ከተከለው የተረኝነት አባዜ መውጣት ነው። ሁሉንም ዜጎች እኩል ማየት ነው። እንደውሻ አጥንትና ደም ከማፈንፈን ድውይነት ወጥቶ በሜሪት ማለትን በትምህርትና በሙያ ችሎታ ዜጎችን ወደ ሥራ ማሠማራት ነው። ወገብን ጠበቅ አድርጎ ሙሥናን መዋጋት ነው። በጎሣና በእከክልኝ ልከክልህ ከየጉራንጉሩ ተጠራርቶ ቢሮክራሲውን የሥንግ ይዞት ያለውን ለኢንቬስትመንት ፍሰትና ለአጠቃላይ የሀገር ዕድገትና ብልጽግና ደንቃራ የሆነ የተተበተበ ቢሮክራሲ ማዘመን ነው። በአናቱ የተፈጠፈጠውን የትምህርት ጥራት ወደቦታው መመለሥ ነው። የጠፋውን የሃይማኖትና የሞራል እንዲሁም የባህልና ወግ ዕሤቶች በመመለሥ በተለይ ወጣቱን ከገባበት የከሠረ ሥብዕና መታደግ ነው። … የነበሩብንን ችግሮች አርሞና አሥተካክሎ፣ ጠቃሚ አዳዲስ የተራክቧችን ፈርጦችንም ጨምሮ የተዋበች ኢትዮጵያን ለሁላችንም በምትመች መልኩ መፍጠር ከገባንበት አጣብቂኝ በአንዴም ባይሆን በሂደት ያወጣናል።
          “ውይ፣ ውይ፣ ውይ … ምን ዓይነት ነዝናዛ ሰው ገጠመኝ” ሳትለኝ ነገሬን ባጭሩ መቅጨት እንዳለብኝ ተረዳሁ፤ ቻው ወንድማለም። ለማንኛውም ma74085/gmail.com

        • እኔም እንደ ጻሓፊው ነው እምነቴ። በተለይ የ ዳንኤል ክብረት ከመጠን በላይ ዉዳሴ ማቅረቡ ገርሞኛል። ለነገሩ ሰይጣንም አልጠላዉም ካለ ሰው ምን ይጠበቃል። እግዚአብሄር እንካን ሰይጣንን ስለ ጠላው ሲኦል ኣዘጋጀለት ለሚከተሉትም ጭምር። ዳንኤል ክብረት በትክክል የእግዚአብሄር ኣገልጋይ ቢሁን ወደ እግዜአብሄር ጸልዮ የ ዶክቶር አብይ ልብ ምን እንደ አሰብ አዉቆ ቢያወድሰው ጥሩ ነበር።

  6. ጓድ ጉዱ ካሳ
    መንግስቱን የምትደገፍ ፍጡር ሌሎችን ለመገምገም ምንም የሞራል ብቃት የለህም።
    አንተ የምትፈልጋት ኢትዮጵያ አትኖርም።

  7. ለመታወቅ ብለህ እንቅልፍ አጣህ ። በርበሬ ነጋዴዎች መገደላቸው ትክክል ነው ያልክና አብይ ነጋዴዎቹን መግደል አለበት ብለህ የጻፍክ ሰው አሁን ደግሞ አብይን ትወቅሳለህ ። አብይ ኦሮሞ ስለሆነ ነው? የተሻለ ሃሳብ ከሌለህ ጀርመን ተቀምጠህ መለቅለቁንአቁም ወይም ገብተህ ታገል።

    • ይቺ የጀርመን ነገር እዚህም ተደገመች! እንዳፋችሁ ያድርግልኝ እንዳልል ለነሱም አልሆነላቸውም፤ ይሄውና ኮሮና ባመጣው የኢኮኖሚ ቀውሥ ተበሣጭቶ የሄስ እሥቴት የገንዘብ ሚ/ር ሰሞኑን ራሱን አጠፋ። ስለዚህ ዕድሜና ዕድል ካሣኩልኝና ይህን ደደብ ወረርሽኝ ካመለጥኩ እዚሁ አገሬ ላይ ሆኜ “ስደት ወደ ኢትዮጵያ ይሆናል” የተባለለትን ወርቃማ ዘመን ብጠብቅ ይሻለኛል።
      Robii ለተባልከው ኦነግ የምለው የለኝም፤ ያልከኝ ሁሉ እኔን እንደማይወክል ግን መግለጥ አለብኝ። ማንም ከህግ አግባብ ውጪ ይገደል አልልም፤ ኦሮሞ ሆኜ ኦሮሞን አልጠላም፤ ለመታወቅ ብሎ የሚጽፍ ሰው የመዝገብ ሥሙን ይጠቀማል…
      የኦቦ ቀጀላ ልጅ “አንተ የምትፈልጋት ኢትዮ አትኖርም” ላልከው የኔ ኢትዮ በቅርቡ እንደምትነሣ በእ/ር ሥም እምልልሃለሁ – በምንም ነገር መማል ባይፈቀድም። አትቸኩል።
      ግርምሽ በምርቃና ያልካትን ቃል ከረሳኋት አንድ 10 እና 11 ዓመታትን ያህል አሣለፍኩ። በምርቃና ሣይሆን በብርድና በንዴት ውሥጥ ሆኜ ብዘውን ጊዜ ደግሞ በሌሊት ነው የምጽፈው።

  8. ትልቅ ስብዕና የተላበሰን ገፅ ባህርይ ስትቀልድብት ማየት
    ያማል።
    የብእር ስምህን ብትቀይር ለኔ ትልቅ ውለታ ነው።
    ጉዱ ካሳን አትመጥንም ።በጭራሽ።

