እንዴት ከዘቀጥንበት ወጥተን ወደ ፊት እንራመድ? – ባይሳ ዋቅ-ወያ1

ባለፉት ወራት ባገራችን የተከሰተውን አሳዝኝና ትርጉም የለሽ ግድያን በተመለከተ የተለያዩ የመንግሥትና የግል ሚዲያ ተቋማት በየፊናቸው ያስተላልፉ የነበረውን ዜና ከያለንበት ሆነን ስንሰማውና በቴሌቪዥን መስኮቶቻችን ስንመለከተው እንደነበር ይታወሳል። አዎ! ሰዎች በግልጽ በአደባባይ እየተቀጠቀጡ ሲገደሉ አይተን በእጅጉ አዘንን። እጀግ በጣም አሳዛኝና ምነው ኢትዮጵያ ውስጥ ባልተፈጠርኩ የሚያሰኝ የጭካኔ ጣራ የታየበት ዓመት! በወጣትነት ዘመናችን ሲነገረን የነበረውና እኛም እንደወረደ ስንጋተው የነበረው ኢትዮጵያዊ ጨዋነት፣ ባህሉን አክባሪና ከሁሉም ጋር ተስማምቶ በፍቅር ኗሪ፣ የደከመውን የሚያበረታታና ያዘነውን የሚያጽናና፣ ፈሪሃ እግዚአብሄርን በመላበሱ በአምላክ ፍጡር ላይ ጉዳትን የማያደርስ ቅዱስ ሕዝብ ወዘተ የሚባለው ባሕላዊ እሴቶቻችን ወዴት እንደተነኑ በበኩሌ አልገባ ካለኝ ውሎ ሰንብቷል። የዚያኑ ያህል የሚዘገንነው ደግሞ የሕዝባችን ከሚያየው ይልቅ ከሚሰማው ብቻ ተነስቶ እርምጃ ለመውሰድ ያለውን ችሎታ ነው፡፡ ብዙውን ጊዜ እንዳስተዋልኩት ከሆነ ሕዝቦቻችን የሚሰሙትን ወሬ እውነተኝነት ለማረጋገጥ ሴኮንድ እንኳ ሳያጠፉ፣ የሰሙትን ወሬ እንዳለ፣ ከተቻለም ጆሮያቸው ሊሰማ በሚፈልገው ልክ አመቻችተው ተመሳሳይ አስተሳሰብን ለሚያስተናግዱ ጓደኞቻቸው ያቀብላሉ፡

 

  • በዚሁ ሂደት ውስጥ ውጭ አገር የከተሙ የግል ሚዲያዎችና አፍቃረ – ፌስቡኮች ደግሞ ወሬው እንደደረሳቸው ለአርዕስታቸውም እንደሚመች አሳምረውት፣ አገሪቷ ከሰሜን እስከ ደቡብ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ታምሳና ሕዝቦች ተገዳድለው ሕልውናዋ በቀጭን ገመድ ላይ ተንጠንጥሎ ይገኛል ብለው ማስተጋባት ይጀምራሉ፡፡ የወሬዎቹ ይዘትም ወገንተኛና አንዱ ቡድን በሌላው ላይ ስላደረሰው ወይም ሊያደርስ ስለተዘጋጀው ጥቃትና እንዴት ለመከላከል ብሎም ለመልሶ ማጥቃት መዘጋጀት እንዳለባቸው ነው፡፡ በአጭሩ፣ በአገሪቷ ሰፍኖ ያለው ድባብ “እኛና” “እነሱ” በሚል ሁለት ጎራ የተከፈለ ይመስለኛል፡

 

  • የዚህ ሁሉ ፊታውራሪ ደግሞ ከሁሉም ብሄር የተውጣጡ፣ ሳይወከሉ ተወክለናል ወይም የሕዝባችን አደራ አለብን የሚሉ ጽንፈኛ ኤሊቶች ናቸው፡፡

 

ግን ለምን እንዲህ ሊሆን ቻለ? ለምንድነው ታዋቂ በሆኑ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ የትምህርት ተቋማት ሳይቀር የፊደል ቆጠራ ጉብዝናቸውን ያስመሰከሩ ኤሊቶቻችንን ስላገራችን ነባራዊም ሆነ ወቅታዊ ፖሊቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊና ማሕበረሰባዊ ችግር በትክክል እያወቁ ወይም ማወቅ ሲገባቸውና፣ ለዘመናት ነቀርሳ ሆነው ውስጥ ድረስ በልተውን ከደሃ አገሮች ተርታ ብቻ ሳይሆን መጨረሻ ላይ ያሰለፉንን እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ መረባረብ ሲገባቸው፣ ሁላቸውም በየጎሬያቸው መሽገው “የማንነትን ጥያቄ” በማንገብ ሕዝብን ለሕዝብ ጋር ለማጋጨት የተሰለፉት? ለምንድነው ዛሬ ባገራችን ያብዛኛው ኤሊት ቀዳሚ ታማኝነት ለተወለደበት ብሄር እንጂ ለሰማኒያ አምስቱ ብሄር ወይም “ለኢትዮጵያ ሕዝብ” ያልሆነው? እንደው የሶስት ሺህ ዘመኑን ታሪክ እንተውና ላለፉት አንድ መቶ ሃምሳ ዓመታት እንኳ ኢትዮጵያ በምትባል አገር ውስጥ ባንድ መንግሥትና ባንድ ባንዲራ ሥር እየኖሩ፣ ለምንድነው ሕዝቦቿ በሌሎች አገራት እንደታየው አንዱ ባንዱ ውስጥ ቀልጦ “አንድ ሕዝብ” መሆን ያልቻለው? ምን ዓይነት የሂደት ችግር ቢፈጠር ነው የዛሬ መቶ ሃምሳ ዓመት የነበረው ሰማኒያ አምስት የየራሱ ቋንቋ የነበረው ብሄር ዛሬም ከመቶ አምሳ ዓመት በኋላ ሰማኒያ አምስት ብሄርና ሰማኒያ አምስት ቋንቋ እንዳለ ይዘን የቀረው? የት ቦታ ላይ የአገር ምሥረታው ስልት ቢጠፋብን ነው ዛሬ፣ ከመቶ አምሳ ዓመታት በኋላ፣ “ማንነቱና ቋንቋው ከስሞ አማራ ሆነዋል” በመባል የታወቁ የአገውና የቅማንት ሕዝብ፣ “የለም በአማራ ተጨቁነን ማንነታችን ተዳፍኖ ነው እንጂ አልከሰምንም” ብለው የማንነት ጥያቄ የሚያቀርቡት? አዎ ባንድ ባንዲራ ሥር ለዚያን ያህል ዓመታት የኢትዮጵያ የግዛት አንድነቷ ተጠብቆ፣ ሕዝቦቿ ደግሞ በተለያዩ ጊዜያት የውጪ ወራሪ ኃይልን ባንድ ላይ ሆኖ ተከላክሎ የግዛቷን አንድነት አስከበሮ የኖረውን ያህል የሕዝቦቿ አንድነት ዕውን ሆኖ አንድ ሃገረ ብሄር ለመሥረት ያልቻልነው ለምንድነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ ይመስለኛል። አንዳች ዓይነት ምክንያት ቢኖር ነው እንጂ፣ የውጪ ወራሪ ኃይል ሲመጣ ሆ ብሎ ባንድ ላይ ዘምቶ ድልን ከተጎናጸፈ በኋላ ሁሉም ወደየጎሬው ተመልሶ ባንድ ላይ የተጎናጸፈውን ድል አንድ ላይ ሆኖ እንደማጣጣም፣ ውሃና ዘይት ሆኖ ጎን ለጎን መኖርን እንደ ትክክለኛ የጉርብትና ኑሮ ዘይቤ አይቆጥርም ነበረ። ይህንን ምክንያት ለይቶ አውቆ መፍትሄ ፍለጋው ላይ መረባረብ ግን ተምረናል ከምንል ኤሊቶች የሚጠበቀብን አገራዊ ግዴታ ነበር። እየሆነ ያለው ግን ተቃራኒው ነው።

