August 28, 2024
3 mins read

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን አሚኮን በምክትል ስራ አስፈፃሚነት የሚመራው የብልፅግናው ሹም በቁጥጥር ስር ዋሉ

Amhara Media Amicoየፋኖ ብርቱ እንቅስቃሴ ደግሞ በአማራ ህዝብ ገንዘብ ተቋቁሞ የብልፅግናውን መንግስት የጥፋት አዋጅ እያራገበና የጥፋ አዋጁን እያስፈፀመ ያለውን የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን አሚኮን በምክትል ስራ አስፈፃሚነት የሚመራው የብልፅግናው ሹም በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል ዝርዝሩን ይዘነዋል፡፡

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ከስሙ በስተቀር ለአማራ ህዝብ የሰራውና የፈየደው አንድም ነገር እንደሌለ ግልፅ ነው፡፡

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በአማራ ህዝብ ገንዘብና በአማራ ህዝብ ስም የተቋቋመ ቢሆንም እያደረገ ያለው ተግባር ግን ለጠላት ተግባር ማስፈፀሚያና የአማራን ህዝብ የጥፋት አዋጅ ማስተግበር ሆኖ ቀጥሏል።

ይህን ተግባሩን እንዲያቆምና ከብልፅግናው ቡድን በላይ የኦሮሙማው ሙቭመንት አስተግባሪና አስፈፃሚ ካልሆንን የሚሉ የራሱ የአማራው ተወላጅ የአሚኬ ብአዴኖችን በአማራ ፋኖ ተደጋጋሚ መልዕክት ቢሰጣቸውም በእንቢታ ቆይተዋል።

በዚህ የጥፋት ተግባራቸውም በርካታ ንፁሀን በብልፅግናው ቡድን ሲገደሉ፣ ሲፈናቀሉና ሲረሸኑ በዝምታ እያለፉ በአማራ ህዝብ እንባና ደም ለብልፅግናው ቡድን እስክስታ ሲወርዱ የነበሩ ብአዴናውያን በቁጥጥር ስር እየዋሉ ይገኛሉ።

ከነዚህ ውስጥ አንዱና ዋነኛው አሁን የተያዘው የአሚኮ ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ አንተነህ መንግስቴና የፕሮግራም ክፍል ኃላፊ ጋዜጠኛ ደምሳቸው ፈንታ ተይዘዋል።

ተደጋጋሚ ተቋማዊ ማሻሻያ እንዲደረግና በፋኖ ሀየረሎች ላይ በተቋሙ በኩል ያለው ፋኖን የማጥላላት ዘመቻ እንዲቀንስ ተደጋጋሚ መልዕክት የደረሰው አቶ አንተነህ መንግስቴ አሁን ላይ በፋኖ ሀይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።

በህዝብ ንብረት የተቋቋመው ድርጅቱ ለአማራ ህዝብ ክብርና ጥቅም የቆሙ ሰራተኞቹን በደመወዝና በአገዛዙ ወታደሮች ከማስፈራራትና ከማሳደድ ሳይቆጠብ አሁንም የአማራን የህልውና ትግለወ እንዳራከሰ ቀጥሏል ያሉት የትግሉ ሰዎች አሁንም የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ

1 Comment

  1. አሚኮ ሲጀመርም የታመመ ነበር።

    አሚኮ መቼ ሞተ? አብይ አህመድ በደመቀ መኮነን ታግዞ አዲስ አበባ ወስዶ በብብቱ ሲያስቀምጠው ሞተ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

fano 67
Previous Story

ስብሰባው በተቃውሞ ተበተነ | የአብይና የጌታቸዉ ሴራ | የጀኔራሎች ስብሰባ ላይ ጥቃት ተፈፀመ | ሙሴቬኒ ስለኢትዮጵያ የብሄር ፖለቲካ | መለስ ነገሩኝ ያሉት ሚስጥር

456668044 2750390011800456 1633307317353207615 n
Next Story

አሜሪካ በዐቢይ አህመድ የተሾሙትን የሌንጮ ባቲን የአምባሳደርነት ሹመት አልቀበልም አለች

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop