‘ያልታረሙ አንደበቶች ሀገርን ያዘቅጣሉ!’ – ፀጋዝአብ ለምለም ተስፋይ

ፀጋዝአብ ለምለም ተስፋይ- የኢኮኖሚክስ መምህርና ጸሓፊ

(ሸክም የበዛበት ትውልድ፡2009 እና የምሥራቃዊት ኮከብ፡ 2010 መጻሕፍት አዘጋጅ)

ንግግር በሰው ልጆች ያለፉ፣ ያሉና የሚኖሩ ኹለንተናዊ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መሰተጋብሮች ውስጥ የማይተካ ሚና እንዳላቸው የሚታወቅ ሃቅ ነው፡፡ ንግግር ስሜትን፣ ሃሳብንና ምኞትን የሚገልጽ ከመኾን ባሻገር ከአንዱ ወደ አንዱ የማስተላለፊያ – ትልቅም ተጽዕኖ የመፍጠሪያ ዐቢይ መሣሪያ ስለመኾኑ ማንም በመኖር የሚያውቀው ዕውነት (Truth) እና እውነታ (Reality) ነው፡፡

በሀገራችን ባህል፣ ወግ፣ ልማድና ኹለንተናዊ መስተጋብር ውስጥ ንግግር ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ከመኾኑም ባሻገር ሰዎች እርስ በራስ የሚተያዩበትን አውድ ራሱ የወሰን ኃይል አለው፡፡ በሥነ ቃሎቻችንም ቢኾን ብዙ ብዙ ተብሏል፡፡

ለአብነት፡- “ከንግግር ይፈረዳል – ካያያዝ ይቀደዳል፤” የሚለውን እናገኛለን፡፡

ይህም ከግለሰብ/ቦች፣ ከቡድን/ኖች እና ተቋማት/ቶች መልዕክትና ገለጻ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው፡፡ በተለይ ከማንኛውም የሕብረተሰብ ክፍል በላቀ – በተሻለና አርዓያነት ባለው መንገድ ከምሁራን፣ ከኪነ ጥበብና የሥነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ከሃይማኖት አባቶች፣ ከመሪዎች፣ ከገዥዎች፣ ከባለሙያዎች፣ ከጋዜጠኞች፣ ከእድሜ ባለጸጋዎች – – –  ወዘተ የሚጠበቁ ነገሮች አሉበት፡፡

አንድ ሰው የሃይማኖት አባት ኾኖ እንደአንድ ሥነ ምግባር የሌለው ወጣት የሚጠቀምበትን የንግግር ዘዪ ተከትሎ ቢናገር ከንግግሩ በላይ “ከአንድ የሃይማት አባት የማይጠበቀ” እየተባለ የሚወቀስበት ነጥብ ሚዛን የሚደፋ ኾኖ እናገኘዋለን፡፡

ከንግግር ይዘት፣ አይነትና መጠን ብሎም አቀራረብ አንጻር በባህሪያዊና ጠባያዊ መገለጫዎቹ የተነሳ ንግግር መልካም ብቻ ሳይኾን መጥፎ፤ የላቀ ብቻ ሳይኾን የዘቀጠ፤ ምርቃት ብቻ ሳይኾን እርግማን፤ ምክር ብቻ ሳይኾን ስድብ፤ ቁም ነገር ብቻ ሳይኾን ቧልት – – – ይቀርብበታል፡፡ በውጤቱም ማስደሰት ብቻ ሳይኾን ያሳዝናል፤ አንድ ማድረግ ብቻ ሳይኾን ይከፋፍላል፤ ፍቅርን ብቻ ሳይኾን ጥላቻን ማስፋፊያ ይኾናል፤ – – –  ከመቀራረብ ይልቅ ያራርቃል፤ ከፍ ሲልም ጦር ያማዝዛል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ስሜቱ ይቁምና እስቲ አማራጮችን በእርጋታ እንመልከት - ግርማ ካሳ

በሀገራችን ዛሬ ዛሬ በአደባባይ እንደሚስተዋለውና በየሚድያዎቹ እንደሚስተጋባው ንግግሮችን በተለይ የጋዜጠኞችን፣ የምሁራንና የገዥዎችን ስንመለከት ዕውን የያዙትን ኃላፊነት የሚመጥን፣ የሚገባና አርዓያነት ያለው ነውን?