 

ሌላው ከዚህ ጋር የተያያዘው አሳሳቢ የሆነው ጉዳይ ደግሞ፣ የፖለቲካ ድርጅቶች ደጋግመው ሲያነሱት የምናየው የውሸት መፈክር “ሕዝቡ አደራ ሠጥቶናል” “ሕዝቡ ይህንን ወይም ያንን ይፈልጋል” “ከሕዝቡ አደራ ተቀብለናል” “ይህንን አደራ ከግቡ የማድረስ ግዴታ አለብን” ወዘተ የተሰኙ ወና የሆኑ ቅጥፈቶች ናቸው፡፡ ለወደፊት የሚሆነውን አላውቅም እንጂ በዘመናዊው ያገራችን ታሪክ ውስጥ ሕዝባችን ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ አንድም ጊዜ “ወክሉኝ” ብሎ አደራ የሠጣቸው ግለሰቦችም ሆኑ የፖሊቲካ ድርጅቶች አልነበሩም፡፡ ሳያድለን ቀርቶ፣ የሶስት ሺህ ዓመት ሥልጣኔም ሆነ ለቅኝ ገዢዎች ያለመንበርከክ አኩሪ ታሪካችን ግን የፖሊቲካ ንቃታችንን በአንዲት ሴንቲሜትር እንኳ ከፍ ሊያደርግ አልቻለም፡፡ ስም ያልተገኘለት ሁላችንንም

ተጨማሪ ያንብቡ:  በእውነቱ ኢትዮጵያ መንግሥት አላትን? አማራውስ አሁን ምን ማድረግ አለበት?

 

  • ጸሃፊው ቀድሞ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባላሥልጣን የነበሩ የዓለም አቀፍ ሕግ ባላሙያ ናቸው፡፡

 

እያጠቃን ያለው በሽታ! የዚህ ጽሁፌ ዓላማ የዚህን መሆን ስለነበረበት ግን ደግሞ ስላልሆነው “የሕዝቦች አንድነት” ወይም ስለከሸፈው “የሃገረ ብሄር ምሥረታ” ሂደት ሳይሆን፣ ላለፉት ጥቂት ወራት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ራሴ በግልም ሆነ በቡድን በመካፈል ስላካሄድኳቸው የሁለትዮሽ ወይም የጋርዮሽ ውይይት፣ እንዲሁም ባጠቃላይ በየዕለቱ የታዘብኳቸውን አሳሳቢ የሆኑ አገራዊ ጉዳዮችን በተቻለኝ መጠን ገለልተኝነቴን ጠብቄ ለኤሊቱ ለማቅረብ ነበር። ኤሊቶቹም አንብበው ዝም እንዲሉ ሳይሆን፣ እየሄድንበት ያለው ጉዞ ወደ ጥፋት እንጂ ወደ ልማት የማያመራ ስለሆነ ይህንን አሳሳቢ ጉዳይ በጋራ ሆነን መፍትሄ የምናገኝበትን መንገድ ማፈላለጉ ላይ እንዲተጉ ለማሳሰብ ነበር።

 

ባገራችን ዛሬ ወደድንም ጠላን፣ ብሄር ተኮር ግጭቶች በያቅጣጫው እየተከሰቱ ነው። ለምን ተከሰቱ ለሚለው ሂሳባዊ ፎርሙላ ባይኖረኝም የተወሰኑ ምክንያቶችን አሁን ጊዜና ቦታው አይደለም እንጂ ለማቅረብ እችላለሁ። የብሄር ጥያቄን በለመለከተ በስድሳዎቹ አካባቢ በኢትዮጵያ ምሁራን ጭንቅላት ተቀርጾ ወደ ተግባር ከተመነዘረበትና እኔም እንደ ያኔው ተከታይ ትውልድ ጥያቄውን በተማሪ ማህበራት ስብሰባችን ስንነታረክበት የተካፈልኩበት ስለሆነ፣ ለጉዳዩ አዲስ አይደለሁም፡፡ አዲስ ሆኖ ያገኘሁት ግን ያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ በተለይም የደቡብን ሕዝብ በግፍ ሲገዛት የነበረው ጨቋኝ ሥርዓት የመበዝበዣ መሳርያ

 

የነበረው “መሬት” በዓዋጅ የሕዝብና የመንግሥት ከሆነ አርባ ዓመታት በኋላና፣ ከ1991 ጀምሮ ደግሞ ብሄሮች የራሳቸውን ክልል በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ ተብሎ የፌዴራሊዝም ሥርዓት ከሰፈነ በኋላ፣ ዛሬም ዜጎች “አማራ” “ኦሮሞ” “ቅማንት” “አገው” “ትግራይ” ወዘተ እያሉና የብሄር ጥያቄያችን አልተመለሰልንም ሲሉ መስማትን ነው። ዛሬ የትኛው ብሄር ሌላውን ብሄር እየጨቆነ ወይም የየትኛው ብሄር ቋንቋ ወይም ባሕል እንደ ብሄራዊ መገለጫ ሆኖ በሌሎች ላይ እንደተጫነ ማወቁ በጣም አዳግቶኛል፡፡

 