    • “እውነትህን ነው ኃይሉ C አለማው? የኢትዮጵያ ንፍር ቁሥል ሣያምህ የትኛው ገጸ ባሕርይ ላይ መቀለዴ ነው ይበልጥ ያመመህ? ሥሜንስ ወደምን ብለውጥልህ ያስደስትህ ይሆን?” ብዬ ልጽፍ ፈለግሁና ከሥንቱ … ጋር ተዳርቄ እዘልቀዋለሁ ከሚል አስቤ ተውኩት ፥ ምንም እንኳን ዕድሜ ለኮሮና ከበቂ በላይ ጊዜ ቢኖረኝም አሁን። ይሄ ፍቅር የሚሉት ደምባራ በቅሎ ግን ይገርመኛል። ትዝብትንና ይሉኝታ የሚያስረሣ ገልቱ ነገር ነው።

  9. እኔም እንደ ጻሓፊው ነው እምነቴ። በተለይ የ ዳንኤል ክብረት ከመጠን በላይ ዉዳሴ ማቅረቡ ገርሞኛል። ለነገሩ ሰይጣንም አልጠላዉም ካለ ሰው ምን ይጠበቃል። እግዚአብሄር እንካን ሰይጣንን ስለ ጠላው ሲኦል ኣዘጋጀለት ለሚከተሉትም ጭምር። ዳንኤል ክብረት በትክክል የእግዚአብሄር ኣገልጋይ ቢሁን ወደ እግዜአብሄር ጸልዮ የ ዶክቶር አብይ ልብ ምን እንደ አሰብ አዉቆ ቢያወድሰው ጥሩ ነበር።

  10. በዉነቱ አንድ ዜጋ ላይ መጠነ ሰፊና ዘርፈ ብዙ ድብደባ ሲካሄድበት ማየት በእጂጉ ያሳዝናል የሚያሳዝነዉ ደግሞ ልዩ ልዩ አላማ ያላቸዉ ዳንኤል ክብረትን ሲያሳድዱት ሲያዋክቡት ሌላዉ እሱን ለመከላከል ያለመምረጡ ነዉ። ዳንኤል ክብረት ምን በድሎ ነዉ ብዬ ወደሗላ ተመልሼ ነገሮችን ማገናዘብ ሞከረክኩ 1.አንዳርጋቸዉ ጽጌ መጀመሪያ አብሪ ጥይት ተኮሰ ዳንኤል ክብረት በዶ/ር አብይ ሞገስ ማግኘቱ እሱ ያሰበዉን የማማከር ቦታ መያዙን ሰለተገነዘበዉ ማጠልሸት ጀመረ 2. አህመዲን ጀበል አህመዲን ጀበል አቢይ አህመድ አካባቢ ለመሆን ያልፈነቀለዉ ድንጋይ የለም የአብይ አህመድ አባት ሲሞቱ ተሽቀዳድሞ ቦታዉ ላይ በመገኘት በእስልምና ትራዲሺን ፍታት አድርጓል ማን ጠራዉ የአብይ አህመድ አባት በሞቱበት አካባቢ በእስላም ትራዲሺን ይህን የሚያደርግ ሰዉ ጠፍቶ ነዉን አይደለም አህመዲን ጀበል ይህን አስመልክቶ ወደ ቤተመንግስት መጠጋቱ ነበር አልሆነም እንደ ዳንኤል ክብረት የልብ ቅንነት የላቸዉም ዳንኤል ክብረት ሊሰጥ የሚችለዉን አገልግሎት በምንም መልኩ ሊሰጡ አይችሉም እነኳን አብይ አሕመድ እነ አህመዲን ጀበል ስልጣን ላይ ቢወጡ ዳንኤል ክብረት የመጀመሪያ ምርጫቸዉ መሆኑ አይቀርም።
    ቀሪዉን በበቂ ጥናትና ግንዛቤ አወጣዋለሁ ለጊዜዉ ግን ይህን ምንም ያላጠፋ ወይም ደግሞ ጥፋቱና በደሉ ከዳዉድ ኢብሳ፤በቀለ ገርባ፤ጁዋር መሀመድ፤አህመዲን ጀበል፤ዲማ ነገዎ፤አርከበ እቁባይ፤ በያን ሱጳ፤አረጋዊ በርሄ፤ጻድቃን ገ/ተንሳይ ፤ሰየ አብረሃ ባሉበት አገር ይህን ወደፊት ብዙ ሊያደርግ የሚችል ዜጋ ለጥጦ መያዝ አግባብ ባለመሆኑ እጃችሁን እንዳተነሱለት ለማሳሰብ ነዉ ቀሪዉን በቅርቡ በጹህ መልክ አወጣዋለሁ ተከታተሉ። እንዲህ ለኢትዮጵያ ያስባል የምትሉትን በስብጥር ተኩስ እያዋከባችሁ ሰዉ ከኢትዮጵያዊነት እንዲያፈነግጥ የምታደርጉት ርብርብማ መቆም አለበት።
    ዳንኤል በርታ የበረዶ ክምር እንዳንተ በእዉቀት አሎሎ ይደረመሳል አትፍራ አትስጋ በዛዉ ልክ አድናቂ አለህ ጻፍ አትደንግ እነ አህመዲን ጀበል ለራሳቸዉ ተረት ይደርቱ አያገባህም በክርስትና ያለዉን ቆፍር አትድረሱበኝ በላቸዉ ከደረሱብህ ዉርድ ከራሴ ነዉ በላቸዉ።
    ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share