በርካታ ህዝብ በተሰበሰበበትና የህዝብ ተወካዮች ባሉባቸው ቦታዎች የሚነገሩ ንግግሮችን ስንመለከት፡

1ኛ. ከይዘት አንጻር እጅግ የተፋለሰ፤

2ኛ. በአመክንዮ ያልተደገፈ – በስሜት የተሞላ – ማስመሰልና ሴራን ማዕከል ያደረገ – መነሻውና መዳረሻውን ፕሮፖጋንዳዊ ዓላማና ግብን ብቻ ያደረገ ትርጉም አልባ አስተያየቶች የተበራከቱበት፤

3ኛ. አሽሙርና ስድም አለፍ ሲልም በዘለፋ ላይ የተመረኮዙ  – ህልውናቸውንም በዛ ላይ ያደረጉ፤

4ኛ. በቃላት አጠቃቀም እጅግ የወረዱና የዘቀጡ፤

5ኛ. አርዓያነት የሌላቸው – እጅጉን በአደባባይ ሃሰት የተሞሉ፤ ከአንድ ትልቅ የኃላፊነት ደረጃን ከያዘ/ዙ ግለሰቦችና ቡድኖች የማይጠበቁ በርካታ ንግግሮችን በየሚድያውና በየስብሰባ አዳራሹ መስማት እንደአንድ ጀብዱ የሚቆጠርባቸውን ኹነቶች እጅግ በተደጋጋሚ ታዝበናል፡፡

ተናሪው ስለሚናገረው ሀሳብ ዕውን ለምን? እንዴት? መቼ? የት? በምን ኹኔታ ውስጥ ትውልዳዊና ኃላፊነታዊ ግዴታን እወጣለው ብሎ ከማሰብ ይልቅ እጅግ በስሜት የተሞላ፣ ከነባራዊ እውነታ እጅጉን የራቀ፣ በተራ የቃላት ድርደራ የተሞላ፣ ከንቱ መታበይ የተሞላበት፣ በልቅምቃሚ ጥቅሶች የተጥለቀለቀ፣ በጥቃቅንና አነስተኛ አጀንዳዎች የተሞላ፣ ጥላቻን የሚዘራ መልዕክት የተበራከተበት፣ ጭብጨባን ማዕከል ያደረገ፣ ከመድረኮቹ ዓላማ እጅጉን የራቀና የተቃረነ – – – ብዙ ህዝብ በተሰበሰበበት ተራ የግለሰብና ቡድኖች የርስ በራስ የፕሮፖጋንዳ ጦርነት አውድማ የኾነበትን አጋጣሚ በብዙ መንገድ ከመመልከታችን ባሻገር መሻሻሎች ሳይታዩበት እየቀጠለ ይገኛል፡፡

ዕውን የኢትዮጵያ ህዝብ የሚመጥነውን ንግግር እየሰማ ነውን? ዕውን የሚያስፈልገው ኹለንተናዊ መልዕክት እየተላለፈለት ነውን? ዕውን በየመድረኮቹ የምንታዘባቸው እጅግ የዘቀጡና የወረዱ የአንደበት ንግግሮችን አሉታዊ ተጽዕኖ ኹለንተናዊ ዋጋ ማን ይከፍላል? ማንስ ይጠየቃል? ዕውን በኢትዮጵያ ውስጥ ላልታረሙ አንደበቶች ልጓም የኾነው ምንድነው? ያለአሽሙርና ስድብ ንግግር ማድረግ የሚችሉ የማይመስላቸው – ኾን ብልው አስበውና አሰላስለው በመግለጫ፣ በመልዕክትና በመልሳቸው ላይ የሚከቱ ገዥዎች አልተበራከቱምን?

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአገዛዙ መልክ ሜክ አፑ እየለቀቀ አሁን ትክክለኛ ገጽታው እየታየ ነው- ዜጠኛ መሳይ መኮንን

ባዶ ፍሬ ከርስኪ የኾነ ንግግር በማቅረብ በጭብጨባ የሰከሩና ጭብጨባን ማዕከል ያደረጉ እንቶ ፈንቶዎች በየቦታው የሚሰሙ አይደሉምን? የተጠየቀውን ጥያቄ በቀጥታ ከመመለስ ይልቅ ምንም የማይያያዝና ያልተጠየቀ ጥያቄ ራሱ ጠይቆ ራሱ የሚመልስ ትዕቢተኛ አልተበራከተምን? ለአንደበታቸው ሥርዓት፣ ወግና ግብረ ገብነት የሚባል ከቶ ያልፈጠረባቸው – ምሁራዊ ባህሪያትን ከአመክንዮ አንጻርና ከሀሳብ ጥልቀት አንጻር ከቶ የማያቀርቡ በርካቶች አይደሉምን?