ማሕበረሰባዊ ግጭቶች እንዳይከሰቱ ለማድረግ አንችልም፡፡ የግጭቶቹን መንስዔዎች መርምሮ አጥንቶ በሠለጠነ መንገድ ችግሩን መፍታት ግን ሊሳነን ባልተገባ ነበር፡፡ ያልተማሩ አባቶቻችንና አያቶቻችን በጊዜያቸው በዘረጉት የአስተዳደርና የፍትሕ መዋቅር ተመርተው ማህበረሰባዊ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ እየፈቱ ሰላምን ማስፈን ብቻ ሳይሆን አገራችን ኢትዮጵያን ለዘመናት ዳር ድንበሯን አስከብረው ለመኖር ከቻሉ፣ እኛ ለዘመናዊ ትምህርትና እውቀት የተጋለጥን ትውልድ እንዴት የቀሰምነውን ዕውቀት በተግባር አውለን ግጭቶችን መፍታት እንዳቃተን ማወቁ ግራ የገባ ነገር ነው፡፡ ለምንድን ነው የዛሬው ኤሊት ጉድለትን ብቻ አጉልቶ በማሳየት ሕዝባችንን ለግጭት ማዘጋጀት ብቻ ላይ ያተኮረው? ሕዝባችን ከኛ የሚጠብቀው እኮ፣ ለዘመናት ያርስበት የነበረው ማረሻ፣ ሞፈር እና ቀንበርን ወደተሻለ የእርሻ መሣርያ ቀይረንላቸው ሕይወታቸው ዋጋ እንዲኖረው እንጂ፣ ሞፈርና ቀንበሩን ሰቅሎ እኛ ራሳችን ለግል ፖሊቲካ ዓላማ ለቀየስንለት “የፖሊቲካ ጥያቄ” ስኬት እርስ በርሱ እንዲዋጋ አይደለም፡፡ አዎ! ለኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን በጎ በጎውን እየተመኘን መቆርቆሩ ዜጋዊ ግዴታችን ነው፡፡ ብሄርን ከብሄር ለይቶ “ለራሴ ብሄር ብቻ” በማለት ላንዱ ወገን አድልቶ ለግጭት መቀስቀስ ግን በምድራዊውም ሆነ በሰማያዊ ሕግ ዋጋ የሚያስከፍል ይመስለኛል፡፡ ማንናችንም ወድደን ወይም ታግለን የዚህ ወይም የዚያኛው ብሄር ተወላጅ ስላልሆንን፣ የዚህ ወይም የዚያኛው ብሄር ተወላጅ መሆን አንዳችም የሚያኮራ ነገር የለበትም፡፡

 

ኦዎ! ችግሮቻችን ባብዛኛው ሰው ሠራሾች ናቸው፡፡ ሰው ሠራሽ ችግር እስከሆነ ድረስ ደግሞ መፍትሄው ያለው በኛው ችግሩን በፈጠርን ሰዎች እጅ ነው፡፡ ከዚህ ሌላ የችግራችን መፍቻ ተዓምራዊ ዘዴ የለም፡፡ ስለዚህ ወደድንም ጠላንም ከልብ አገራችንና ሕዝባችንን የምንወድና ቅንነቱና ፍላጎቱ ካለ ዘመኑ በሚፈቅደው “ሰጥቶ መቀበል” የውይይት ስልት ተመርተን ችግሮቻችንን በሰላም ለመፍታት ዛሬውኑ መጀመር አለብን፡፡ (“ችግሮቻችንን” ያልኩት ዛሬ በየክልሉ የምናስተውላቸውን ግጭቶች ፈጣሪዎቹ እኛ የተማርን ነን ባዮች ጽንፈኛና እፍኝ የማንሞላ መኃይም ምሁራን እንጂ መቶ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ሕዝብማ አማራው ከኦሮሞው፣ ትግሬው ከአፋሩ፣ ጉጂው ከጌዴዎ ጋር ተስማምተው ለዘመናት ኖረዋል)፡፡ በግሌ ዛሬ ላሉን ችግሮች መፍትሄ ይሆናሉ ብዬ የማስባቸው ፎርሙላዎች አሉኝ፣ ያ ማለት ግን የኔ ፎርሙላ ፍቱን ነው ማለቴ አይደለም፡፡ እያንዳንዳችን ያሉንን ፎርሙላዎች ይዘን ባንድ ዋርካ ሥር ተሰባስበን በቅንነት ከተወያየን ግን ዘላቂ መፍትሄ የማናገኝበት ምክንያት የለም፡፡ የሚከተሉትን የግሌን አስተያየቶችና “ምክሮች” የማቀርበው በዚሁ መንፈስ ሆኖ በትክክል ሥራ ላይ ካዋልናቸው ረጅሙን ጉዞ በመጠኑም ቢሆን ያሳጥርልናል የሚል ግምት አለኝ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሰው የዳቢሎስ ጠበቃ ከሆነ ነገር ዓለሙ ሁሉ መበላሸቱ አይቀርም - መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ 

 

ሀ) ከሁሉም በላይ፣ ነገ አብረን መኖራችን ላይቀር፣ ዛሬ “በየብሔሮቻችን ጥላ ሥር ተከልለን” እና ጽንፈኛ የሆነ አቋም ይዘን እርስ በርስ መቆሳሰሉን ማቆም አለብን፡፡ መቆሳሰል በጣም ቀላል ነው፣ ቁስልን ማዳን ግን ምናልባትም ያንድን ትውልድ ዘመን ሊጠይቅ ይችላል፡፡ አንድ ሊሠመርበት የሚገባ ጉዳይ ቢኖር፣ ዛሬ የኢትዮጵያን ሕልውና የሚፈታተን ወይም ኢትዮጵያን ለማፍረስ ፕሮግራም ያለው የፖሊቲካ ድርጅት እኔ እስከማውቀው ድረስ አንድም የለም፡፡ ያ ባይሆን ኖሮ በሕገ መንግሥቱ

 

የተካተተውንና በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ ቀላል በሆነ መንገድ መገነጣጠልን ሊያስተናግድ የሚችለውን አንቀጽ 39ን ተጠቅሞ ብዙ ድርጅቶች የመገንጠልን ጥያቄ አንስተው አገራችንን ሰማኒያ አገር አድርገዋት ነበር፡፡ ከዚያም በላይ፣ የመገንጠል ዓላማ ነበራቸው የተባሉ ድርጅቶችም ሳይቀሩ በሕገ መንግሥቱ መሠረት በሰላም መንገድ ታግለን ከሌሎች ጋር በመሆን ዲሞክራሲያዊቷን ኢትዮጵያን እንገነባለን ብለው አገር ቤት ገብተው ለሚቀጥለው ምርጫ እየተዘጋጁ ናቸው፡፡ ስለዚህ አንዳንዶቻችን ከሌሎች የበለጠ ለኢትዮጵያ አንድነት የምንቆረቆር አድርገን ራሳችንን ከፍ ከፍ ባናደርግ ጥሩ ነው፡፡ ማንም ከማንም በላይ ኢትዮጵያዊ ወይም ማንም ከማንም በላይ ኢትዮጵያን የሚወድ የለምና! የተለያየ አስተሳሰብ ማስተናገድ ደግሞ ተፈጥሮያዊ ነው፡፡ ስለዚህ “ለዘመናት አብረን የኖርን” ብለን የምንለፍፈውን ያህል፣ በተግባርም “ጽንፈኞች ከፋፍለውን ነው እንጂ ድሮም በሕዝባችን መካከል አንዳችም ልዩነት አልነበረም” ብለን በሕዝቦች መካከል የርስ በርስ ግጭትን ለመጫር ሌት ተቀን የሚተጉትን ግለሰቦችንና ቡድኖችን በጋራ ሆነን ዓላማቸውን እናክስምባቸው፡፡

 

