ማንቸስተር ዩናይትድ የኒውካስል ዩናይትድን የግራ መስመር ተከላካይ ሆዜ ኤንሪኬን ለማስፈረም ከሊቨርፑል ጋር ትግል ለማድረግ ቆርጧል፡፡ የሜርሲሳይዱ ክለብ ደጋፊዎች አሰልጣኝ ኬኒ ዳልግሊሽ ስፔናዊውን ተጨዋች እንደሚያስፈርመው እርግጠኛ ሆነዋል፡፡ ሆኖም ሰር አሌክስ ፈርጉሰንም ወደ አንፊልድ ያቀናል የሚለውን ዘገባ ያስተባበለውን ተጨዋች እየተከታተሉት ይገኛሉ፡፡ ባየር ሙኒክም 15 ሚሊዮን ፓውንድ የተገመተውን የ25 ዓመቱን ኤንሪኬ በቻምፒየንስ ሊግ የሚያሳትፈውን ዕድል እንደሚያቀርብለት ገልፆለታል፡፡ ኤሲ ሚላኖችም ኒውካስል በ2007 ከቪያሪያል ላይ በ6.3 ሚሊዮን ፓውንድ ያስፈረመው ተጨዋች አድናቂ ናቸው፡፡ ምንም እንኳን የ30 ዓመቱ ፓትሪስ ኤቭራ በኦልድ ትራፎርድ የሚቆየውን አዲስ ኮንትራት ቢፈርምም ፈርጉሰን በኤንሪኬ ላይ ያላቸው ፍላጎት አልቀነሰም፡፡ የኒውካስሉ አሰልጣኝ አለን ፓርዴው ግን ከክለቡ ጋር ተጨማሪ የአንድ ዓመት ኮንትራት የሚኖረው ተጨዋች በሴንት ጀምስ ፓርክ እንደሚቆይ ገልፀዋል፡፡ ይሁን እንጂ እንደ ፒፕል ዘገባ ተጨዋቹን ከአሁኑ እንደሚያጡት በመፍራት ለፈረንሳይ ከ21 ዓመት በታች የሚጫወተውን የ22 ዓመቱን የቱሉዝ ተከላካይ ሼይክ ምዜንጉዋን በተተኪ እጩነት ይዘውታል፡፡
ዩናይትድ ኤንሪኬን ፈልጎታል
Latest from Blog
የእስክንድር የባልደራስ ፖለቲካ ልምድ ለፋኖ የህልዉና ትግል መቅሰፍት ነዉ!!
አንተነህ ሽፈራዉ (ኢ/ር) October 15, 2024 መርህ አልባዉ እክንድር ነጋ ወደ ማኅበራዊ ሚዲያ ብቅ ባለ ቁጥር በአማራ ሕዝብ የህልዉና ትግል (ፋኖ) አመራሮች ላይ እጅግ በጣም መርዛማ የሆኑ ስም የማጥፋት ዘመቻዉን አጠናክሮ የቀጠለበት
“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት
በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ
መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ
የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ። ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ
አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ
ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ
ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ
በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