የያዙትን ኃላፊነት የማይመጥኑ ከሚጠበቅባቸው እጅግ ወርደው፣ ዘቅጠውና ኃላ ቀርተው የሚገኙ ኾነው ሳለ ህዝብን  – የሚፈልገውን – ይፈልገዋል የሚባል – ያልኾነውንና ሊኾን የማይችለውን ውዳሴ በመንገርና በስሜት በማስከር አልያም በንግግራቸው ፍጹም ከተነሱ ኹለንተናዊ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መሠረታዊ ጥያቄዎች እጅግ የራቀ ተረት ተረት፣ ፍሬ ከርስኪ ቀልድና ቧልት አለፍ ሲልም ሃሰት በመጨመር የሚከናወኑ ተግባራት አልተበራከቱምን?

ዛሬ ዛሬ በሃገራችን ንግግሮች እጅጉን በሃሰት የተሞሉና ወደ መሬት የማይወርዱ እጅግ በርካታ ጉዳዮችን አልታዘብንምን? የህዝብን ትኩረት ለመሳብ ሲባል በሀገር ደረጃ ግለሰቦች ብቻ ሳይኾን ቡድኖችና ተቋማት ህዝብን ተደራጅተው፣ አስበውና አስልተው የሚዋሹበት –  የውሸት ዜና፣ መልዕክትና ዶክመንተሪዎች በእጅጉ አልተበራከቱምን? ሃሰተኝነትን የማንነታቸው አካል ያደረጉ – ሲዋሹ በአደባባይ ምንም የማይመስላቸው ነውረኞች አልተበራከቱምን? ሃሰተኝነታቸው ሲታወቅና ሲጋለጥ የበለጠ ውሸት በመዋሸት የሚዳክሩስ በርካቶች አይደሉምን? ሃሰተኝነትን ዋነኛ የስብዕናቸው መገለጫ ከማድረጋቸው የተነሳ ደሞ መጡ የሚባሉ በርካቶች አይደሉምን?

ዕውን ዛሬ ዛሬ የሚታመኑ ገዥዎች እነማን ናቸው? በንግግሩ የሚታመን ባለሥልጣን ማን ነው? እንኳንስ ህዝብ ሚስቱና ልጆቹ የሚያምኑት ባለሥልጣን ማን ነው? ሃሰተኛነትን የስብዕናው አካል ያላደረገ ማን ነው? ቃሉን የሚያከብር ጀግና ኢትዮጵያ አላትን?

ተጨማሪ ያንብቡ:  ማኪያቬሊ በዘመናዊው አምባገነን መንግስታት አብይ አህመድ እና ኒኮሊያ ማኬቪሊ በ 21ኛ ዘመን በኢትዮጵያ ሲተገበር

“ያልታረሙ አንደበቶች ካልታረሙ ግለሰቦችና ቡድኖች ሲወጡ – የታረሙ አንደበቶች በአንጻሩ ከታረሙ ግለሰቦችና ቡድኖች ይወጣል፡፡”

ንግግር በባህሪው በሰው ልጆች ኹለንተናዊ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስተጋብሮች ውስጥ ዘር ኾኖ በሰዎች አዕምሮ የሚቀር እያደገ ሲሄድም በዕይታ፣ በምልከታ፣ በአስተሳሰብና በአመለካከት ሂደት ውስጥ እጅግ የላቀ ሚናን የሚጫወት ታላቅ መሣሪያ ስለኾነ ያልታረሙ አንደበቶች እንዲታረሙ ኹለንተናዊ ሥራ መስራት ያስፈልጋል፡፡ ያልታረሙ አንደበቶች ሀገርን፣ ህዝብንና ትውልድን ወደ አዘቅጥ ሲወስዱ የታረሙ አንደበቶች በአንጻሩ ወደ ከፍታ ይወስዳሉ፡፡ ፈጣሪ ሀገራችን ነጻ ፍቃድን የኹሉ ነገር ማዕከል ወደ ሚያደርግ የዕሳቤ ሂደት ትገባ ዘንድ ይርዳን!