ለ) ከሁሉም በላይ፣ ለምናደርገው የፖሊቲካ እንቅስቃሴ መነሻውና መድረሻው አሁን ያለው ሕገ መንግሥት መሆኑን ጠንቅቀን ማወቅ አለብን፡፡ “ሕገ መንግሥቱ ሕዝባዊ ስላልሆነ አይመለክተንም” ማለት የትም አያደርስም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ በዘመናዊ ታሪኩ ውስጥ የራሱ የሆነ ሕገ መንግሥት ኖሮት አያውቅም፡፡ ለዚህም ነው “ሕገ ሕዝብ” ሳይሆን “ሕገ መንግሥት” የተባለው! ሕገ መንግሥቱ ብዙ የማይጥሙን ግን ደግሞ በቅንነት ከተወያየንባቸው በቀላሉ ሊሻሻሉ የሚችሉ ብዙ አንቀጾችን አቅፏል፡፡

 

  • ደግሞ ዕውን ሊሆን የሚችለው ከሚቀጥለው ዲሞክራሲያዊ ምርጫ በኋላ ተወካዮቻችን ተወያይተውበት ለውሳኔ በሚያቀርቡልን ረቂቅ ሕገ መንግሥት ላይ ተነጋግረንበት ስንመኘው የኖርነውን እውነተኛውን ሕገ ሕዝብ ስናስጸድቅ ብቻ ስለሆነ ዛሬውኑ ሕገ መንግሥቱ ካልተቀየረ በሚል ቅስቀሳ ጊዜ ማጥፋቱን ትተን የሚቀጥለው ምርጫ ነጻና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን በጋራ መሥራት ነው፡፡

 

ሐ) ምርጫው ከስድስት ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ እንደሚካሄድ መንግሥት አስታውቋል፡፡ ብዙዎቹ የፖሊቲካ ድርጅቶች ለብሔራዊ ምርጫ አዲስ ስላልሆኑ የቀረው ጊዜ ለዝግጅቱ የሚያንሳቸው አይመስለኝም፡፡ ለመስኩ አዲስ የሆኑ ፓርቲዎችም “ከለማዳዎቹ” ተሞክሮ በጎ በጎውን ተምረው ለምርጫው ለመዘጋጀት የሚችሉ ይመስለኛል፡፡ አንድ መረዳት ያለብንና በቅድሚያ ራሳችንን ማዘጋጀት ያለብን ጉዳይ፣ ምርጫው ያላንዳች አድልዖና ተጽዕኖ እስከተካሄደ ድረስ የምርጫውን ውጤት ለመቀበል ዝግጁ መሆን አለብን፡፡ ባገራችን ዘወትር ሲነገር የምንሰማው፣ በምርጫ መወዳደር ማለት ወይ ማሸነፍ አለያም መሸነፍ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ ይህ እጅግ በጣም የተሳሳተ ግምት ነው፡፡ ምርጫው ነጻና ዲሞክራሲያዊ እስከ ሆነ ድረስ በምርጫ ውጤት አናሳ ድምጽ ያገኘው የፖሊቲካ ፓርቲ ከሌላው ጋር ግንባር ፈጥሮ መንግሥት ሊመሠርት የሚችልበት ሁኔታም ሊፈጠር ይችላል፡፡ በተፈጥሮያቸው ሊቀራረቡ አይችሉም ብለን የምንገምታቸው ፓርቲዎችም “በሰጥቶ መቀበል” መሪህ መሠረት የጋራ ግንባር ፈጥረው መንግሥት ሊመሠርቱ ይችላሉ፡፡ ምርጫው ነጻና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን ደግሞ መንግሥት ብቻ ሳይሆን እያንዳንዳችንም እንደ ዜጋ መጫወት ያለብን ሚና አለን፡፡ በየክልሉ በዞንና በየወረዳው ምርጫውን እንዲታዘቡ ብቻ ሳይሆን የምርጫን ሂደት ጠንቅቆ የሚረዳና ድምጽንም ኮረጆ ውስጥ መክተት ብቻ ሳይሆን ከኮረጆውም “ተንኖ” እንዳይጠፋ ዘብ መቆም የሚችል ንቁ ዜጋ ለመፍጠር መቻል የያንዳንዳችን የቤት ሥራ መሆን አለበት፡፡

 

መ) የፖሊቲካ ፓርቲዎችን በተመለከተ፣ እስከ ዛሬ ድረስ፣ አንዳቸው ከሌላውና ዛሬ ሥልጣን ላይ ካለው መንግሥት ምን የተሻለ ወይም የተለየ የትምሕርት፣ የኤኮኖሚ፣ የመከላከያ፣ የጤናና ወጣቱን ሥራ የማስያዝ ወዘተ የመሳሰሉት ፕሮግራም እንዳላቸው የነገሩን ነገር የለም፡፡ በኔ ግምት፣ እነዚህ ፓርቲዎች፣ አገር አቀፍ በሆኑ ማህበራዊና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን አቋምና ከዓቢይ መንግሥትና ከእርስ በርሳቸውም የሚለያዩበትንና የተሻለ ነው ብለው የሚያምኑበትን ፕሮግራማቸውን ዛሬውኑ ለሕዝብ አቅርበው የማሳመኛ ቅስቀሳ ማድረግ ወቅቱ አሁን ይመስለኛል፡፡ በፕሮግራማቸው ይህን ያህል የሚለያያቸው ከሌለ ደግሞ አንዱ ባንደኛው ውስጥ የማይቀልጡበት ምክንያት የለም፡፡ አለበለዚያ ግን ሁላቸውም ከተለያየ አቅጣጫ ዝም ብሎ የማይዳሰስና የማይጨበጥ ግን ደግሞ ስሜትን ለመቀሰቀስ የሚረዳ “ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማስፈን” የሚል አንድ ዓይነት መፈክር ብቻ በማሰማት ሕዝቡን ማማለል ትርፍ አይኖረውም፡፡ ስለዚህ ያላቸውን አጄንዳ እና እኛም የዓቢይን መንግሥት ትተን እነሱን እንዲመርጥ የሚያሳምኑበትን አገር አቀፍ ፕሮግራም ዛሬውኑ አቅርበው እኛን ማወያየት አለባቸው፡፡ ከመንግሥት የተሻለ ፕሮግራም ከሌላቸው ደግሞ፣ በምርጫ ሰበብ የሕዝብን ኃብትና ጊዜ ከማቃጠል፣ አንደኛውኑ ከመንግሥት ጋር ቢወግኑ፣ ከብዙ ጣጣ እንድናለን ባይ ነኝ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ለዶ/ር መስፍን አረጋ “ዮናስ ብሩ፤ የጭራቅ አህመድ አዛኝ ቅቤ አንጓች” በማለት ለሰጠው ዘለፋ የቀረበ ሳይንሳዊ ትችት! - ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)

ሠ) ፖሊቲካ ጥበብ ነው፡፡ በፖሊቲካ ዓለም ተፎካካሪ እንጂ ጠላት የሌለውን ያህል ቋሚ ጠላት ወይም ወዳጅም የለም፡፡ ሁሉም እንደ ሁኔታው ሊቀያየር ይችላል፡፡ ቋሚ ጠላት እስከሌለ ድረስ ደግሞ፣ “ይህኛውን ሃሳብ ከሚያራምደው ተፎካካሪ ጋር አልደራደርም” “በፌዴራሊዝም አንደራደርም” “ከጽንፈኞች ጋር አንደራደርም” ብሎ ቅድመ ሁኔታዎችን ማስቀመጥ ለችግሮቻችን ማባባሻ እንጂ መቅረፍያ አይሆኑም፡፡ ላንዲት አገር የሚመጥን “ብቸኛና አማራጭ የሌለው” ብሎ ፕሮግራም ነገር የለም፡፡ ዋናው እና ወሳኙ እያንዳንዱ የፖሊቲካ ድርጅት ላገሪቷ ተስማሚ ነው ብሎ የሚያምንበትን ፕሮግራም ለሕዝብ አቅርቦ እንዲመርጡት ሰላማዊ በሆነ መንገድ መቀስቀስ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ግን፣ እኔ ያዘጋጀሁት ፕሮግራም ብቻ ትክክለኛ ስለሆነ ሌላው ሁሉ ላገራችን አይጠቅምምና የተፎካካሪው ፓርቲ ሃሳብ ብቻ ሳይሆን ሃሳቡንም ያፈለቁ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች መገለል አለባቸው ብሎ መቀስቀስ የፖሊቲካን ሀሁ አለማወቅ ነው፡፡ የፖሊቲካ ድርጅቶቻችን ጠንቅቀው ማወቅ ያለባቸው ዋነኛው የፖለቲካ ዕውቀት መገለጫ ምልክት የሆነውን “የሰጥቶ መቀበልን” ጥበብ ጠንቅቆ ማወቅ ነው፡፡ ባልና ሚስት ትዳር መሥርተው ብልኮ ተጋፍፈው ልጆች አፍርተው የሚኖሩት በመካከላቸው የማያግባባቸው ነገር ስላልኖረና ሁሉም ነገር አልጋ በአልጋ ሆኖ ሳይሆን፣ “በሰጥቶ መቀበል መሪህ መሠረት” በሚያግባባቸው ጉዳዮች ላይ ጠንካራ መሠረት እያኖሩ በማያግባባቸው ላይ ደግሞ አንደኛው የሌላውን ፍላጎት ተረድቶ ላለመስማማት ተስማማተው ነው፡፡ ያ ባይሆን ኖሮ ተከታታይ ትውልድ፣ ማህበረሰብና አገርም አይኖርም ነበር፡፡ ስለዚህ የተፎካካሪን ሃሳብ በመጥፎ ዓይን አትዩት ማለቴ ነው፡፡ ለማንኛውም፣ እናንተ እኮ ሕዝብን ወክላችሁ ይህኛው ሃሳብ ከዚያኛው ለሕዝቡ ይጠቅማል ብሎ የመወሰን መብት ያላችሁ አይመስለኝም፡፡ ሕዝቡም ለዚህ ማንዴት አልሰጣችሁም፡፡ የናንተ ሚና መሆን ያለበት፣ ሕዝቡ ባቀረባችሁለት ፕሮግራም ላይ በነጻ ተወያይቶበት የሚበጀውን ለመምረጥ የሚችልበትን ነጻና ዲሞክራሲያዊ መድረክ ማመቻቸት ብቻ ነው፡፡

 

ስለዚህ ወገኖቼ፣ ሌላ በድብቅ የምታስተናግዱት አገሪቷን የመበታተን ዓላማ ከሌላችሁና ባንዲት ኢትዮጵያ በምትባል አገር ውስጥ በሰላም ተከባብረን አብረን እንድንኖር የምትመኙና ለዚያም የምትተጉ ከሆነ፣ ከላይ ያስቀመጥኳቸውን ወንድማዊ ምክሮቼን በተግባር ለማዋል ሞክሩ፡፡ የምንታገለው “ለአንዲት ዲሞክራሲያዊት አገር” እና “በማንነቱ ኮርቶ ከሌላው ጋር በእኩልነት ለሚኖር ሕዝብ” ከሆነ፣ ሁላችንም በእኩልነት ደረጃ ቁጭ ብለን ከመወያየት ሌላ አማራጭ የለንምና በጥብቅ አስቡበት፡፡ አገር ማለት ግዑዙ አፈር ሳይሆን በላዩ ላይ የሚኖሩ ሕዝቦች ማለት ስለሆነ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝቦች አንድነት ሳይሆን ለኢትዮጵያ የግዛት አንድነት እታገላለሁ ማለቱን ትተን የሕዝባችንን ጥቅም እናስቀድም! እናት ኢትዮጵያም አፍ ቢኖራትና ብትናገር ኖሮ፣ ሁሉንም ልጆቿን እኩል እንደምትወደንና ተቻችለን እንድንኖር በአንክሮ ትመክረን ነበር እንጂ አንዳችንን ከሌላው ለይቼ እወደዋለሁ የሚል ቃል አይወጣትም ነበር፡፡ ስለዚህ በትናንቱ መንጋጋ የዛሬውን ቋንጣ ማኘክ ትተን፣ የየግላችንን አስተሳሰቦች እያስተናገድን ግን ደግሞ በጋራ ሆነን ሕዝባችንን ዛሬ ካለበት የድህነት መቀመቅ አውጥተን ሰላም በሠፈነበት አገር ውስጥ ቢያንስ ቢያንስ በቀን አንድ ጊዜ ጠግቦ ሊበላ የሚችልበትን አገር ለመፍጠር እንድንችል መትጋት የቅንጦት ሳይሆን የዜግነት ግዴታችን መሆኑን ማወቅ ዋነኛው የቤት ሥራችን መሆን አለበት ባይ ነኝ፡፡ ይህንን የቤት ሥራችን በትክክል ከሠራን ፈጣሪም ተባብሮን ባገራችን ሰላምን ያሰፍናል ባይ ነኝ፡፡ በቸር ይግጠመን፡፡

*****

wakwoya2016@gmail.com

Geneva, 10 January, 2020

 

4 Comments

  1. Wakoya: Why do you hate diaspora Ethiopians so much? I was surprised that you failed to mention the criminal activities of your cousin joy-war in your long diatribe against the Amhara people.
    You claim to be an expert in international law but barely mentioned the kidnapping of Amhara girls by your cousins, the OLF shiftas-the former goat herders of Esayas Afeworki.

    Again, being an expert of international law, how do you talk about election in a country where people feel unsafe even to leave Addis let alone participating in a free and fair election. Your cousins make sure that the more than 15 million non-oromo Ethiopians living in “oromia” do not elect or get elected.

    Stop the pretense!!!