ቸር እንሰንብት!

4 Comments

  1. The people of Ethiopia were not given freedom of speech for too long , now when they open their mouth vulgar comes out. The religious leaders and the elders need to encourage people to hold conversations freely at an early age talking freely to people of all ages freely.
    Whipping beating children for what they say silences children until they get the chance to be free , all that beating donot stop them for life they keep silent only for the children to open their mouth in vulgar when they reach an adulthood age.

    ZIM BALEW AMARA YIHUNIBIN

    LIJOCHACHININ FIKEDULACHEW YANAGIRUN

  2. Mr. Tesfay

    Before you teach others about ግብረ ገብነት, try to learn and polish your conduct yourself. Look at the words you used to teach others.

    እንቶ ፈንቶዎች
    የወረዱ የአንደበት ንግግሮችን
    በጭብጨባ የሰከሩ
    በልቅምቃሚ ጥቅሶች የተጥለቀለቀ

    The people you insulted are better than the hypocrites like you.

    Thank you.

  3. በቅርቡ አንድ ከሃገር ውጭ የሚኖሩ ሃበሾች ለራት ይጠሩኛል። እኔም እሺ በማለት የሚይዘውን ይዤ ከሥፍራው እደርሳለሁ። ሌሎች ለእራቱ የታደሙ ሰዎችም ቀድመውኝ አገኘሁ። አንድንም አላውቃቸውም። ተዋውቀን ጥግ ጥግ ይዘን ወሬ ጀምረናል። ራት ቀርቧል ተባለና የአማረ ምግብ ቀረበልን። ገና መቅመስ ስንጀምር የሴትዬዋ ባለቤት እንዴት እንዲህ ጨው ታሳንሻለሽ በማለት ሚስቱን ማጣጣል ይጀምራል። እኔም ደንግጬ ጨው እኮ አንተ ራስህ መጨመር ትችላለህ ስለው እሷ መልሳ ተው ዝም በለው አመሉ ነው ስትል ተንሰቶ በጥፊ ይመታታል። ከዚያ በህዋላ ነገሩ ሁሉ ዝብርቅርቁ ወጣ። እኔም ከቤታቸው ወጥቼ መኪናዬ የቆመችበት ቦታ በመሄድ ወደ ቤቴ አቀናሁ። እነዚህ ሰዎች ልጅ የወለድ፤ ለረጅም ጊዜ ተጋብተው የቆዪ ሲሆኑ ሰውየውን ነበር የማውቀውና በማግሥቱ ደውዬ እንዴት እንዲህ ታደርጋለህ ስለው “ዝም በላት ለምዳለች መደብደብ፡፤ ካልተመታች ያፈቀርኳት አይመስላትም” በማለት ሲነግረኝ ችግሩ ሥር የሰደደ እና ያኔ ብቻ ያለሆነ መሆኑ ተረዳኝ። እኔም ከልጅ ጋር ያለኝን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ ቆረጥኩት።
    የመናገርና የመጻፍ የመሰብሰብ ነጻነት ልክ አልባ ሲሆን ሥርዓት የለሽ መሆኑ ቀድሞ የታወቀ ነው። በሃገሪቱ ሃብት ተምረው በተሰባጠረ ህብረተሰብ ኑረው ሃገር ቤት ገብተው የዘር ፓለቲካን የሚነዙ ጠባብ ብሄርተኞች እንደ ተለከፈ ውሻ በሚቅበዘበዙቧት ሃገር እላፊ ንግግርና የፈጠራ ታሪክ ቢደመጥ የሚያስገርም ነገር አይደለም። 