  2. ይህን ፅሁፍ ሰፋ ላለ ውይይት እንደ መንደርደሪያነት አቅርበውት ካልሆነ በሰተቀር በራሱ ብዙ የተሸፋፈነ ነገር ይታይበታል፡፡ ግልፅ ሆነን መወያየት ያለመቻላችን እየታወቀ በተፃፃሪ ጎራ ተሰልፈው ያሉ ተወያይተው መግባባት ላይ መድረስ አለባቸው የሚሉት አባባሎች ጧት ማታ ሕብረተሰቡን ከማደንቆር አልፈው እያሰላቹ የመጡ ናቸው፡፡ የመጀመሪያው ስሕተት መስሎ የሚታየኝ አገራችን ያለችበትን ሁኔታ በአግባቡ ያለመለየት ሲሆን ሁለተኛው የፖለቲካ ፓርቲ ትርጉሙንና አስፈላጊነቱ ያለማጤን ይሰማኛል፡፡

    አሁን አገራችን ያለችበት ሁኔታ ምን ይመስላል ለሚለው በእኔ አመለካከት፡ከዚህ መንግስት በፊት በነበረው መንግስት ለዘረፋ በሚያመቸው መልኩ ከተራ ቀበሌ አስተዳደር ጀምሮ እስከ ፓርላማ ያስቀመጣቸው ህሊናቢስ ተላላኪዎች የሚበዙበት ነው፡፡ አሁንም እነዚህኑ ተለላኪዎች ከቦታ ቦታ ከመቀያየር በስተቀር የተለየ ለውጥ ሲደረግ አልታየም ፡፡ በተጨማሪ በአሁኑ ጊዜ አገሪቱ ከቀድሞ በባሰ በከፋ የኢኮኖሚና ሶሻል ቀውስ ላይ እንድትገኝ ካደረጓት ምክንያቶች ቀድሞ የተጀመረው ቅጥ ያጣ ዘረፋና በእነዚሁ በፖለቲካ አዋቂነት ስም የቀጠለው የማወናበድ ዘመቻ ማቆሚያ ማጣቱ ነው፡፡ የፖሊቲካ ፓርቲን ትርጉምና አስፈላጊነት በተመለከተ፡ለመሆኑ በእኛም ሆነ በሰለጠነው አለም የፖለቲካ ፓርቲዎች አንድ ወይም ተመሳሳይ አቋም/ፕሮግራም (ያውም በድርድር) ኖሯቸው ለውድድር ቀርበው ያውቃሉን? ወጥ የሆነ አቋም ካለቸው ለምን መወደዳር አስፈለጋቸው?

    በአጠቃላይ አገራችን ላለችበትም ሁኔታም ሆነ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ለሚታየው ልዩነት በየትኛውም ዓለም እንደሚደረገው መፍትሔውና እውነተኛው ዳኛ የሕዝብ ድምፅ ነው፡፡ ይህም በሁሉም ወገን ምርጫው በጊዜው እንዲካሄድ በማድረግ ለምሳሌ፡
    – ቢያንስ ሕዝቡ በምርጫው በተመራጭ ስም በላዩ ላይ ተጭነው ያሉትን ዘራፊዎችና ተላለኪዎቻቸውን በሌሎች በሚያምንባቸው ዜጎች የመተካት ዕድል ይኖረዋል፡፡ ያለው መንግስት ምርጫውን ያጭበረብራል ወይም በብቃት ማካሄድ አይቸልም በሚል ምክንያት እነዚህን ዘራፊዎች ተሸክሞ መኖር ያለበት አይመስለኝም፡፡ ባይሆን ምርጫው ቢጭበረበር ሕዝቡ ለትክክለኛ ዲሞክራሲና ለፍትሕ የሚያደርገውን ትግል የበለጠ ያጠናክረዋል፡፡
    – ቢያንስ ምርጫው በጊዜው ቢካሄድ በምርጫው የተሰሩ ስሕተቶች ቢኖሩ በጊዜው ለማረምና በሕዝቡ የተመረጡት ፓርቲዎች እንዴት መንግስት መመስረት እንደሚችሉ ረጋ ባለ መንፈስ ተወያይተው መግባባት ላይ ለመድረስ በቂ ጊዜ የሚሰጣቸው ይሆናል፡፡ በሕዝብ የተመረጡ በመሆናቸው (በአምባገነኖች የሚታየው ስግብግብነትና ከዚህ የሚመነጨው ቀና ያልሆነ መንፈስ ስለማያጠቃቸው) ተነጋግረው መግባባት ላይ መድረስ አያቅታቸውም፡፡ እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት በአገር ደረጃ ብቻ ሳይሆን በክልሎችም ልዩነቶች ያሉ በመሆናቸው ከልዩነት የፀዳ ክልል ይኖራል ብሎ መገመት አይቻልም፡፡ ስለዚህ ሕብረተሰቡ በሚከፋፍሉት ቀማኞች ተወክሎ ሳይሆን በእውነተኛ ወኪሎች አማካይነት ችግሮችን በጋራ ሆኖ በቀላሉ የመፍታት ዕድል ይኖረዋል፡፡
    – ምርጫው ለምሳሌ ነሐሴ ላይ ወይም ከዚያም በኋላ ይካሄድ ቢባል ከላይ ለተጠቀሱት ጉዳዮች የጊዜ መጣበቦች ከመፍጠር በተጨማሪ የነበረው ፓርላማ ከሕጉ ውጪ (ምርጫ ቦርድ ቆጠራውን አጠናቆ ችግሮችን ፈቶና አሸናፊዎቹ የፖለቲካ ፓረቲዎች ተደራድረው አስኪስማሙ) ያለ ጊዜ ገደብ ለሌላ ተጨማሪ ጊዜ ይቆያል ማለት ነው፡፡ ይህም በአገሪቱ ተንሰራፍተው ላሉት ቀማኞች ሌላ የትርምስ መፍጠሪያ ጊዜ ይፈጥርላቸዋል ማለት ነው፡፡

  3. ወንድሜ ባይሣ – የሃገሪቱ ችግር በየዘመናቱ እናውቅላችሁሃለን በማለት በዘር ሃረግም ሆነ በጠበንጃ ሃይል ራሳቸውን በሚኒሊክ ቤ/መንግስት ያስጠለሉ ሃይሎችና ፍርፋሪ ለቃሚዎች ናቸው። ቀልደኛው እንዳለው ነው። ቤ/መንግሥት ለመጎብኘት 200 ብር ብቻ ነው ቢሉት እዛው ለመቅረት ስንት ነው እንዳለው አይነት። አማራ፤ ትግሬ፤ ኦሮሞ ወይም ሌሎችን የሃገሪቱን ስፍር ቁጥር የሌላቸው ብሄረሰብ መሆን ብቻውን የነጻነት ምልክት አይደለም። ራሳችው ነጻ ሳይወጡ ሌላውን ነጻ እናወጣለን የሚሉ ሾተላዪች እንደ ጉንዳን የፈላባት ሃገር ናት። አሁን ማን ይሙት የትግራይ ህዝብ ነጻ ህዝብ ነው? ቅኝ ግዛት ነበርኩ በማለት እልፍ ሰው አስጨርሶ አሁን አስመራ ላይ አለቃ የሆነው አቶ ኢሳያስ ለኤርትራ ህዝብ ነጻነት አምጥቷል? ለዘመናት በኦሮሞ ህዝብ ስም በውጭና በሃገር ውስጥ በስሙ ሲነግድ የነበሩ የፓለቲካ ወሮበሎች ለኦሮሞ ህዝብ ይገዳቸዋል? ለአማራ ህዝብ ነጻነትና አንድነት ቆመናል የሚሉት ወስላቶች የአማራን ህዝብ ከጥቃት ይመክታሉ? ግን የፓለቲካ ውስልትና ማቆሚያ የለውም። ሁሌም ደንበር ገተር ነው። የአስረሽ ምቺው ፓለቲካ!
    አንድ ህንዳዊ ስለሃገሩ ስንጫወት ትልቁ ዲሞክራሲ ያለባት ሃገር አለኝና እስቲ ይህን ያልክበትን ሶስት ነጥቦች ንገረኝ ስለው ለሁልጊዜው ለፍልፎ የማይጠግበው መልስ ጠፍቶት ዝም አለ። በመሰረቱ (Caste system untouchables) 200 ሚሊዪን ህዝብን እንደ ጉድፍ እያየ ስለዲሞክራሲ ማውራት አይችልም። በምድራችን ላይ ፍጽም ዲሞክራሲ የለም። ዲሞክራሲ መሰል ስርዓቶች ግን ይታያሉ። እናማ በሺህ ጉዳዮች ተወጥራ በተያዘችው ከቁራሽ ትራፊ ሃገር ዲሞክራሲና ሰላም ይሰፍናል ብሎ ማመን ቂልነት ነው። በዚያች ሃገር ወንጀል የሚሰራው መንግስት ብቻ ሳይሆን ህዝብም ነው። በቅርቡ በደረሰኝ መረጃ መሰረት ከአማራ ክልል በተለይም ከባህርዳርና ከአካባቢዋ ሴቶች እየታፈኑ ይደፈራሉ፤ ለሱዳን፤ ለአረብ፤ ለሌሎች በሃገር ውስጥ ላሉ ባለሃብቶች ይሸጣሉ። በሃገሪቱ ታሪክ ተስመቶና ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ዘር እየተመረጠ የሽያጭ ዋጋው ከፍና ዝቅ ይላል። በዘርና በቋንቋ እንዲሁም በክልል በተሰመረቸው ሃገር ላይ ሰዎች ሰርተው የመግባትና በሰላም የመኖር ዋስትናቸውን ከተነፈጉ ቆየ። በመዲናይቱ በአዲስ አበባ ሰራቂው የቆመው ብቻ ሳይሆን አፈር የተመለሰበትም በተወካዮቻቸው ጭምር ነው። ከመቃበር ሆኖ ምዝበራ ይሉሃል ይህ ነው። የሃሰት ደረሰኝ ይሰራል፤ የትምህርት መረጃ ይሰጣል፤ የክስ ወረቀት ይቀርባል፤ የሌለ እዳ የቤቱ አባወራ ከሞተ በህዋላ አለ በመባል ቀሪ ሃብቱን ይቀራመታሉ። የሃገሪቱ ባንኮች ሳይቀሩ የውሸት እዳ ቅጽ በማዘጋጀት የተበደረው ገንዘብ አለ ክፈይ በማለት ሚስትን ያለምንም ነገር የሚያስቀሩ አረመኔዎች ያፈራች ምድር ናት።
    በወለጋ ለሰላም ተጠርተው ኦነግ ሸኔና ሌላም የተናጠል ስም እያወጡ ህዝቡን ሲገሉና ሲዘርፉ ድሮስ ቢሆን ለኦሮሞ ህዝብ መቼ ቆሙና ለሆዳቸው እንጂ ያስብላል። ልክ እንደ አክራሪ እስላሞች አሰራር ተማሪዎችን በመጥለፍ ለፍትወተ ስጋ ጥቅምና እንግልት የሚዳርጉ እነዚህ አውሬዎች ከሰው ተራ አይመደቡም። በጎንደር በቅማንትና በአማራ መካከል ፍልሚያው ጦፏል። በሌሎችም የሃገሪቱ ክፍሎችም ጤና የለም። በትግራይ አኩራፊው ሃይል 27 ዓመት ሃገሪቱን ለመከራ የዳረጋት አልበቃ ብሎ አንዴ እገነጠላለሁ፤ ሌላ ጊዜ የፓለቲካ ውህደት አልጣፈጠኝም ወዘተ.. እያለ በቀጥታና በእጅ አዙር የዶ/ር አብይ መንግስትን ለማዳከም እየሰራ እንደሆነ ግልጽ ነው። አሁን ዘጥ ዘጥ የሚባልበት የኤርትራውም የሰላም እርቅ ያው ለኤርትራዊያን እንጂ ለቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ ጥቅም የለውም። የሃገሬ ሰው ደስ ይለኛል በተረቱ ” ሲለዪ ምንጥቅ፤ ሲኖሩ ልጥቅ” ይላል። ትላንት ሻቢያን እስከ አፍንጫው አስታጥቀው ሂድ በለው ያሉት አረቦች ጥቂቶች ሃገር መሆናቸው እየቀረ፤ ሌሎች ደግሞ ተቧድነው ዛሬ የኤርትራን ሰላም ለመንፈግ በሱዳን በኩል ሴራ ላይ እንደሆኑ ግልጽ ነው። ቱርክ ሶማሊያ ውስጥ ምን ትሰራለች? ቱርክ ሱዳን ውስጥ ምን እያረገች ነው። ቱርኮች ሊቢያ ላይ ሰላም ለማምጣት ነው የገቡት? አለማችን ተመሳቅላለች። በዚህ ላይ አል ሲሲ የህዳሴውን ግድብ ለማቡነን የትራምፕን አረንጓዴ ምልክት እየጠበቁ እንደሆነ ጠቋሚ ምልክቶች አሉ። ግራም ነፈሰ ቀኝ ሰላም ለኢትዮጵያ ላም አለኝ በሰማይ ከሆነ ዘመን ተቆጥሯል። አሁን እንደ አሸን የፈሉት የፓለቲካ ድርጅቶችም በዘርና በቋንቋ ዙሪያ የተሰለፉ በመሆናቸው ለሃገር አንድነትና ሰላም የሚያመጡት ፋይዳ የለም። ኢትዮጵያ እንደ ገና ኢትዮጵያ የመሆን እጣ ፈንታዋ ከተነነ ቆይቷል። በአንዲት ሃገር ውስጥ በአስተርጓሚ ብቻ ሰው የሚግባባት ሃገር ለአንድነት የቆመን አፍርሶ የሚከፋፍል ነገር ብቻ በአንድ ጀምበር በቅሎ በሚታይባት ሃገር ሰላም ሰላም ቢሉት የትም አይመጣም። ዝም ብሎ መዳከር ብቻ ነው። ኦሮሞ አማራን ሲከስ፤ አማራው ኦሮሞን ሲወነጅል፤ ትግሬው እኔ ብቻ ነኝ መግዛት ያለብኝ ሲል፤ አፋሩ ከሱማሌ ጋር ሲፋለም፤ አናሳው ብሄር እኔም ሃገርና ክልል ልሆን ሲል ይህ የእብዶች ሃገር እንጂ የሰላም ሃገር እንዳልሆነ ደንቆሮና ድዳ ይረዳል። ኦሮሞ የቁጥር የበላይነት ስላለው ሃገሪቱን ማስተዳደር ያለበት ከዚያው የሚወጣ ብቻ ነው ማለትም ጨርቅ ማውለቅ ነው። መሆን ያለበት ከየትም ይምጣ ከየትም ሃገርን እንዴት ይመራል እንጂ ዘሩና ቋንቋ ከየት ነው የሚል ህዝብ ራሱን ለመከራ ይዳርጋል። መከራውም አያባራም። ባጭሩ አሁን ያለው የፓለቲካ ስልት የደቡብ አፍሪቃውን የአፓርታይድ አሰራር መሰረት ያደረገ ነው። የሙታን ፓለቲካ! እንዳሻችሁ ጻፉ፤ ዝፈኑ፤ አቅራሩ፤ ሸልሉ እንደ እንቁራሪት አንድ ሲጮህ ሌላው ተከትሎ በሚጮህበት ምድር ሰላምና ዲሞክራሲ ሊኖር አይችልም። ዝንተ ዓለም እያለቀሱ መኖር ይሉሃል እሱ ነው። የተማረ ይግደለኝ ይል የለ የሃገራችን ህዝብ እኮ የተማረ አደል ሃገሪቱን እያፈረሰ ያለው። የተመኙት አይቀርም ይሉሃል እንዲህ ነው። ድንቄም ትምህርት!