17 ዓመት በወታደር መንጋ የታመሰችው ሃገር ለዘረኛዎቹ ወያኔንና ሻቢያ ታልፋ ስትሰጥ የመጀመሪያ ፍልሚያቸው የሃብት ክፍፍል ላይ ነበር። ሌባ ሲሰርቅ አይጣላም እንዲሉ ሲከፋፈሉ በደንበር አሳበው ተቧቀሱ። የብዙ ንጽሃን ደም ፈሰሰ። አሁን ደግሞ አንድ አስመራ አንድ መቀሌ ሆነው እጣት እየቀሰሩ እንጋጠም ይላሉ። የውሾች ፓለቲካ እንደዚህ ነው። ሁልጊዜ መነካከስ። ይህን ተገን አርጎ የሚወጣ ጽሁፍ የሚዲያ ዲስኩር የቁም ዲስኩር ሁሉ ልቅና የእኔ ያምራል ብቻን የሚያወራ የጠባብ ብሄርተኞች ቱልቱላ ነው። እውነት የምታገለግለው በገለልተኝነት ነው። ትላንት ነፍጠኛ ጡት ቆረጠ በማለት ወያኔ አኖሌን ያቆመለት የኦሮሞ ጠባብ ብሄርተኞች ዛሬ ቢስሚላሂና በስማም ሳይሉ ቤት የሚያቃጥሉና የሰው አንገትን በቆንጨራ የሚቆርጡ አረመኔዎችን አፍርታለች። በጠራራ ጸሃይ በወለጋ በሆነ ባልሆነው እያመካኙ የሰውን ደም የሚያፈሱት እነዚሁ የኦሮሞ ህዝብን ነጻነት እንሻለን የሚሉ በራሪ ተለጣፊዎችና ወሮበሎች ናቸው። ያልታረሙ አንደበቶች ሃገርን ቁልቁል ማውረዳቸው ዛሬ አይደለም የተጀመረው። ሟቹ የወያኔ አለቃ መለስ ዜናዊ ” ከወርቅ ህዝብ ወጣሁ” በማለት የደነፋበትም ጊዜ ትዝ ይለናል። በደርግ ዘመን እንደምን አደራችሁ ሲባሉ “እናሸንፋለን” ይባል እንደነበረው ሁሉ ዛሬም በድንግዝግዝ መጓዛችን ቀጥሏል። አፈኛና በጭብጨባ የታጀበ ከእውነት የራቀ ዲስኩር እንሰማለን። ግን ማንም ይሁን ምንም የሌላውን እያጥላላና ጥላሸት እየቀባ የእኔን ውደድልኝ ማለት አይችልም። እንደ ህዝቅየል፤ መራራ፤ ጃዋር፤ በቀለ ያሉት የኦሮሞ ዘረኛ ፓለቲካ አራማጆች የሚያላዝኑት በሻገተ የፓለቲካ እይታ ነው። በአለም ላይ ምንም ቢሆን ሳይገፋና ሳይጨቆን የኖረ የለም። ጭራሽ። እነዚህ ተምረናል የሚሉ የምላስ ሾቶሎች ግን መማራቸው በሃገራችን ሞፈርና ቀንበር አስማምቶ አርሶ በሰላም ከሚገባው ገበሬ ያነሰ እይታ ያላቸው የክፋት ቋቶች ናቸው። ዘረኞች ሁልጊዜም ሰልፋቸው በቋንቋቸውና በጎጣቸው ብቻ ነው። የሚጽፈውን፤ የሚባለውን ሁሉ አንብበን ከተሟገትን ጊዜ አይበቃም። ዝምታ ወርቅ ነው የሚለው የሃገሬ ህዝብ የእነዚህን የ21ኛ ክፍለ ዘመን የሙታን ፓለቲከኞችን እይታ አይቶ ለማለፍ እንዲረዳም ጭምር ነው። ሚስቱን ደብዳቢውም አባወራ አድፋጭ ፓለቲከኛና በዘሩ ተሰላፊ ነው። ቤቱን ግን ማስተዳደር እንኳን አልቻልም። አታድርስ ነው!

    • The truth is the series of crimes Ethiopians suffered and are continuing to suffer with no end in sight predespotioned Ethiopians to be frustrated to a point where they loose their patience. If we see the current leaders AKA the Prosperity Party is an illegal party , electoral board committed a serious crime when it recognized Prosperity Party.
      EPRDF killed looted murdered made a mockery out of Ethiopia and to top it off tried to say it became PP and TPLF NOMORE EPRDF, promising none of the EPRDF crimes will happen again and the people forgave EPRDF Ethiopians believed EPRDf is in a reform , but EPRDF’s crimes against humanity did not stop , actually the crimes against humanity it all happened in a pace too quick for anyone to keep track off all the crimes that got committed while Sahleworq Zewde and Birtukan Midekssa were busy fingering vibrating themselves hugging Abiyot Ahmed’s picture or picturing the jigilo Abiyot Ahmed in their minds all-day and all-night .

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share