  4. በአገር መከላከያ ሰራዊት የተፈጠረው ከፍተኛ አለመግባባት መንስኤዎች ይፋ ወጡ::

    January 14, 2020 – Konjit Sitotaw — Comments ↓

    በአገር መከላከያ ሰራዊት የተፈጠረው ከፍተኛ አለመግባባት መንስኤዎች ይፋ ወጡ (ቪዲዮውን ከታች ያገኙታል)

    360 ሚድያ ላይ በመከላከያ ሰራዊት የአገርን ጥቅም የሚጎዳ ተግባር እየተፈፀመ እንዳለ ጥልቅና በበቂ ሰነድ የተደገፈ መረጃ እንደደረሰው ዘግቧል፡፡ መሰረታዊ የአገርን ደህንነት ሊጎዱ የሚችሉ መረጃዎችን ከመግለፅ የተቆጠበው ሚድያው በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ለተፈጠረው አለመግባባት ምክንያቶች ናቸው ያላቸውን ዘርዝሯል፡፡

    ከምክንያቶቹ መካከል፡-

    1. በአሁኑ ጊዜ በመከላከለያ ውስጥ በከፍተኛም ሆነ በመካከለኛ አመራር ውስጥ በጣም ከፍተኛ የሆነ አለመግባባትና ግብግብ እንዲፈጠር ምክንያት የሆነው አንዱና መሰረታዊ ነገር የዓረቦች ጣልቃገብነት ነው፡፡ ጣልቃገብነቱ በመከላከያ ውስጥ ከፍተኛ ክርክር አስነስቷል፡፡ የመከላከያ አመራሮች ዓረቦች በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ እያሳዩት ያለው ጣልቃገብነት የአገሪቱ ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ነው፡፡ ስለዚ ይሄ ነገር ሊታረም ይገቧል በሚል ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር እንዲሁም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸሟቸው ሌሎች የመከላከያ አመራሮችም ከፍተኛ ንትርክና ግብግብ ተፈጥሯል፡፡ የተወሰኑ ማሳያዎች ለመጥቀስ ያህል ጀነራል ሰዓረ መኮነን ከመገደላቸው ከ15 ቀናት በፊት ስልጣናቸውን እንዲያስረክቡ ውሳኔ ላይ ተደርሶ የጀነራል ሰዓረን ቦታ በመተካት ስልጣን የሚይዘው ጀነራል አደም እንዲሆን ተወስኖ ነበር፡፡ ጀነራል አደምም ከደህንነት መስሪያቤት እንደሚነሳ ተነግሮት ኃላፊነቱን ሲያስረክብ ነበር፡፡ ሲጠየቅ ደግሞ ይል የነበረው “የሰዓረን ቦታ ልተካ ነው” የሚል ነበር፡፡ አንድ ግዜ አንስተነው የነበረው ጥያቄ ጀነራል ሰዓረ ከመሞታቸው ከ15 ቀናት በፊት ከስልጣናቸው ተነስተው ጀነራል አደም ይተካ ከነበረ ጀነራል ሰዓረ የሚነሱበት ምክንያት ምን ነበረ? ከስልጣን ከተነሱ በኋላስ ምንድነው የሚደረጉት? እንደተደረገው ተገድለው ነው ዞር የሚደረጉት ወይስ ሌላ የተዘጋጀላቸው ኃላፊነት አለ? የሚል ጥያቄ ነበር፡፡ አሁን ግዜው እየገፋ ስለመጣ አንዳንድ ምልክቶች ወደ አደባባይ መጥተዋል፡፡

    2. አሁን ዓረቦች በተጨባጭ እያደረጉት ያሉት የመከላከያ ቤዝ ለመገንባት የገንዘብ ከማዘጋጀት ጀምሮ እስከ መዋቅሩ ድረስ ይሳተፋሉ፡፡ ልክ እንደ ፔንታጎን ሁሉንም ለመቆጣጠር የሚያስችላቸው የመከላከያ ተቋም ለመገንባት ነው ያቀዱት፡፡ ስለዚህ እዛ የመገናኛ አውታሮች ሊዘረጉ ነው፤ የመሰለያ መዋቅሮች ሊዘረጉ ነው፤ የአገሪቱ ምስጢር የሚገኝበት ክፍል ሊገነባ ነው፡፡ ይህንን ስራ ዓረቦች ሙሉ ኃላፊነት ወስደው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቤተ-መንግስቱን ለማሳደስ በሚል እድል እንደሰጡዋቸው ሁሉ የመከላከያ ቤዝም ለዓረቦች ሊሰጡ ሲሉ ጀነራል ሰዓረ “ይሄ ነገር የአገርን ብሄራዊ ጥቅም የሚጎዳ ነው፣ ህልውናን አደጋ ላይ የሚጥል ነው፣ የትም አለም የመከላከያ ቤዝ ለተለየ ብሄራዊ ጥቅም ላላቸው አገራት አይሰጥም፣ ይሄ ቁልፍ የሚስጥር ጉዳይ ነው፣ የአገሪቱ ህልውና ጉዳይ ነው” ብለው ጀነራል ሰዓረ ተቃውሟቸውን አሰምተው ነበር፡፡ ከዛ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በሰጡት ትእዛዝ ተጀምሮ የነበረው እንቅስቃሴ ጀነራል ሰዓረ “ከኃላፊነቴን ለቅቄ ኢትዮጵያ አደጋ ውስጥ ወድቃለች ብየ ለኢትዮጵያ ህዝብ እናገራለሁ” የሚል አቋም ይይዛሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደግሞ ይህንን ነገር በጀነራል ብርሃኑ ጁላ ለማስፈፀም ሞክረው ግብግቡ ሲጠናከር ነገር እንዲቆም ተደረገ፡፡ ይሄ ነገር ቆሞ የአማራ ክልል ባለስልጣናት በተገደሉበት ጊዜ ጀነራል ሰዓረም ተገደሉ፡፡.

    ► መረጃ ፎረም – JOIN US

    በኦሮሚያ ክልል የሚኖሩ የአማራ ተወላጆችን አፈናቅላል፣

    http

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share